Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

1 Corinthians

6

1Dare any one of you, having a matter with the other, go to be judged before the unrighteous, and not before the saints?
1ከእናንተ አንዱ ከባልንጀራው ጋር ሙግት ቢኖረው በቅዱሳን ፊት በመፋረድ ፋንታ በዓመፀኞች ፊት ሊፋረድ ይደፍራልን?
2have ye not known that the saints shall judge the world? and if by you the world is judged, are ye unworthy of the smaller judgments?
2ቅዱሳን በዓለም ላይ እንዲፈርዱ አታውቁምን? በዓለምስ ላይ ብትፈርዱ ከሁሉ ይልቅ ትንሽ ስለሚሆን ነገር ልትፈርዱ አትበቁምን?
3have ye not known that we shall judge messengers? why not then the things of life?
3የትዳር ጉዳይ ይቅርና በመላእክት እንኳ እንድንፈርድ አታውቁምን?
4of the things of life, indeed, then, if ye may have judgment, those despised in the assembly — these cause ye to sit;
4እንግዲህ ስለ ትዳር ጉዳይ የፍርድ ቤት ቢያስፈልጋችሁ በቤተ ክርስቲያን የተናቁትን ሰዎች ፈራጆች አድርጋችሁ ታስቀምጣላችሁን?
5unto your shame I speak: so there is not among you one wise man, not even one, who shall be able to discern in the midst of his brethren!
5አሳፍራችሁ ዘንድ ይህን እላለሁ። እንደዚህ ነውን? በወንድሞች መካከል ሽማግሌ ሊሆን የሚችል አንድ አስተዋይ ሰው በእናንተ ዘንድ አይገኝምን?
6but brother with brother doth go to be judged, and this before unbelievers!
6ነገር ግን ወንድም ወንድሙን ይከሳል፥ ይህም በማያምኑ ፊት ይደረጋልን?
7Already, indeed, then, there is altogether a fault among you, that ye have judgments with one another; wherefore do ye not rather suffer injustice? wherefore be ye not rather defrauded?
7እንግዲህ ፈጽሞ የእርስ በርስ ሙግት እንዳለባችሁ በእናንተ ጉድለት ነው። ብትበደሉ አይሻልምን? ብትታለሉስ አይሻልምን?
8but ye — ye do injustice, and ye defraud, and these — brethren!
8ነገር ግን እናንተ ትበድላላችሁ ታታልሉማላችሁ፥ ያውም ወንድሞቻችሁን።
9have ye not known that the unrighteous the reign of God shall not inherit? be not led astray; neither whoremongers, nor idolaters, nor adulterers, nor effeminate, nor sodomites,
9ወይስ ዓመፀኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንዳይወርሱ አታውቁምን? አትሳቱ፤ ሴሰኞች ቢሆን ወይም ጣዖትን የሚያመልኩ ወይም አመንዝሮች ወይም ቀላጮች ወይም ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ
10nor thieves, nor covetous, nor drunkards, nor revilers, nor extortioners, the reign of God shall inherit.
10ወይም ሌቦች ወይም ገንዘብን የሚመኙ ወይም ሰካሮች ወይም ተሳዳቢዎች ወይም ነጣቂዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።
11And certain of you were these! but ye were washed, but ye were sanctified, but ye were declared righteous, in the name of the Lord Jesus, and in the Spirit of our God.
11ከእናንተም አንዳንዶቹ እንደ እነዚህ ነበራችሁ፤ ነገር ግን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ ታጥባችኋል፥ ተቀድሳችኋል፥ ጸድቃችኋል።
12All things are lawful to me, but all things are not profitable; all things are lawful to me, but I — I will not be under authority by any;
12ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን አይጠቅምም። ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳ አይሠለጥንብኝም።
13the meats [are] for the belly, and the belly for the meats. And God both this and these shall make useless; and the body [is] not for whoredom, but for the Lord, and the Lord for the body;
13መብል ለሆድ ነው፥ ሆድም ለመብል ነው፤ እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። ሥጋ ግን ለጌታ ነው እንጂ ለዝሙት አይደለም፤ ጌታም ለሥጋ ነው፤
14and God both the Lord did raise, and us will raise up through His power.
14እግዚአብሔርም ጌታንም አስነሣ እኛንም በኃይሉ ያስነሣናል።
15Have ye not known that your bodies are members of Christ? having taken, then, the members of the Christ, shall I make [them] members of an harlot? let it be not!
15ሥጋችሁ የክርስቶስ ብልቶች እንደ ሆነ አታውቁምን? እንግዲህ የክርስቶስን ብልቶች ወስጄ የጋለሞታ ብልቶች ላድርጋቸውን? አይገባም።
16have ye not known that he who is joined to the harlot is one body? `for they shall be — saith He — the two for one flesh.`
16ወይስ ከጋለሞታ ጋር የሚተባበር አንድ ሥጋ እንዲሆን አታውቁምን? ሁለቱ አንድ ሥጋ ይሆናሉ ተብሎአልና።
17And he who is joined to the Lord is one spirit;
17ከጌታ ጋር የሚተባበር ግን አንድ መንፈስ ነው።
18flee the whoredom; every sin — whatever a man may commit — is without the body, and he who is committing whoredom, against his own body doth sin.
18ከዝሙት ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከሥጋ ውጭ ነው፤ ዝሙትን የሚሠራ ግን በገዛ ሥጋው ላይ ኃጢአትን ይሠራል።
19Have ye not known that your body is a sanctuary of the Holy Spirit in you, which ye have from God? and ye are not your own,
19ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
20for ye were bought with a price; glorify, then, God in your body and in your spirit, which are God`s.