Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

2 Corinthians

12

1To boast, really, is not profitable for me, for I will come to visions and revelations of the Lord.
1ትምክህት የሚያስፈልግ ነው፤ አይጠቅምም ነገር ግን ከጌታ ወዳለው ራእይና መገለጥ እመጣለሁ።
2I have known a man in Christ, fourteen years ago — whether in the body I have not known, whether out of the body I have not known, God hath known — such an one being caught away unto the third heaven;
2ሰውን በክርስቶስ አውቃለሁ፥ በሥጋ እንደ ሆነ አላውቅም ወይም ከሥጋ ውጭ እንደ ሆነ አላውቅም፥ እግዚአብሔር ያውቃል፤ እንዲህ ያለው ሰው ከአሥራ አራት ዓመት በፊት እስከ ሦስተኛው ሰማይ ድረስ ተነጠቀ።
3and I have known such a man — whether in the body, whether out of the body, I have not known, God hath known, —
3እንዲህ ያለውንም ሰው አውቃለሁ፥ በሥጋ እንደ ሆነ ወይም ያለ ሥጋ እንደ ሆነ አላውቅም፥ እግዚአብሔር ያውቃል፤
4that he was caught away to the paradise, and heard unutterable sayings, that it is not possible for man to speak.
4ወደ ገነት ተነጠቀ፥ ሰውም ሊናገር የማይገባውን የማይነገረውን ቃል ሰማ።
5Of such an one I will boast, and of myself I will not boast, except in my infirmities,
5እንደዚህ ስላለው እመካለሁ፥ ስለ ራሴ ግን ከድካሜ በቀር አልመካም።
6for if I may wish to boast, I shall not be a fool, for truth I will say; but I forebear, lest any one in regard to me may think anything above what he doth see me, or doth hear anything of me;
6ልመካ ብወድስ ሞኝ አልሆንም፥ እውነትን እላለሁና፤ ነገር ግን ማንም ከሚያይ ከእኔም ከሚሰማ የምበልጥ አድርጎ እንዳይቆጥረኝ ትቼአለሁ።
7and that by the exceeding greatness of the revelations I might not be exalted overmuch, there was given to me a thorn in the flesh, a messenger of the Adversary, that he might buffet me, that I might not be exalted overmuch.
7ስለዚህም በመገለጥ ታላቅነት እንዳልታበይ የሥጋዬ መውጊያ፥ እርሱም የሚጎስመኝ የሰይጣን መልእክተኛ ተሰጠኝ፤ ይኸውም እንዳልታበይ ነው።
8Concerning this thing thrice the Lord did I call upon, that it might depart from me,
8ስለዚህ ነገር ከእኔ እንዲለይ ሦስት ጊዜ ጌታን ለመንሁ።
9and He said to me, `Sufficient for thee is My grace, for My power in infirmity is perfected;` most gladly, therefore, will I rather boast in my infirmities, that the power of the Christ may rest on me:
9እርሱም። ጸጋዬ ይበቃሃል፥ ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና አለኝ። እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ።
10wherefore I am well pleased in infirmities, in damages, in necessities, in persecutions, in distresses — for Christ; for whenever I am infirm, then I am powerful;
10ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም በመንገላታትም በችግርም በስደትም በጭንቀትም ደስ ይለኛል፤ ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና።
11I have become a fool — boasting; ye — ye did compel me; for I ought by you to have been commended, for in nothing was I behind the very chiefest apostles — even if I am nothing.
11በመመካቴ ሞኝ ሆኜአለሁ፤ እናንተ ግድ አላችሁኝ፤ እናንተ እኔን ልታመሰግኑ ይገባ ነበርና። እኔ ምንም ባልሆን እንኳ፥ ከዋነኞቹ ሐዋርያት በምንም አልጎድልምና።
12The signs, indeed, of the apostle were wrought among you in all patience, in signs, and wonders, and mighty deeds,
12በእርግጥ የሐዋርያነት ምልክት በመካከላችሁ በምልክትና በድንቅ ነገር በተአምራትም በሁሉ ትዕግሥት ተደረገ።
13for what is there in which ye were inferior to the rest of the assemblies, except that I myself was not a burden to you? forgive me this injustice!
13እኔ ራሴ ካልከበድሁባችሁ ከዚህ በቀር፥ ከሌላ ቤተ ክርስቲያን ያነሳችሁበት በምን እኮ ነው? ይህን በደሌን ይቅር በሉልኝ።
14Lo, a third time I am ready to come unto you, and I will not be a burden to you, for I seek not yours, but you, for the children ought not for the parents to lay up, but the parents for the children,
14እነሆ፥ ወደ እናንተ እመጣ ዘንድ ስዘጋጅ ይህ ሦስተኛዬ ነው፤ አልከብድባችሁምም፥ እናንተን እንጂ ያላችሁን አልፈልግምና። ወላጆች ለልጆች እንጂ ልጆች ለወላጆች ገንዘብ ሊያከማቹ አይገባቸውምና።
15and I most gladly will spend and be entirely spent for your souls, even if, more abundantly loving you, less I am loved.
15እኔ ግን ስለ ነፍሳችሁ በብዙ ደስታ ገንዘቤን እከፍላለሁ፥ ራሴን እንኳ እከፍላለሁ። ከመጠን ይልቅ ብወዳችሁ በዚህ ልክ ፍቅራችሁ የሚያንስ ነውን?
16And be it [so], I — I did not burden you, but being crafty, with guile I did take you;
16ይሁን እንጂ እኔ አልከበድሁባችሁም፤ ነገር ግን ሸንጋይ ሆኜ በተንኰል ያዝኋችሁ።
17any one of those whom I have sent unto you — by him did I take advantage of you?
17ወደ እናንተ ከላክኋቸው በአንዱ ስንኳ አታለልኋችሁን?
18I entreated Titus, and did send with [him] the brother; did Titus take advantage of you? in the same spirit did we not walk? — did we not in the same steps?
18ቲቶን መከርሁት ከእርሱም ጋር ወንድሙን ላክሁት፤ ቲቶስ አታለላችሁን? በአንድ መንፈስ አልተመላለስንምን? በአንድ ፍለጋስ አልተመላለስንም?
19Again, think ye that to you we are making defence? before God in Christ do we speak; and the all things, beloved, [are] for your up-building,
19ለእናንተ ስለ ራሳችን እንድንመልስ ሁልጊዜ ይመስላችኋልን? በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን፤ ነገር ግን፥ ወዳጆች፥ እናንተን ልናንጻችሁ ሁሉን እንናገራለን።
20for I fear lest, having come, not such as I wish I may find you, and I — I may be found by you such as ye do not wish, lest there be strifes, envyings, wraths, revelries, evil-speakings, whisperings, puffings up, insurrections,
20ስመጣ፥ እንደምወደው ሳትሆኑ አገኛችሁ ይሆናል እኔም እንደምትወዱት ሳልሆን ታገኙኝ ይሆናል ብዬ እፈራለሁና፤ ምናልባት ክርክር ቅንዓትም ቁጣም አድመኝነትም ሐሜትም ማሾክሾክም ኩራትም ሁከትም ይሆናሉ፤
21lest again having come, my God may humble me in regard to you, and I may bewail many of those having sinned before, and not having reformed concerning the uncleanness, and whoredom, and lasciviousness, that they did practise.
21እንደ ገና ስመጣ በእናንተ ዘንድ አምላኬ እንዲያዋርደኝ፥ አስቀድመውም ኃጢአት ከሠሩትና ስላደረጉት ርኵሰትና ዝሙት መዳራትም ንስሐ ካልገቡት ወገን ስለ ብዙዎች ምናልባት አዝናለሁ ብዬ እፈራለሁ።