Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

1 Corinthians

16

1And concerning the collection that [is] for the saints, as I directed to the assemblies of Galatia, so also ye — do ye;
1ለቅዱሳንም ገንዘብን ስለ ማዋጣት፥ ለገላትያ አብያተ ክርስቲያናት እንደ ደነገግሁት እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ።
2on every first [day] of the week, let each one of you lay by him, treasuring up whatever he may have prospered, that when I may come then collections may not be made;
2እኔ ስመጣ ይህ የገንዘብ ማዋጣት ያን ጊዜ እንዳይሆን፥ ከእናንተ እያንዳንዱ በየሳምንቱ በፊተኛው ቀን እንደ ቀናው መጠን እያስቀረ በቤቱ ያስቀምጥ።
3and whenever I may come, whomsoever ye may approve, through letters, these I will send to carry your favour to Jerusalem;
3ስመጣም ማናቸውም ቢሆኑ የታመኑ የሚመስሉአችሁ ሰዎች ቸርነታችሁን ወደ ኢየሩሳሌም ያደርሱ ዘንድ ደብዳቤ ሰጥቼ እልካቸዋለሁ፤
4and if it be meet for me also to go, with me they shall go.
4እኔ ደግሞ ልሄድ የሚገባኝ ብሆን ከእኔ ጋር አብረው ይሄዳሉ።
5And I will come unto you, when I pass through Macedonia — for Macedonia I do pass through —
5በመቄዶንያም ሳልፍ ወደ እናንተ እመጣለሁ፤ በመቄዶንያ አድርጌ አልፋለሁና፤
6and with you, it may be, I will abide, or even winter, that ye may send me forward whithersoever I go,
6እናንተም ወደምሄድበት ወደ ማናቸውም ስፍራ በጉዞዬ እንድትረዱኝ ምናልባት በእናንተ ዘንድ እቆይ ወይም እከርም ይሆናል።
7for I do not wish to see you now in the passing, but I hope to remain a certain time with you, if the Lord may permit;
7አሁን እግረ መንገዴን ሳልፍ ልጎበኛችሁ አልወድምና፤ ጌታ ቢፈቅደው የሆነውን ዘመን በእናንተ ዘንድ ልሰነብት ተስፋ አደርጋለሁና።
8and I will remain in Ephesus till the Pentecost,
8በኤፌሶን ግን እስከ በዓለ ኀምሳ ድረስ እሰነብታለሁ።
9for a door to me hath been opened — great and effectual — and withstanders [are] many.
9ሥራ የሞላበት ትልቅ በር ተከፍቶልኛልና ተቃዋሚዎችም ብዙ ናቸው።
10And if Timotheus may come, see that he may become without fear with you, for the work of the Lord he doth work, even as I,
10ጢሞቴዎስም የመጣ እንደ ሆነ በእናንተ ዘንድ ያለ ፍርሃት እንዲኖር ተጠንቀቁ፤ እንደ እኔ ደግሞ የጌታን ሥራ ይሠራልና፤ እንግዲህ ማንም አይናቀው።
11no one, then, may despise him; and send ye him forward in peace, that he may come to me, for I expect him with the brethren;
11ነገር ግን ከወንድሞቹ ጋር እጠብቀዋለሁና ወደ እኔ ይመጣ ዘንድ በሰላም በጉዞው እርዱት።
12and concerning Apollos our brother, much I did entreat him that he may come unto you with the brethren, and it was not at all [his] will that he may come now, and he will come when he may find convenient.
12ስለ ወንድማችን ስለ አጵሎስ ግን ከወንድሞቹ ጋር ወደ እናንተ ሊሄድ እጅግ አድርጌ ለምኜው ነበር፤ ዛሬም ለመምጣት ከቶ ፈቃድ አልነበረውም፥ ሲመቸው ግን ይመጣል።
13Watch ye, stand in the faith; be men, be strong;
13ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።
14let all your things be done in love.
14በእናንተ ዘንድ ሁሉ በፍቅር ይሁን።
15And I entreat you, brethren, ye have known the household of Stephanas, that it is the first-fruit of Achaia, and to the ministration to the saints they did set themselves —
15ወንድሞች ሆይ፥ የእስጢፋኖስ ቤተ ሰዎች የአካይያ በኩራት እንደ ሆኑ ቅዱሳንንም ለማገልገል ራሳቸውን እንደ ሰጡ ታውቃላችሁ፤
16that ye also be subject to such, and to every one who is working with [us] and labouring;
16እንደ እነርሱ ላሉትና አብሮ ለሚሠራ ለሚደክምም ሁሉ እናንተም እንድትገዙ እለምናችኋለሁ።
17and I rejoice over the presence of Stephanas, and Fortunatus, and Achaicus, because the lack of you did these fill up;
17በእስጢፋኖስና በፈርዶናጥስ በአካይቆስም መምጣት ደስ ይለኛል፥ እናንተ ስለሌላችሁ የጎደለኝን ፈጽመዋልና፤ መንፈሴንና መንፈሳችሁን አሳርፈዋልና።
18for they did refresh my spirit and yours; acknowledge ye, therefore, those who [are] such.
18እንግዲህ እንደነዚህ ያሉትን እወቁአቸው።
19Salute you do the assemblies of Asia; salute you much in the Lord do Aquilas and Priscilla, with the assembly in their house;
19የእስያ አብያተ ክርስቲያናት ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። አቂላና ጵርስቅላ በቤታቸው ካለች ቤተ ክርስቲያን ጋር በጌታ እጅግ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
20salute you do all the brethren; salute ye one another in an holy kiss.
20ወንድሞች ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። በተቀደሰ አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ።
21The salutation of [me] Paul with my hand;
21እኔ ጳውሎስ ይህን ሰላምታ በገዛ እጄ ጽፌአለሁ።
22if any one doth not love the Lord Jesus Christ — let him be anathema! The Lord hath come!
22ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን። ጌታችን ሆይ፥ ና።
23The grace of the Lord Jesus Christ [is] with you;
23የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።
24my love [is] with you all in Christ Jesus. Amen.
24ፍቅሬ በክርስቶስ ኢየሱስ ከሁላችሁ ጋር ነው። አሜን።