1And working together also we call upon [you] that ye receive not in vain the grace of God —
1አብረንም እየሠራን የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ እንዳትቀበሉ ደግሞ እንለምናለን፤
2for He saith, `In an acceptable time I did hear thee, and in a day of salvation I did help thee, lo, now [is] a well-accepted time; lo, now, a day of salvation,` —
2በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።
3in nothing giving any cause of offence, that the ministration may be not blamed,
3አገልግሎታችንም እንዳይነቀፍ በአንዳች ነገር ማሰናከያ ከቶ አንሰጥም።
4but in everything recommending ourselves as God`s ministrants; in much patience, in tribulations, in necessities, in distresses,
4ነገር ግን በሁሉ እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ራሳችንን እናማጥናለን፤
5in stripes, in imprisonments, in insurrections, in labours, in watchings, in fastings,
5በብዙ መጽናት፥ በመከራ፥ በችግር፥ በጭንቀት፥ በመገረፍ፥ በወኅኒ፥ በሁከት፥ በድካም፥ እንቅልፍ በማጣት፥
6in pureness, in knowledge, in long-suffering, in kindness, in the Holy Spirit, in love unfeigned,
6በመጦም፥ በንጽህና፥ በእውቀት፥ በትዕግሥት፥ በቸርነት፥ በመንፈስ ቅዱስ፥ ግብዝነት በሌለው ፍቅር፥ በእውነት ቃል፥
7in the word of truth, in the power of God, through the armour of the righteousness, on the right and on the left,
7በእግዚአብሔር ኃይል፥ ለቀኝና ለግራ በሚሆን በጽድቅ የጦር ዕቃ፥ በክብርና በውርደት፥
8through glory and dishonour, through evil report and good report, as leading astray, and true;
8በክፉ ወሬና በመልካም ወሬ ራሳችንን እናማጥናለን፤ አሳቾች ስንባል እውነተኞች ነን፤
9as unknown, and recognized; as dying, and lo, we live; as chastened, and not put to death;
9ያልታወቁ ስንባል የታወቅን ነን፤ የምንሞት ስንመስል እነሆ ሕያዋን ነን፤ የተቀጣን ስንሆን አንገደልም፤
10as sorrowful, and always rejoicing; as poor, and making many rich; as having nothing, and possessing all things.
10ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው።
11Our mouth hath been open unto you, O Corinthians, our heart hath been enlarged!
11እናንተ የቆሮንቶስ ሰዎች ሆይ፥ አፋችን ለእናንተ ተከፍቶአል ልባችንም ሰፍቶላችኋል፤
12ye are not straitened in us, and ye are straitened in your [own] bowels,
12በእኛ አልጠበባችሁም በሆዳችሁ ግን ጠቦባችኋል፤
13and [as] a recompense of the same kind, (as to children I say [it],) be ye enlarged — also ye!
13ልጆቼ እንደ መሆናችሁ ግን እላችኋለሁ፥ እናንተ ደግሞ ብድራት መልሳችሁልን ተስፋፉ።
14Become not yoked with others — unbelievers, for what partaking [is there] to righteousness and lawlessness?
14ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው?
15and what fellowship to light with darkness? and what concord to Christ with Belial? or what part to a believer with an unbeliever?
15ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው?
16and what agreement to the sanctuary of God with idols? for ye are a sanctuary of the living God, according as God said — `I will dwell in them, and will walk among [them], and I will be their God, and they shall be My people,
16ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስም ከጣዖት ጋር ምን መጋጠም አለው? እኛ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነንና እንዲሁም እግዚአብሔር ተናገረ እንዲህ ሲል። በእነርሱ እኖራለሁ በመካከላቸውም እመላለሳለሁ፥ አምላካቸውም እሆናለሁ እነርሱም ሕዝቤ ይሆናሉ።
17wherefore, come ye forth out of the midst of them, and be separated, saith the Lord, and an unclean thing do not touch, and I — I will receive you,
17ስለዚህም ጌታ። ከመካከላቸው ውጡና የተለያችሁ ሁኑ ርኵስንም አትንኩ ይላል፤ ሁሉንም የሚገዛ ጌታ። እኔም እቀበላችኋለሁ፥ ለእናንተም አባት እሆናለሁ እናንተም ለእኔ ወንድ ልጆችና ሴት ልጆች ትሆናላችሁ ይላል።
18and I will be to you for a Father, and ye — ye shall be to Me for sons and daughters, saith the Lord Almighty.`