Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

1 Corinthians

7

1And concerning the things of which ye wrote to me: good [it is] for a man not to touch a woman,
1ስለ ጻፋችሁልኝስ ነገር፥ ከሴት ጋር አለመገናኘት ለሰው መልካም ነው።
2and because of the whoredom let each man have his own wife, and let each woman have her proper husband;
2ነገር ግን ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑረው ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራስዋ ባል ይኑራት።
3to the wife let the husband the due benevolence render, and in like manner also the wife to the husband;
3ባል ለሚስቱ የሚገባትን ያድርግላት፥ እንደዚሁም ደግሞ ሚስቲቱ ለባልዋ።
4the wife over her own body hath not authority, but the husband; and, in like manner also, the husband over his own body hath not authority, but the wife.
4ሚስት በገዛ ሥጋዋ ላይ ሥልጣን የላትም፥ ሥልጣን ለባልዋ ነው እንጂ፤ እንዲሁም ደግሞ ባል በገዛ ሥጋው ላይ ሥልጣን የለውም፥ ሥልጣን ለሚስቱ ነው እንጂ።
5Defraud not one another, except by consent for a time, that ye may be free for fasting and prayer, and again may come together, that the Adversary may not tempt you because of your incontinence;
5ለጸሎት ትተጉ ዘንድ ተስማምታችሁ ለጊዜው ካልሆነ በቀር፥ እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ፤ ራሳችሁን ስለ አለመግዛት ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ።
6and this I say by way of concurrence — not of command,
6ዳሩ ግን ይህን እንደ ፈቃድ እላለሁ እንጂ እንደ ትእዛዝ አይደለም።
7for I wish all men to be even as I myself [am]; but each his own gift hath of God, one indeed thus, and one thus.
7ሰው ሁሉ እንደ እኔ ሊሆን እወዳለሁና፤ ነገር ግን እያንዳንዱ ከእግዚአብሔር ለራሱ የጸጋ ስጦታ አለው፥ አንዱ እንደዚህ ሁለተኛውም እንደዚያ።
8And I say to the unmarried and to the widows: it is good for them if they may remain even as I [am];
8ላላገቡና ለመበለቶች ግን እላለሁ። እንደ እኔ ቢኖሩ ለእነርሱ መልካም ነው፤
9and if they have not continence — let them marry, for it is better to marry than to burn;
9ነገር ግን በምኞት ከመቃጠል መጋባት ይሻላልና ራሳቸውን መግዛት ባይችሉ ያግቡ።
10and to the married I announce — not I, but the Lord — let not a wife separate from a husband:
10ሚስትም ከባልዋ አትለያይ፥ ብትለያይ ግን ሳታገባ ትኑር ወይም ከባልዋ ትታረቅ፥ ባልም ሚስቱን አይተዋት ብዬ የተጋቡትን አዛቸዋለሁ፥ እኔ ግን አላዝም፥ ጌታ እንጂ።
11but and if she may separate, let her remain unmarried, or to the husband let her be reconciled, and let not a husband send away a wife.
12ሌሎችንም እኔ እላለሁ፥ ጌታም አይደለም፤ ከወንድሞች ወገን ያላመነች ሚስት ያለችው ቢኖር እርስዋም ከእርሱ ጋር ልትቀመጥ ብትስማማ፥ አይተዋት፤
12And to the rest I speak — not the Lord — if any brother hath a wife unbelieving, and she is pleased to dwell with him, let him not send her away;
13ያላመነ ባል ያላት ሚስትም ብትኖር ይህ ከእርስዋ ጋር ሊቀመጥ ቢስማማ፥ አትተወው።
13and a woman who hath a husband unbelieving, and he is pleased to dwell with her, let her not send him away;
14ያላመነ ባል በሚስቱ ተቀድሶአልና፥ ያላመነችም ሚስት በባልዋ ተቀድሳለች፤ አለዚያ ልጆቻችሁ ርኵሳን ናቸው፤ አሁን ግን የተቀደሱ ናቸው።
14for the unbelieving husband hath been sanctified in the wife, and the unbelieving wife hath been sanctified in the husband; otherwise your children are unclean, but now they are holy.
15የማያምን ግን ቢለይ ይለይ፤ ወንድም ቢሆን ወይም እኅት እንዲህ በሚመስል ነገር አይገዙም፤ እግዚአብሔር ግን በሰላም ጠርቶናል።
15And, if the unbelieving doth separate himself — let him separate himself: the brother or the sister is not under servitude in such [cases], and in peace hath God called us;
16አንቺ ሴት፥ ባልሽን ታድኚ እንደ ሆንሽ ምን ታውቂአለሽ? ወይስ አንተ ሰው፥ ሚስትህን ታድን እንደ ሆንህ ምን ታውቃለህ?
16for what, hast thou known, O wife, whether the husband thou shalt save? or what, hast thou known, O husband, whether the wife thou shalt save?
17ብቻ ለእያንዳንዱ እግዚአብሔር እንደ ከፈለለት እያንዳንዱም እግዚአብሔር እንደ ጠራው እንዲሁ ይመላለስ። እንዲሁም በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እደነግጋለሁ።
17if not, as God did distribute to each, as the Lord hath called each — so let him walk; and thus in all the assemblies do I direct:
18ማንም ተገርዞ ሳለ ተጠርቶ እንደ ሆነ፥ ወደ አለመገረዝ አይመለስ፤ ማንም ሳይገረዝ ተጠርቶ እንደ ሆነ አይገረዝ።
18being circumcised — was any one called? let him not become uncircumcised; in uncircumcision was any one called? let him not be circumcised;
19መገረዝ ቢሆን አለመገረዝም ቢሆን ከንቱ ነው፥ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ መጠበቅ ነው እንጂ።
19the circumcision is nothing, and the uncircumcision is nothing — but a keeping of the commands of God.
20እያንዳንዱ በተጠራበት መጠራት እንደዚሁ ይኑር።
20Each in the calling in which he was called — in this let him remain;
21ባሪያ ሆነህ ተጠርተህ እንደ ሆነ አይገድህም፤ አርነት ልትወጣ ቢቻልህ ግን አርነትን ተቀበል።
21a servant — wast thou called? be not anxious; but if also thou art able to become free — use [it] rather;
22ባሪያ ሆኖ በጌታ የተጠራ የጌታ ነጻ ነውና፤ እንዲሁም ነጻ ሆኖ የተጠራ የክርስቶስ ባሪያ ነው።
22for he who [is] in the Lord — having been called a servant — is the Lord`s freedman: in like manner also he the freeman, having been called, is servant of Christ:
23በዋጋ ተገዝታችኋል፤ የሰው ባሪያዎች አትሁኑ።
23with a price ye were bought, become not servants of men;
24ወንድሞች ሆይ፥ እያንዳንዱ በተጠራበት እንደዚሁ ሆኖ በእግዚአብሔር ዘንድ ይኑር።
24each, in that in which he was called, brethren, in this let him remain with God.
25ስለ ደናግልም የጌታ ትእዛዝ የለኝም፥ ነገር ግን የታመንሁ እሆን ዘንድ ከጌታ ምሕረትን የተቀበልሁ እንደ መሆኔ ምክር እመክራለሁ።
25And concerning the virgins, a command of the Lord I have not; and I give judgment as having obtained kindness from the Lord to be faithful:
26እንግዲህ ስለ አሁኑ ችግር ይህ መልካም ይመስለኛል፤ ሰው እንዲህ ሆኖ ቢኖር መልካም ነው።
26I suppose, therefore, this to be good because of the present necessity, that [it is] good for a man that the matter be thus: —
27በሚስት ታስረህ እንደ ሆንህ መፋታትን አትሻ፤ በሚስት አልታሰርህ እንደ ሆንህ ሚስትን አትሻ።
27Hast thou been bound to a wife? seek not to be loosed; hast thou been loosed from a wife? seek not a wife.
28ብታገባ ግን ኃጢአት አትሠራም ድንግሊቱም ብታገባ ኃጢአት አትሠራም፤ ነገር ግን እንዲህ በሚያደርጉ በሥጋቸው ላይ መከራ ይሆንባቸዋል፥ እኔም እራራላችሁ ነበር።
28But and if thou mayest marry, thou didst not sin; and if the virgin may marry, she did not sin; and such shall have tribulation in the flesh: and I spare you.
29ዳሩ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እናገራለሁ፤ ዘመኑ አጭር ሆኖአል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሚስቶች ያሉአቸው እንደሌላቸው ይሁኑ፥
29And this I say, brethren, the time henceforth is having been shortened — that both those having wives may be as not having;
30የሚያለቅሱም እንደማያለቅሱ፥ ደስ የሚላቸውም ደስ እንደማይላቸው፥
30and those weeping, as not weeping; and those rejoicing, as not rejoicing; and those buying, as not possessing;
31የሚገዙም ምንም እንደሌላቸው፥ በዚችም ዓለም የሚጠቀሙ በሙሉ እንደማይጠቀሙባት ይሁኑ፤ የዚች ዓለም መልክ አላፊ ነውና።
31and those using this world, as not using [it] up; for passing away is the fashion of this world.
32ነገር ግን ያለ አሳብ ልትኖሩ እወዳለሁ። ያላገባው ጌታን እንዴት ደስ እንዲያሰኘው የጌታን ነገር ያስባል፤
32And I wish you to be without anxiety; the unmarried is anxious for the things of the Lord, how he shall please the Lord;
33ያገባው ግን ሚስቱን እንዴት ደስ እንዲያሰኛት የዓለምን ነገር ያስባል፥ ልቡም ተከፍሎአል።
33and the married is anxious for the things of the world, how he shall please the wife.
34ያልተጋባች ሴትና ድንግል በሥጋም በነፍስም እንዲቀደሱ የጌታን ነገር ያስባሉ፤ የተጋባች ግን ባልዋን እንዴት ደስ እንድታሰኘው የዓለምን ነገር ታስባለች።
34The wife and the virgin have been distinguished: the unmarried is anxious for the things of the Lord, that she may be holy both in body and in spirit, and the married is anxious for the things of the world, how she shall please the husband.
35ይህንም ለራሳችሁ ጥቅም እላለሁ፤ በአገባብ እንድትኖሩ ሳትባክኑም በጌታ እንድትጸኑ ነው እንጂ ላጠምዳችሁ ብዬ አይደለም።
35And this for your own profit I say: not that I may cast a noose upon you, but for the seemliness and devotedness to the Lord, undistractedly,
36ዳሩ ግን ማግባት ወደሚገባው ዕድሜ በደረሰ ጊዜ ስለ ድንግልናው ያፈረ ሰው ቢኖር፥ የወደደውን ያድርግ፤ ኃጢአት የለበትም፤ ይጋቡ።
36and if any one doth think [it] to be unseemly to his virgin, if she may be beyond the bloom of age, and it ought so to be, what he willeth let him do; he doth not sin — let him marry.
37ሳይናወጥ በልቡ የጸና ግን ግድ የለበትም፥ የወደደውን እንዲያደርግ ተፈቅዶለታል፤ ድንግልናውንም በልቡ ይጠብቅ ዘንድ ቢጸና፥ መልካም አደረገ።
37And he who hath stood stedfast in the heart — not having necessity — and hath authority over his own will, and this he hath determined in his heart — to keep his own virgin — doth well;
38እንዲሁም ድንግልን ያገባ መልካም አደረገ ያላገባም የተሻለ አደረገ።
38so that both he who is giving in marriage doth well, and he who is not giving in marriage doth better.
39ሴት ባልዋ በሕይወት ሳለ የታሰረች ናት፤ ባልዋ ቢሞት ግን በጌታ ይሁን እንጂ የወደደችውን ልታገባ ነጻነት አላት።
39A wife hath been bound by law as long time as her husband may live, and if her husband may sleep, she is free to be married to whom she will — only in the Lord;
40እንደ ምክሬ ግን እንዳለች ብትኖር ደስተኛ ናት፤ እኔም ደግሞ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ያለ ይመስለኛል።
40and she is happier if she may so remain — according to my judgment; and I think I also have the Spirit of God.