Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Galatians

6

1Brethren, if a man also may be overtaken in any trespass, ye who [are] spiritual restore such a one in a spirit of meekness, considering thyself — lest thou also may be tempted;
1ወንድሞች ሆይ፥ ሰው በማናቸውም በደል ስንኳ ቢገኝ፥ መንፈሳውያን የሆናችሁ እናንተ እንደዚህ ያለውን ሰው በየውሃት መንፈስ አቅኑት፤ አንተ ደግሞ እንዳትፈተን ራስህን ጠብቅ።
2of one another the burdens bear ye, and so fill up the law of the Christ,
2ከእናንተ እያንዳንዱ የአንዱን ሸክም ይሸከም እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ።
3for if any one doth think [himself] to be something — being nothing — himself he doth deceive;
3አንዱ ምንም ሳይሆን ምንም የሆነ ቢመስለው ራሱን ያታልላልና።
4and his own work let each one prove, and then in regard to himself alone the glorying he shall have, and not in regard to the other,
4ነገር ግን እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሥራ ይፈትን፥ ከዚያም በኋላ ስለ ሌላው ሰው ያልሆነ ስለ ራሱ ብቻ የሚመካበትን ያገኛል፤
5for each one his own burden shall bear.
5እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሸክም ሊሸከም ነውና።
6And let him who is instructed in the word share with him who is instructing — in all good things.
6ነገር ግን ቃሉን የሚማር ከሚያስተምረው ጋር መልካምን ነገር ሁሉ ይከፋፈል።
7Be not led astray; God is not mocked; for what a man may sow — that also he shall reap,
7አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤
8because he who is sowing to his own flesh, of the flesh shall reap corruption; and he who is sowing to the Spirit, of the Spirit shall reap life age-during;
8በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል።
9and in the doing good we may not be faint-hearted, for at the proper time we shall reap — not desponding;
9ባንዝልም በጊዜው እናጭዳለንና መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት።
10therefore, then, as we have opportunity, may we work the good to all, and especially unto those of the household of the faith.
10እንግዲያስ ጊዜ ካገኘን ዘንድ ለሰው ሁሉ ይልቁንም ለሃይማኖት ቤተ ሰዎች መልካም እናድርግ።
11Ye see in how large letters I have written to you with my own hand;
11እንዴት ባሉ ታላላቆች ፊደላት በእጄ እንደ ጻፍሁላችሁ እዩ።
12as many as are willing to make a good appearance in the flesh, these constrain you to be circumcised — only that for the cross of the Christ they may not be persecuted,
12በሥጋ መልካም ሆነው ሊታዩ የሚወዱ ሁሉ እንድትገረዙ ግድ አሉአችሁ፥ ነገር ግን ስለ ክርስቶስ መስቀል እንዳይሰደዱ ብቻ ነው።
13for neither do those circumcised themselves keep the law, but they wish you to be circumcised, that in your flesh they may glory.
13በሥጋችሁ እንዲመኩ ልትገረዙ ይወዳሉ እንጂ የተገረዙቱ ራሳቸው እንኳ ሕግን አይጠብቁም።
14And for me, let it not be — to glory, except in the cross of our Lord Jesus Christ, through which to me the world hath been crucified, and I to the world;
14ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።
15for in Christ Jesus neither circumcision availeth anything, nor uncircumcision, but a new creation;
15በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት መሆን ይጠቅማል እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና።
16and as many as by this rule do walk — peace upon them, and kindness, and on the Israel of God!
16በዚህም ሥርዓት በሚመላለሱ ሁሉ ላይ በእግዚአብሔር እስራኤልም ላይ ሰላምና ምሕረት ይሁን።
17Henceforth, let no one give me trouble, for I the scars of the Lord Jesus in my body do bear.
17እኔ የኢየሱስን ማኅተም በሥጋዬ ተሸክሜአለሁና ከእንግዲህ ወዲህ አንድ ስንኳ አያድክመኝ።
18The grace of our Lord Jesus Christ [is] with your spirit, brethren! Amen.
18ወንድሞች ሆይ፥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከመንፈሳችሁ ጋር ይሁን። አሜን።