1O that ye were bearing with me a little of the folly, but ye also do bear with me:
1በጥቂቱ ሞኝነቴ ብትታገሡኝ መልካም ይሆን ነበር፤ ቢሆንም በእርግጥ ታገሡኝ።
2for I am zealous for you with zeal of God, for I did betroth you to one husband, a pure virgin, to present to Christ,
2በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና፤
3and I fear, lest, as the serpent did beguile Eve in his subtilty, so your minds may be corrupted from the simplicity that [is] in the Christ;
3ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ።
4for if, indeed, he who is coming doth preach another Jesus whom we did not preach, or another Spirit ye receive which ye did not receive, or other good news which ye did not accept — well were ye bearing [it],
4የሚመጣውም ያልሰበክነውን ሌላ ኢየሱስ ቢሰብክ፥ ወይም ያላገኛችሁትን ልዩ መንፈስ ወይም ያልተቀበላችሁትን ልዩ ወንጌል ብታገኙ፥ በመልካም ትታገሡታላችሁ።
5for I reckon that I have been nothing behind the very chiefest apostles,
5ከእነዚህ ከዋነኞቹ ሐዋርያት በአንድ ነገር እንኳ እንደ ጎደልሁ ራሴን አልቆጥርም።
6and even if unlearned in word — yet not in knowledge, but in every thing we were made manifest in all things to you.
6በአነጋገሬ ያልተማርሁ ብሆን እንኳ፥ በእውቀት ግን እንዲህ አይደለሁም። ነገር ግን በሰው ሁሉ መካከል በነገር ሁሉ ተገልጠንላችኋል።
7The sin did I do — myself humbling that ye might be exalted, because freely the good news of God I did proclaim to you?
7ወይስ የእግዚአብሔርን ወንጌል ያለ ደመወዝ ስለ ሰበክሁላችሁ፥ እናንተ ከፍ እንድትሉ ራሴን እያዋረድሁ ኃጢአት አድርጌ ይሆንን?
8other assemblies I did rob, having taken wages, for your ministration;
8እናንተን ለማገልገል ደመወዝ እየተቀበልሁ ሌሎችን አብያተ ክርስቲያናት ዘረፍሁ።
9and being present with you, and having been in want, I was chargeable to no one, for my lack did the brethren supply — having come from Macedonia — and in everything burdenless to you I did keep myself, and will keep.
9ከእናንተም ጋር ሳለሁ በጎደለኝ ጊዜ፥ በማንም አልከበድሁበትም፤ ከመቄዶንያ የመጡት ወንድሞች የጎደለኝን በሙሉ ሰጥተዋልና፤ በነገርም ሁሉ እንዳልከብድባችሁ ተጠነቀቅሁ እጠነቀቅማለሁ።
10The truth of Christ is in me, because this boasting shall not be stopped in regard to me in the regions of Achaia;
10የክርስቶስ እውነት በእኔ እንዳለ፥ ይህ ትምክህት በእኔ ዘንድ በአካይያ አገር አይከለከልም።
11wherefore? because I do not love you? God hath known!
11ስለ ምን? ስለማልወዳችሁ ነውን? እግዚአብሔር ያውቃል።
12and what I do, I also will do, that I may cut off the occasion of those wishing an occasion, that in that which they boast they may be found according as we also;
12ነገር ግን በዚያ በሚመኩበት እንደ እኛ ሆነው ሊገኙ፥ ምክንያትን ከሚፈልጉቱ ምክንያትን እቆርጥ ዘንድ አሁን የማደርገውን ከዚህ ወዲህ ደግሞ አደርጋለሁ።
13for those such [are] false apostles, deceitful workers, transforming themselves into apostles of Christ,
13እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና።
14and no wonder — for even the Adversary doth transform himself into a messenger of light;
14ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።
15no great thing, then, if also his ministrants do transform themselves as ministrants of righteousness — whose end shall be according to their works.
15እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፤ ፍጻሜአቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል።
16Again I say, may no one think me to be a fool; and if otherwise, even as a fool receive me, that I also a little may boast.
16እንደ ገና እላለሁ። ለማንም ሰው ሞኝ የሆንሁ አይምሰለው፤ ያለዚያ ግን እኔ ደግሞ ጥቂት እመካ ዘንድ እንደ ሞኝ እንኳ ሆኜ ተቀበሉኝ።
17That which I speak, I speak not according to the Lord, but as in foolishness, in this the confidence of boasting;
17እንደዚህ ታምኜ ስመካ የምናገረው፥ በሞኝነት እንጂ ጌታ እንዳዘዘኝ አልናገርም።
18since many boast according to the flesh, I also will boast:
18ብዙዎች በዓለማዊ ነገር ስለሚመኩ እኔ ደግሞ እመካለሁ።
19for gladly do ye bear with the fools — being wise,
19ልባሞች ስለምትሆኑ በደስታ ሞኞችን ትታገሣላችሁና፤
20for ye bear, if any one is bringing you under bondage, if any one doth devour, if any one doth take away, if any one doth exalt himself, if any one on the face doth smite you;
20ማንም ባሪያዎች ቢያደርጋችሁ፥ ማንም ቢበላችሁ፥ ማንም ቢቀማችሁ፥ ማንም ቢኮራባችሁ፥ ማንም ፊታችሁን በጥፊ ቢመታችሁ ትታገሣላችሁና።
21in reference to dishonour I speak, how that we were weak, and in whatever any one is bold — in foolishness I say [it] — I also am bold.
21ደካሞች መስለን እንደ ነበርን በውርደት እላለሁ። ነገር ግን በሞኝነት እላለሁ፤ ማንም በሚደፍርበት እኔ ደግሞ እደፍርበታለሁ።
22Hebrews are they? I also! Israelites are they? I also! seed of Abraham are they? I also!
22ዕብራውያን ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ። የእስራኤል ወገን ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ። የአብርሃም ዘር ናቸውን? እኔ ደግሞ ነኝ። የክርስቶስ አገልጋዮች ናቸውን?
23ministrants of Christ are they? — as beside myself I speak — I more; in labours more abundantly, in stripes above measure, in prisons more frequently, in deaths many times;
23እንደ እብድ ሰው እላለሁ፤ እኔ እበልጣለሁ፤ በድካም አብዝቼ፥ በመገረፍ አብዝቼ፥ በመታሰር አትርፌ፥ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ።
24from Jews five times forty [stripes] save one I did receive;
24አይሁድ አንድ ሲጎድል አርባ ግርፋት አምስት ጊዜ ገረፉኝ።
25thrice was I beaten with rods, once was I stoned, thrice was I shipwrecked, a night and a day in the deep I have passed;
25ሦስት ጊዜ በበትር ተመታሁ፤ አንድ ጊዜ በድንጋይ ተወገርሁ፤ መርከቤ ሦስት ጊዜ ተሰበረ፤ ሌሊትና ቀን በባሕር ውስጥ ኖርሁ።
26journeyings many times, perils of rivers, perils of robbers, perils from kindred, perils from nations, perils in city, perils in wilderness, perils in sea, perils among false brethren;
26ብዙ ጊዜ በመንገድ ሄድሁ፤ በወንዝ ፍርሃት፥ በወንበዴዎች ፍርሃት፥ በወገኔ በኩል ፍርሃት፥ በአሕዛብ በኩል ፍርሃት፥ በከተማ ፍርሃት፥ በምድረ በዳ ፍርሃት፥ በባሕር ፍርሃት፥ በውሸተኞች ወንድሞች በኩል ፍርሃት ነበረብኝ፤
27in laboriousness and painfulness, in watchings many times, in hunger and thirst, in fastings many times, in cold and nakedness;
27በድካምና በጥረት ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት፥ በራብና በጥም ብዙ ጊዜም በመጦም፥ በብርድና በራቁትነት ነበርሁ።
28apart from the things without — the crowding upon me that is daily — the care of all the assemblies.
28የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።
29Who is infirm, and I am not infirm? who is stumbled, and I am not fired;
29የሚደክም ማን ነው፥ እኔም አልደክምምን? የሚሰናከል ማን ነው፥ እኔም አልናደድምን?
30if to boast it behoveth [me], of the things of my infirmity I will boast;
30ትምክህት የሚያስፈልግ ከሆነ፥ ከድካሜ በሚሆነው ነገር እመካለሁ።
31the God and Father of our Lord Jesus Christ — who is blessed to the ages — hath known that I do not lie! —
31ለዘላለም የተባረከ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት እንዳልዋሽ ያውቃል።
32In Damascus the ethnarch of Aretas the king was watching the city of the Damascenes, wishing to seize me,
32በደማስቆ አርስጦስዮስ ከተባለ ንጉሥ በታች የሆነ የሕዝብ ገዥ ሊይዘኝ እየወደደ የደማስቆ ሰዎችን ከተማ ያስጠብቅ ነበር፥
33and through a window in a rope basket I was let down, through the wall, and fled out of his hands.
33በቅጥሩም ባለ መስኮት በቅርጫት አወረዱኝና ከእጁ አመለጥሁ።