Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

1 Corinthians

15

1And I make known to you, brethren, the good news that I proclaimed to you, which also ye did receive, in which also ye have stood,
1ወንድሞች ሆይ፥ የሰበክሁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በእርሱም ደግሞ የቆማችሁበትን በእርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባችኋለሁ፤
2through which also ye are being saved, in what words I proclaimed good news to you, if ye hold fast, except ye did believe in vain,
2በከንቱ ካላመናችሁ በቀር፥ ብታስቡት፥ በምን ቃል እንደ ሰበክሁላችሁ አሳስባችኋለሁ።
3for I delivered to you first, what also I did receive, that Christ died for our sins, according to the Writings,
3እኔ ደግሞ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ እንዲህ ብዬ። መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥
4and that he was buried, and that he hath risen on the third day, according to the Writings,
4መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥
5and that he appeared to Cephas, then to the twelve,
5ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ፤
6afterwards he appeared to above five hundred brethren at once, of whom the greater part remain till now, and certain also did fall asleep;
6ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነርሱም የሚበዙቱ እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል፤
7afterwards he appeared to James, then to all the apostles.
7ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ፤
8And last of all — as to the untimely birth — he appeared also to me,
8ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ።
9for I am the least of the apostles, who am not worthy to be called an apostle, because I did persecute the assembly of God,
9እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ፤
10and by the grace of God I am what I am, and His grace that [is] towards me came not in vain, but more abundantly than they all did I labour, yet not I, but the grace of God that [is] with me;
10ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።
11whether, then, I or they, so we preach, and so ye did believe.
11እንግዲህስ እኔ ብሆን እነርሱም ቢሆኑ እንዲሁ እንሰብካለን እንዲሁም አመናችሁ።
12And if Christ is preached, that out of the dead he hath risen, how say certain among you, that there is no rising again of dead persons?
12ክርስቶስ ከሙታን እንደ ተነሣ የሚሰበክ ከሆነ ግን ከእናንተ አንዳንዶቹ። ትንሣኤ ሙታን የለም እንዴት ይላሉ?
13and if there be no rising again of dead persons, neither hath Christ risen;
13ትንሣኤ ሙታንስ ከሌለ ክርስቶስ አልተነሣማ፤
14and if Christ hath not risen, then void [is] our preaching, and void also your faith,
14ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት፤
15and we also are found false witnesses of God, because we did testify of God that He raised up the Christ, whom He did not raise if then dead persons do not rise;
15ደግሞም። ክርስቶስን አስነሥቶታል ብለን በእግዚአብሔር ላይ ስለ መሰከርን ሐሰተኞች የእግዚአብሔር ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፤ ሙታን ግን የማይነሡ ከሆነ እርሱን አላስነሣውም።
16for if dead persons do not rise, neither hath Christ risen,
16ሙታን የማይነሡ ከሆነ ክርስቶስ አልተነሣማ፤
17and if Christ hath not risen, vain is your faith, ye are yet in your sins;
17ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት፤ እስከ አሁን ድረስ በኃጢአታችሁ አላችሁ።
18then, also, those having fallen asleep in Christ did perish;
18እንግዲያስ በክርስቶስ ያንቀላፉት ደግሞ ጠፍተዋላ።
19if in this life we have hope in Christ only, of all men we are most to be pitied.
19በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።
20And now, Christ hath risen out of the dead — the first-fruits of those sleeping he became,
20አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።
21for since through man [is] the death, also through man [is] a rising again of the dead,
21ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።
22for even as in Adam all die, so also in the Christ all shall be made alive,
22ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና።
23and each in his proper order, a first-fruit Christ, afterwards those who are the Christ`s, in his presence,
23ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ተራ ይሆናል፤ ክርስቶስ እንደ በኩራት ነው፥ በኋላም በመምጣቱ ለክርስቶስ የሆኑት ናቸው፤
24then — the end, when he may deliver up the reign to God, even the Father, when he may have made useless all rule, and all authority and power —
24በኋላም፥ መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ አለቅነትንም ሁሉና ሥልጣንን ሁሉ ኃይልንም በሻረ ጊዜ፥ ፍጻሜ ይሆናል።
25for it behoveth him to reign till he may have put all the enemies under his feet —
25ጠላቶቹን ሁሉ ከእግሩ በታች እስኪያደርግ ድረስ ሊነግሥ ይገባዋልና።
26the last enemy is done away — death;
26የኋለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው፤
27for all things He did put under his feet, and, when one may say that all things have been subjected, [it is] evident that He is excepted who did subject the all things to him,
27ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቶአልና። ነገር ግን። ሁሉ ተገዝቶአል ሲል፥ ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው።
28and when the all things may be subjected to him, then the Son also himself shall be subject to Him, who did subject to him the all things, that God may be the all in all.
28ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል።
29Seeing what shall they do who are baptized for the dead, if the dead do not rise at all? why also are they baptized for the dead?
29እንዲያማ ካልሆነ፥ ስለ ሙታን የሚጠመቁ ምን ያደርጋሉ? ሙታንስ ከቶ የማይነሡ ከሆነ፥ ስለ እነርሱ የሚጠመቁ ስለ ምንድር ነው?
30why also do we stand in peril every hour?
30እኛስ ዘወትር በሚያስፈራ ኑሮ የምንኖር ስለ ምንድር ነው?
31Every day do I die, by the glorying of you that I have in Christ Jesus our Lord:
31በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ ባለኝ በእናንተ ትምክህት እየማልሁ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ዕለት ዕለት እሞታለሁ።
32if after the manner of a man with wild beasts I fought in Ephesus, what the advantage to me if the dead do not rise? let us eat and drink, for to-morrow we die!
32እንደ ሰው በኤፌሶን ከአውሬ ጋር ከታገልሁ፥ ሙታንስ የማይነሡ ከሆነ፥ ምን ይጠቅመኛል? ነገ እንሞታለንና እንብላና እንጠጣ።
33Be not led astray; evil communications corrupt good manners;
33አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል።
34awake up, as is right, and sin not; for certain have an ignorance of God; for shame to you I say [it].
34በጽድቅ ንቁ ኃጢአትንም አትሥሩ፤ እግዚአብሔርን የማያውቁ አሉና፤ አሳፍራችሁ ዘንድ ይህን እላለሁ።
35But some one will say, `How do the dead rise?
35ነገር ግን ሰው። ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።
36unwise! thou — what thou dost sow is not quickened except it may die;
36አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም፤
37and that which thou dost sow, not the body that shall be dost thou sow, but bare grain, it may be of wheat, or of some one of the others,
37የምትዘራውም፥ ስንዴ ቢሆን ከሌላም ዓይነት የአንዱ ቢሆን፥ ቅንጣት ብቻ ነው እንጂ የምትዘራው የሚሆነውን አካል አይደለም፤
38and God doth give to it a body according as He willed, and to each of the seeds its proper body.
38እግዚአብሔር ግን እንደ ወደደ አካልን ይሰጠዋል ከዘሮችም ለእያንዳንዱ የገዛ አካሉን ይሰጠዋል።
39All flesh [is] not the same flesh, but there is one flesh of men, and another flesh of beasts, and another of fishes, and another of birds;
39ሥጋ ሁሉ አንድ አይደለም፥ የሰው ሥጋ ግን አንድ ነው፥ የእንስሳም ሥጋ ሌላ ነው፥ የወፎችም ሥጋ ሌላ ነው፥ የዓሣም ሥጋ ሌላ ነው።
40and [there are] heavenly bodies, and earthly bodies; but one [is] the glory of the heavenly, and another that of the earthly;
40ደግሞ ሰማያዊ አካል አለ፥ ምድራዊም አካል አለ፤ ነገር ግን የሰማያዊ አካል ክብር ልዩ ነው፥ የምድራዊም አካል ክብር ልዩ ነው።
41one glory of sun, and another glory of moon, and another glory of stars, for star from star doth differ in glory.
41የፀሐይ ክብር አንድ ነው የጨረቃም ክብር ሌላ ነው የከዋክብትም ክብር ሌላ ነው፤ በክብር አንዱ ኮከብ ከሌላው ኮከብ ይለያልና።
42So also [is] the rising again of the dead: it is sown in corruption, it is raised in incorruption;
42የሙታን ትንሣኤ ደግሞ እንዲሁ ነው። በመበስበስ ይዘራል፥ ባለመበስበስ ይነሣል፤
43it is sown in dishonour, it is raised in glory; it is sown in weakness, it is raised in power;
43በውርደት ይዘራል፥ በክብር ይነሣል፤ በድካም ይዘራል፥ በኃይል ይነሣል፤
44it is sown a natural body, it is raised a spiritual body; there is a natural body, and there is a spiritual body;
44ፍጥረታዊ አካል ይዘራል፥ መንፈሳዊ አካል ይነሣል። ፍጥረታዊ አካል ካለ መንፈሳዊ አካል ደግሞ አለ።
45so also it hath been written, `The first man Adam became a living creature,` the last Adam [is] for a life-giving spirit,
45እንዲሁ ደግሞ። ፊተኛው ሰው አዳም ሕያው ነፍስ ሆነ ተብሎ ተጽፎአል፤ ኋለኛው አዳም ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ሆነ።
46but that which is spiritual [is] not first, but that which [was] natural, afterwards that which [is] spiritual.
46ነገር ግን አስቀድሞ ፍጥረታዊው ቀጥሎም መንፈሳዊው ነው እንጂ መንፈሳዊው መጀመሪያ አይደለም።
47The first man [is] out of the earth, earthy; the second man [is] the Lord out of heaven;
47የፊተኛው ሰው ከመሬት መሬታዊ ነው፤ ሁለተኛው ሰው ከሰማይ ነው።
48as [is] the earthy, such [are] also the earthy; and as [is] the heavenly, such [are] also the heavenly;
48መሬታዊው እንደ ሆነ መሬታውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው፥ ሰማያዊው እንደ ሆነ ሰማያውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው።
49and, according as we did bear the image of the earthy, we shall bear also the image of the heavenly.
49የዚያንም የመሬታዊውን መልክ እንደ ለበስን የሰማያዊውን መልክ ደግሞ እንለብሳለን።
50And this I say, brethren, that flesh and blood the reign of God is not able to inherit, nor doth the corruption inherit the incorruption;
50ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እላለሁ። ሥጋና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊወርሱ አይችሉም፥ የሚበሰብሰውም የማይበሰብሰውን አይወርስም።
51lo, I tell you a secret; we indeed shall not all sleep, and we all shall be changed;
51እነሆ፥ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበት ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።
52in a moment, in the twinkling of an eye, in the last trumpet, for it shall sound, and the dead shall be raised incorruptible, and we — we shall be changed:
53ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና።
53for it behoveth this corruptible to put on incorruption, and this mortal to put on immortality;
54ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ። ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል።
54and when this corruptible may have put on incorruption, and this mortal may have put on immortality, then shall be brought to pass the word that hath been written, `The Death was swallowed up — to victory;
55ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ?
55where, O Death, thy sting? where, O Hades, thy victory?`
56የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው፤
56and the sting of the death [is] the sin, and the power of the sin the law;
57ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።
57and to God — thanks, to Him who is giving us the victory through our Lord Jesus Christ;
58ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።
58so that, my brethren beloved, become ye stedfast, unmovable, abounding in the work of the Lord at all times, knowing that your labour is not vain in the Lord.