Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

John

1

1In the beginning was the Word, and the Word was with God, and the Word was God;
1በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።
2this one was in the beginning with God;
2ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ።
3all things through him did happen, and without him happened not even one thing that hath happened.
3ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም።
4In him was life, and the life was the light of men,
4በእርሱ ሕይወት ነበረች፥ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረች።
5and the light in the darkness did shine, and the darkness did not perceive it.
5ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም።
6There came a man — having been sent from God — whose name [is] John,
6ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤
7this one came for testimony, that he might testify about the Light, that all might believe through him;
7ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምኑ ይህ ስለ ብርሃን ይመሰክር ዘንድ ለምስክር መጣ።
8that one was not the Light, but — that he might testify about the Light.
8ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ እንጂ፥ እርሱ ብርሃን አልነበረም።
9He was the true Light, which doth enlighten every man, coming to the world;
9ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ይመጣ ነበር።
10in the world he was, and the world through him was made, and the world did not know him:
10በዓለም ነበረ፥ ዓለሙም በእርሱ ሆነ፥ ዓለሙም አላወቀውም።
11to his own things he came, and his own people did not receive him;
11የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም።
12but as many as did receive him to them he gave authority to become sons of God — to those believing in his name,
12ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤
13who — not of blood nor of a will of flesh, nor of a will of man but — of God were begotten.
13እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።
14And the Word became flesh, and did tabernacle among us, and we beheld his glory, glory as of an only begotten of a father, full of grace and truth.
14ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።
15John doth testify concerning him, and hath cried, saying, `This was he of whom I said, He who after me is coming, hath come before me, for he was before me;`
15ዮሐንስ ስለ እርሱ መሰከረ እንዲህም ብሎ ጮኸ። ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ከእኔ በፊት ነበረና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል፤ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነበረ።
16and out of his fulness did we all receive, and grace over-against grace;
16እኛ ሁላችን ከሙላቱ ተቀብለን በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጥቶናልና ሕግ በሙሴ ተሰጥቶ ነበርና፤
17for the law through Moses was given, the grace and the truth through Jesus Christ did come;
17ጸጋና እውነት ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ሆነ።
18God no one hath ever seen; the only begotten Son, who is on the bosom of the Father — he did declare.
18መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው።
19And this is the testimony of John, when the Jews sent out of Jerusalem priests and Levites, that they might question him, `Who art thou?`
19አይሁድም። አንተ ማን ነህ? ብለው ይጠይቁት ዘንድ ከኢየሩሳሌም ካህናትንና ሌዋውያንን በላኩበት ጊዜ፥ የዮሐንስ ምስክርነት ይህ ነው።
20and he confessed and did not deny, and confessed — `I am not the Christ.`
20መሰከረም አልካደምም፤ እኔ ክርስቶስ አይደለሁም ብሎ መሰከረ።
21And they questioned him, `What then? Elijah art thou?` and he saith, `I am not.` — `The prophet art thou?` and he answered, `No.`
21እንኪያስ ማን ነህ? ኤልያስ ነህን? ብለው ጠየቁት። አይደለሁም አለ። ነቢዩ ነህን? አይደለሁም ብሎ መለሰ።
22They said then to him, `Who art thou, that we may give an answer to those sending us? what dost thou say concerning thyself?`
22እንኪያስ። ማን ነህ? ለላኩን መልስ እንድንሰጥ፤ ስለራስህ ምን ትላለህ? አሉት።
23He said, `I [am] a voice of one crying in the wilderness: Make straight the way of the Lord, as said Isaiah the prophet.`
23እርሱም። ነቢዩ ኢሳይያስ እንዳለ። የጌታን መንገድ አቅኑ ብሎ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ እኔ ነኝ አለ።
24And those sent were of the Pharisees,
24የተላኩትም ከፈሪሳውያን ነበሩና። እንኪያስ አንተ ክርስቶስ ወይም ኤልያስ ወይም ነቢዩ ካይደለህ፥ ስለ ምን ታጠምቃለህ? ብለው ጠየቁት።
25and they questioned him and said to him, `Why, then, dost thou baptize, if thou art not the Christ, nor Elijah, nor the prophet?`
26ዮሐንስ መልሶ። እኔ በውኃ አጠምቃለሁ፤ ዳሩ ግን እናንተ የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሞአል፤
26John answered them, saying, `I baptize with water, but in midst of you he hath stood whom ye have not known, this one it is who is coming after me, who hath been before me,
27እኔ የጫማውን ጠፍር ልፈታ የማይገባኝ፥ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ከእኔ ይልቅ የሚከብር ይህ ነው አላቸው።
27of whom I am not worthy that I may loose the cord of his sandal.`
28ይህ ነገር ዮሐንስ ያጠምቅበት በነበረው በዮርዳኖስ ማዶ በቢታንያ በቤተ ራባ ሆነ።
28These things came to pass in Bethabara, beyond the Jordan, where John was baptizing,
29በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ። እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።
29on the morrow John seeth Jesus coming unto him, and saith, `Lo, the Lamb of God, who is taking away the sin of the world;
30አንድ ሰው ከእኔ በኋላ ይመጣል፥ ከእኔም በፊት ነበርና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል ብዬ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነው።
30this is he concerning whom I said, After me doth come a man, who hath come before me, because he was before me:
31እኔም አላውቀውም ነበር፥ ዳሩ ግን ለእስራኤል ይገለጥ ዘንድ ስለዚህ በውኃ እያጠመቅሁ እኔ መጣሁ።
31and I knew him not, but, that he might be manifested to Israel, because of this I came with the water baptizing.
32ዮሐንስም እንዲህ ብሎ መሰከረ። መንፈስ ከሰማይ እንደ ርግብ ሆኖ ሲወርድ አየሁ፤ በእርሱ ላይም ኖረ።
32And John testified, saying — `I have seen the Spirit coming down, as a dove, out of heaven, and it remained on him;
33እኔም አላውቀውም ነበር፥ ዳሩ ግን በውኃ አጠምቅ ዘንድ የላከኝ እርሱ። መንፈስ ሲወርድበትና ሲኖርበት የምታየው፥ በመንፈስ ቅዱስ የሚያጠምቅ እርሱ ነው አለኝ።
33and I did not know him, but he who sent me to baptize with water, He said to me, On whomsoever thou mayst see the Spirit coming down, and remaining on him, this is he who is baptizing with the Holy Spirit;
34እኔም አይቻለሁ እርሱም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ መስክሬአለሁ።
34and I have seen, and have testified, that this is the Son of God.`
35በነገው ደግሞ ዮሐንስ ከደቀ መዛሙርቱም ሁለት ቆመው ነበር፥
35On the morrow, again, John was standing, and two of his disciples,
36ኢየሱስም ሲሄድ ተመልክቶ። እነሆ የእግዚአብሔር በግ አለ።
36and having looked on Jesus walking, he saith, `Lo, the Lamb of God;`
37ሁለቱም ደቀ መዛሙርት ሲናገር ሰምተው ኢየሱስን ተከተሉት።
37and the two disciples heard him speaking, and they followed Jesus.
38ኢየሱስም ዘወር ብሎ ሲከተሉትም አይቶ። ምን ትፈልጋላችሁ? አላቸው። እነርሱም። ረቢ፥ ወዴት ትኖራለህ? አሉት፤ ትርጓሜው መምህር ሆይ ማለት ነው።
38And Jesus having turned, and having beheld them following, saith to them, `What seek ye?` and they said to them, `Rabbi, (which is, being interpreted, Teacher,) where remainest thou?`
40መጥታችሁ እዩ አላቸው። መጥተው የሚኖርበትን አዩ፥ በዚያም ቀን በእርሱ ዘንድ ዋሉ፤ አሥር ሰዓት ያህል ነበረ።
39He saith to them, `Come and see;` they came, and saw where he doth remain, and with him they remained that day and the hour was about the tenth.
41ከዮሐንስ ዘንድ ሰምተው ከተከተሉት ከሁለቱ አንዱ የስምዖን ጴጥሮስ ወንድም እንድርያስ ነበረ።
40Andrew, the brother of Simon Peter, was one of the two who heard from John, and followed him;
42እርሱ አስቀድሞ የራሱን ወንድም ስምዖንን አገኘውና። መሢሕን አግኝተናል አለው፤ ትርጓሜውም ክርስቶስ ማለት ነው።
41this one doth first find his own brother Simon, and saith to him, `We have found the Messiah,` (which is, being interpreted, The Anointed,)
43ወደ ኢየሱስም አመጣው። ኢየሱስም ተመልክቶ። አንተ የዮና ልጅ ስምዖን ነህ፤ አንተ ኬፋ ትባላለህ አለው፤ ትርጓሜው ጴጥሮስ ማለት ነው።
42and he brought him unto Jesus: and having looked upon him, Jesus saith, `Thou art Simon, the son of Jonas, thou shalt be called Cephas,` (which is interpreted, A rock.)
44በነገው ኢየሱስ ወደ ገሊላ ሊወጣ ወደደ፥ ፊልጶስንም አገኘና። ተከተለኝ አለው።
43On the morrow, he willed to go forth to Galilee, and he findeth Philip, and saith to him, `Be following me.`
45ፊልጶስም ከእንድርያስና ከጴጥሮስ ከተማ ከቤተ ሳይዳ ነበረ።
44And Philip was from Bethsaida, of the city of Andrew and Peter;
46ፊልጶስ ናትናኤልን አግኝቶ። ሙሴ በሕግ ነቢያትም ስለ እርሱ የጻፉትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል አለው።
45Philip findeth Nathanael, and saith to him, `Him of whom Moses wrote in the Law, and the prophets, we have found, Jesus the son of Joseph, who [is] from Nazareth;`
47ናትናኤልም። ከናዝሬት መልካም ነገር ሊወጣ ይችላልን? አለው። ፊልጶስ። መጥተህ እይ አለው።
46and Nathanael said to him, `Out of Nazareth is any good thing able to be?` Philip said to him, `Come and see.`
48ኢየሱስ ናትናኤልን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ። ተንኰል የሌለበት በእውነት የእስራኤል ሰው እነሆ አለ።
47Jesus saw Nathanael coming unto him, and he saith concerning him, `Lo, truly an Israelite, in whom guile is not;`
49ናትናኤልም። ከወዴት ታውቀኛለህ? አለው። ኢየሱስም መልሶ። ፊልጶስ ሳይጠራህ፥ ከበለስ በታች ሳለህ፥ አየሁህ አለው።
48Nathanael saith to him, `Whence me dost thou know?` Jesus answered and said to him, `Before Philip`s calling thee — thou being under the fig-tree — I saw thee.`
50ናትናኤልም መልሶ። መምህር ሆይ፥ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ፤ አንተ የእስራኤል ንጉሥ ነህ አለው።
49Nathanael answered and saith to him, `Rabbi, thou art the Son of God, thou art the king of Israel.`
51ኢየሱስም መልሶ። ከበለስ በታች አየሁህ ስላልሁህ አመንህን? ከዚህ የሚበልጥ ነገር ታያለህ አለው።
50Jesus answered and said to him, `Because I said to thee, I saw thee under the fig-tree, thou dost believe; greater things than these thou shalt see;`
52እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይ ሲከፈት የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ አለው።
51and he saith to him, `Verily, verily, I say to you, henceforth ye shall see the heaven opened, and the messengers of God going up and coming down upon the Son of Man.`