Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

John

11

1And there was a certain one ailing, Lazarus, from Bethany, of the village of Mary and Martha her sister —
1ከማርያምና ከእኅትዋ ከማርታ መንደር ከቢታንያ የሆነ አልዓዛር የሚባል አንድ ሰው ታሞ ነበር።
2and it was Mary who did anoint the Lord with ointment, and did wipe his feet with her hair, whose brother Lazarus was ailing —
2ማርያምም ጌታን ሽቱ የቀባችው እግሩንም በጠጕርዋ ያበሰችው ነበረች፤ ወንድምዋም አልዓዛር ታሞ ነበር።
3therefore sent the sisters unto him, saying, `Sir, lo, he whom thou dost love is ailing;`
3ስለዚህ እኅቶቹ ጌታ ሆይ፥ እነሆ የምትወደው ታሞአል ብለው ወደ እርሱ ላኩ።
4and Jesus having heard, said, `This ailment is not unto death, but for the glory of God, that the Son of God may be glorified through it.`
4ኢየሱስም ሰምቶ። ይህ ህመም የእግዚአብሔር ልጅ በእርሱ ይከብር ዘንድ ስለ እግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት አይደለም አለ።
5And Jesus was loving Martha, and her sister, and Lazarus,
5ኢየሱስም ማርታንና እኅትዋን አልዓዛርንም ይወድ ነበር።
6when, therefore, he heard that he is ailing, then indeed he remained in the place in which he was two days,
6እንደ ታመመም በሰማ ጊዜ ያን ጊዜ በነበረበት ስፍራ ሁለት ቀን ዋለ፤
7then after this, he saith to the disciples, `We may go to Judea again;`
7ከዚህም በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ። ወደ ይሁዳ ደግሞ እንሂድ አላቸው።
8the disciples say to him, `Rabbi, now were the Jews seeking to stone thee, and again thou dost go thither!`
8ደቀ መዛሙርቱ። መምህር ሆይ፥ አይሁድ ከጥቂት ጊዜ በፊት ሊወግሩህ ይፈልጉ ነበር፥ ደግሞም ወደዚያ ትሄዳለህን? አሉት።
9Jesus answered, `Are there not twelve hours in the day? if any one may walk in the day, he doth not stumble, because the light of this world he doth see;
9ኢየሱስም መልሶ። ቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት አይደለምን? በቀን የሚመላለስ ቢኖር የዚህን ዓለም ብርሃን ያያልና አይሰናከልም፤
10and if any one may walk in the night, he stumbleth, because the light is not in him.`
10በሌሊት የሚመላለስ ቢኖር ግን ብርሃን በእርሱ ስለ ሌለ ይሰናከላል አላቸው።
11These things he said, and after this he saith to them, `Lazarus our friend hath fallen asleep, but I go on that I may awake him;`
11ይህን ተናገረ፤ ከዚህም በኋላ። ወዳጃችን አልዓዛር ተኝቶአል፤ ነገር ግን ከእንቅልፉ ላስነሣው እሄዳለሁ አላቸው።
12therefore said his disciples, `Sir, if he hath fallen asleep, he will be saved;`
12እንግዲህ ደቀ መዛሙርቱ። ጌታ ሆይ፥ ተኝቶስ እንደ ሆነ ይድናል አሉት።
13but Jesus had spoken about his death, but they thought that about the repose of sleep he speaketh.
13ኢየሱስስ ስለ ሞቱ ተናግሮ ነበር፤ እነርሱ ግን ስለ እንቅልፍ መተኛት እንደ ተናገረ መሰላቸው።
14Then, therefore, Jesus said to them freely, `Lazarus hath died;
14እንግዲህ ያን ጊዜ ኢየሱስ በግልጥ። አልዓዛር ሞተ፤
15and I rejoice, for your sake, (that ye may believe,) that I was not there; but we may go to him;`
15እንድታምኑም በዚያ ባለመኖሬ ስለ እናንተ ደስ ይለኛል፤ ነገር ግን ወደ እርሱ እንሂድ አላቸው።
16therefore said Thomas, who is called Didymus, to the fellow-disciples, `We may go — we also, that we may die with him,`
16ስለዚህ ዲዲሞስ የሚሉት ቶማስ ለባልንጀሮቹ ለደቀ መዛሙርት። ከእርሱ ጋር እንሞት ዘንድ እኛ ደግሞ እንሂድ አለ።
17Jesus, therefore, having come, found him having been four days already in the tomb.
17ኢየሱስም በመጣ ጊዜ በመቃብር እስከ አሁን አራት ቀን ሆኖት አገኘው።
18And Bethany was nigh to Jerusalem, about fifteen furlongs off,
18ቢታንያም አሥራ አምስት ምዕራፍ ያህል ለኢየሩሳሌም ቅርብ ነበረች።
19and many of the Jews had come unto Martha and Mary, that they might comfort them concerning their brother;
19ከአይሁድም ብዙዎች ስለ ወንድማቸው ሊያጽናኑአቸው ወደ ማርታና ወደ ማርያም መጥተው ነበር።
20Martha, therefore, when she heard that Jesus doth come, met him, and Mary kept sitting in the house.
20ማርታም ኢየሱስ እንደ መጣ በሰማች ጊዜ ልትቀበለው ወጣች፤ ማርያም ግን በቤት ተቀምጣ ነበር።
21Martha, therefore, said unto Jesus, `Sir, if thou hadst been here, my brother had not died;
21ማርታም ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ወንድሜ ባልሞተም ነበር፤
22but even now, I have known that whatever thou mayest ask of God, God will give to thee;`
22አሁንም ከእግዚአብሔር የምትለምነውን ሁሉ እግዚአብሔር እንዲሰጥህ አውቃለሁ አለችው።
23Jesus saith to her, `Thy brother shall rise again.`
23ኢየሱስም። ወንድምሽ ይነሣል አላት።
24Martha saith to him, `I have known that he will rise again, in the rising again in the last day;`
24ማርታም። በመጨረሻው ቀን በትንሣኤ እንዲነሣ አውቃለሁ አለችው።
25Jesus said to her, `I am the rising again, and the life; he who is believing in me, even if he may die, shall live;
25ኢየሱስም። ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤
26and every one who is living and believing in me shall not die — to the age;
26ሕያው የሆነም የሚያምንብኝም ሁሉ ለዘላለም አይሞትም፤ ይህን ታምኚያለሽን? አላት።
27believest thou this?` she saith to him, `Yes, sir, I have believed that thou art the Christ, the Son of God, who is coming to the world.`
27እርስዋም። አዎን ጌታ ሆይ፤ አንተ ወደ ዓለም የሚመጣው ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ እኔ አምናለሁ አለችው።
28And these things having said, she went away, and called Mary her sister privately, saying, `The Teacher is present, and doth call thee;`
28ይህንም ብላ ሄደች እኅትዋንም ማርያምን በስውር ጠርታ። መምህሩ መጥቶአል ይጠራሽማል አለቻት።
29she, when she heard, riseth up quickly, and doth come to him;
29እርስዋም በሰማች ጊዜ ፈጥና ተነሣች ወደ እርሱም መጣች፤
30and Jesus had not yet come to the village, but was in the place where Martha met him;
30ኢየሱስም ማርታ በተቀበለችበት ስፍራ ነበረ እንጂ ገና ወደ መንደሩ አልገባም ነበር።
31the Jews, therefore, who were with her in the house, and were comforting her, having seen Mary that she rose up quickly and went forth, followed her, saying — `She doth go away to the tomb, that she may weep there.`
31ሲያጽናኑአት ከእርስዋ ጋር በቤት የነበሩ አይሁድም ማርያም ፈጥና እንደ ተነሣችና እንደ ወጣች ባዩ ጊዜ፥ ወደ መቃብር ሄዳ በዚያ ልታለቅስ መስሎአቸው ተከተሉአት።
32Mary, therefore, when she came where Jesus was, having seen him, fell at his feet, saying to him, `Sir, if thou hadst been here, my brother had not died;`
32ማርያምም ኢየሱስ ወዳለበት መጥታ ባየችው ጊዜ በእግሩ ላይ ወድቃ። ጌታ ሆይ፥ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ወንድሜ ባልሞተም ነበር አለችው።
33Jesus, therefore, when he saw her weeping, and the Jews who came with her weeping, did groan in the spirit, and troubled himself, and he said,
33ኢየሱስም እርስዋ ስታለቅስ ከእርስዋም ጋር የመጡት አይሁድ ሲያለቅሱ አይቶ በመንፈሱ አዘነ በራሱም ታወከ፤
34`Where have ye laid him?` they say to him, `Sir, come and see;`
34ወዴት አኖራችሁት? አለም። እነርሱም። ጌታ ሆይ፥ መጥተህ እይ አሉት።
35Jesus wept.
35ኢየሱስም እንባውን አፈሰሰ።
36The Jews, therefore, said, `Lo, how he was loving him!`
36ስለዚህ አይሁድ። እንዴት ይወደው እንደ ነበረ እዩ አሉ።
37and certain of them said, `Was not this one, who did open the eyes of the blind man, able to cause that also this one might not have died?`
37ከእነርሱ ግን አንዳንዶቹ። ይህ የዕውሩን ዓይኖች የከፈተ ይህን ደግሞ እንዳይሞት ያደርግ ዘንድ ባልቻለም ነበርን? አሉ።
38Jesus, therefore, again groaning in himself, cometh to the tomb, and it was a cave, and a stone was lying upon it,
38ኢየሱስም በራሱ አዝኖ ወደ መቃብሩ መጣ፤ እርሱም ዋሻ ነበረ፤ ድንጋይም ተገጥሞበት ነበር።
39Jesus saith, `Take ye away the stone;` the sister of him who hath died — Martha — saith to him, `Sir, already he stinketh, for he is four days dead;`
39ኢየሱስ። ድንጋዩን አንሡ አለ። የሞተውም እኅት ማርታ። ጌታ ሆይ፥ ከሞተ አራት ቀን ሆኖታልና አሁን ይሸታል አለችው።
40Jesus saith to her, `Said I not to thee, that if thou mayest believe, thou shalt see the glory of God?`
40ኢየሱስ። ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርሁሽምን? አላት።
41They took away, therefore, the stone where the dead was laid, and Jesus lifted his eyes upwards, and said, `Father, I thank Thee, that Thou didst hear me;
41ድንጋዩንም አነሡት። ኢየሱስም ዓይኖቹን ወደ ላይ አንሥቶ። አባት ሆይ፥ ስለ ሰማኸኝ አመሰግንሃለሁ።
42and I knew that Thou always dost hear me, but, because of the multitude that is standing by, I said [it], that they may believe that Thou didst send me.`
42ሁልጊዜም እንድትሰማኝ አወቅሁ፤ ነገር ግን አንተ እንደ ላክኸኝ ያምኑ ዘንድ በዚህ ዙሪያ ስለ ቆሙት ሕዝብ ተናገርሁ አለ።
43And these things saying, with a loud voice he cried out, `Lazarus, come forth;`
43ይህንም ብሎ በታላቅ ድምፅ። አልዓዛር ሆይ፥ ወደ ውጭ ና ብሎ ጮኸ።
44and he who died came forth, being bound feet and hands with grave-clothes, and his visage with a napkin was bound about; Jesus saith to them, `Loose him, and suffer to go.`
44የሞተውም እጆቹና እግሮቹ በመግነዝ እንደ ተገነዙ ወጣ፤ ፈቱም በጨርቅ እንደ ተጠመጠመ ነበር። ኢየሱስም። ፍቱትና ይሂድ ተዉት አላቸው።
45Many, therefore, of the Jews who came unto Mary, and beheld what Jesus did, believed in him;
45ስለዚህ ወደ ማርያም ከመጡት፥ ኢየሱስም ያደረገውን ካዩት ከአይሁድ ብዙዎች በእርሱ አመኑ፤
46but certain of them went away unto the Pharisees, and told them what Jesus did;
46ከእነርሱ አንዳንዶቹ ግን ወደ ፈሪሳውያን ሄደው ኢየሱስ ያደረገውን ነገሩአቸው።
47the chief priests, therefore, and the Pharisees, gathered together a sanhedrim, and said, `What may we do? because this man doth many signs?
47እንግዲህ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ሸንጎ ሰብስበው። ምን እናድርግ? ይህ ሰው ብዙ ምልክቶች ያደርጋልና።
48if we may let him alone thus, all will believe in him; and the Romans will come, and will take away both our place and nation.`
48እንዲሁ ብንተወው ሁሉ በእርሱ ያምናሉ፤ የሮሜም ሰዎች መጥተው አገራችንን ወገናችንንም ይወስዳሉ አሉ።
49and a certain one of them, Caiaphas, being chief priest of that year, said to them, `Ye have not known anything,
49በዚያችም ዓመት ሊቀ ካህናት የነበረ ቀያፋ የሚሉት ከእነርሱ አንዱ። እናንተ ምንም አታውቁም፤
50nor reason that it is good for us that one man may die for the people, and not the whole nation perish.`
50ሕዝቡም ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡም አላቸው።
51And this he said not of himself, but being chief priest of that year, he did prophesy that Jesus was about to die for the nation,
51ይህንም የተናገረ ከራሱ አይደለም፥ ነገር ግን በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ነበረና ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው ትንቢት ተናገረ፤
52and not for the nation only, but that also the children of God, who have been scattered abroad, he may gather together into one.
52ስለ ሕዝቡም ሁሉ አይደለም፥ ነገር ግን የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች ደግሞ በአንድነት እንዲሰበስባቸው ነው እንጂ።
53From that day, therefore, they took counsel together that they may kill him;
53እንግዲህ ከዚያ ቀን ጀምረው ሊገድሉት ተማከሩ።
54Jesus, therefore, was no more freely walking among the Jews, but went away thence to the region nigh the wilderness, to a city called Ephraim, and there he tarried with his disciples.
54ከዚያ ወዲያም ኢየሱስ በአይሁድ መካከል ተገልጦ አልተመላለሰም፤ ነገር ግን ከዚያ በምድረ በዳ አጠገብ ወዳለች ምድር፥ ኤፍሬም ወደምትባል ከተማ ሄደ፤ በዚያም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጠ።
55And the passover of the Jews was nigh, and many went up to Jerusalem out of the country before the passover, that they might purify themselves;
55የአይሁድም ፋሲካ ቀርቦ ነበር። ብዙ ሰዎችም ራሳቸውን ያነጹ ዘንድ ከፋሲካ በፊት ከአገሩ ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ።
56they were seeking, therefore, Jesus, and said one with another, standing in the temple, `What doth appear to you — that he may not come to the feast?`
56ኢየሱስንም ይፈልጉት ነበር፤ በመቅደስም ቆመው እርስ በርሳቸው። ምን ይመስላችኋል? ወደ በዓሉ አይመጣም ይሆንን? ተባባሉ።
57and both the chief priests and the Pharisees had given a command, that if any one may know where he is, he may shew [it], so that they may seize him.
57የካህናት አለቆችም ፈሪሳውያንም ይይዙት ዘንድ እርሱ ያለበትን ስፍራ የሚያውቀው ሰው ቢኖር እንዲያመለክታቸው አዘው ነበር።