Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

John

2

1And the third day a marriage happened in Cana of Galilee, and the mother of Jesus was there,
1በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤
2and also Jesus was called, and his disciples, to the marriage;
2ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ።
3and wine having failed, the mother of Jesus saith unto him, `Wine they have not;`
3የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት። የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው።
4Jesus saith to her, `What — to me and to thee, woman? not yet is mine hour come.`
4ኢየሱስም። አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት።
5His mother saith to the ministrants, `Whatever he may say to you — do.`
5እናቱም ለአገልጋዮቹ። የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው።
6And there were there six water-jugs of stone, placed according to the purifying of the Jews, holding each two or three measures.
6አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር።
7Jesus saith to them, `Fill the water-jugs with water;` and they filled them — unto the brim;
7ኢየሱስም። ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።
8and he saith to them, `Draw out, now, and bear to the director of the apartment;` and they bare.
8አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም።
9And as the director of the apartment tasted the water become wine, and knew not whence it is, (but the ministrants knew, who have drawn the water,) the director of the feast doth call the bridegroom,
9አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ።
10and saith to him, `Every man, at first, the good wine doth set forth; and when they may have drunk freely, then the inferior; thou didst keep the good wine till now.`
10ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል አለው።
11This beginning of the signs did Jesus in Cana of Galilee, and manifested his glory, and his disciples believed in him;
11ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።
12after this he went down to Capernaum, he, and his mother, and his brethren, and his disciples; and there they remained not many days.
12ከዚህ በኋላ ከእናቱና ከወንድሞቹ ከደቀ መዛሙርቱም ጋር ወደ ቅፍርናሆም ወረደ፥ በዚያም ጥቂት ቀን ኖሩ።
13And the passover of the Jews was nigh, and Jesus went up to Jerusalem,
13የአይሁድ ፋሲካም ቀርቦ ነበር፥ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ።
14and he found in the temple those selling oxen, and sheep, and doves, and the money-changers sitting,
14በመቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤
15and having made a whip of small cords, he put all forth out of the temple, also the sheep, and the oxen; and of the money-changers he poured out the coins, and the tables he overthrew,
15የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥
16and to those selling the doves he said, `Take these things hence; make not the house of my Father a house of merchandise.`
16ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።
17And his disciples remembered that it is written, `The zeal of Thy house did eat me up;`
17ደቀ መዛሙርቱም። የቤትህ ቅናት ይበላኛል ተብሎ እንደ ተጻፈ አሰቡ።
18the Jews then answered and said to him, `What sign dost thou shew to us — that thou dost these things?`
18ስለዚህ አይሁድ መልሰው። ይህን ስለምታደርግ ምን ምልክት ታሳየናለህ? አሉት።
19Jesus answered and said to them, `Destroy this sanctuary, and in three days I will raise it up.`
19ኢየሱስም መልሶ። ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው።
20The Jews, therefore, said, `Forty and six years was this sanctuary building, and wilt thou in three days raise it up?`
20ስለዚህ አይሁድ። ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥ አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን? አሉት።
21but he spake concerning the sanctuary of his body;
21እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር።
22when, then, he was raised out of the dead, his disciples remembered that he said this to them, and they believed the Writing, and the word that Jesus said.
22ስለዚህ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ይህን እንደ ተናገረ አሰቡና መጽሐፍንና ኢየሱስ የተናገረውን ቃል አመኑ።
23And as he was in Jerusalem, in the passover, in the feast, many believed in his name, beholding his signs that he was doing;
23በፋሲካ በዓልም በኢየሩሳሌም ሳለ፥ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ ብዙ ሰዎች በስሙ አመኑ፤
24and Jesus himself was not trusting himself to them, because of his knowing all [men],
24ነገር ግን ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ ያውቅ ነበር፤ ስለ ሰውም ማንም ሊመሰክር አያስፈልገውም ነበርና አይተማመናቸውም ነበር፤ ራሱ በሰው ያለውን ያውቅ ነበርና።
25and because he had no need that any should testify concerning man, for he himself was knowing what was in man.