1`Verily, verily, I say to you, He who is not entering through the door to the fold of the sheep, but is going up from another side, that one is a thief and a robber;
1እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤
2and he who is entering through the door is shepherd of the sheep;
2በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው።
3to this one the doorkeeper doth open, and the sheep hear his voice, and his own sheep he doth call by name, and doth lead them forth;
3ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል።
4and when his own sheep he may put forth, before them he goeth on, and the sheep follow him, because they have known his voice;
4የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤
5and a stranger they will not follow, but will flee from him, because they have not known the voice of strangers.`
5ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና።
6This similitude spake Jesus to them, and they knew not what the things were that he was speaking to them;
6ኢየሱስ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ እነርሱ ግን የነገራቸው ምን እንደ ሆነ አላስተዋሉም።
7Jesus said therefore again to them, `Verily, verily, I say to you — I am the door of the sheep;
7ኢየሱስም ደግሞ አላቸው። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እኔ የበጎች በር ነኝ።
8all, as many as came before me, are thieves and robbers, but the sheep did not hear them;
8ከእኔ በፊት የመጡ ሁሉ ሌቦችና ወንበዴዎች ናቸው፤ ዳሩ ግን በጎቹ አልሰሙአቸውም።
9I am the door, through me if any one may come in, he shall be saved, and he shall come in, and go out, and find pasture.
9በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማሪያም ያገኛል።
10`The thief doth not come, except that he may steal, and kill, and destroy; I came that they may have life, and may have [it] abundantly.
10ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።
11`I am the good shepherd; the good shepherd his life layeth down for the sheep;
11መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።
12and the hireling, and not being a shepherd, whose own the sheep are not, doth behold the wolf coming, and doth leave the sheep, and doth flee; and the wolf catcheth them, and scattereth the sheep;
12እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል በጎቹንም ይበትናቸዋል።
13and the hireling doth flee because he is an hireling, and is not caring for the sheep.
13ሞያተኛ ስለ ሆነ ለበጎቹም ስለማይገደው ሞያተኛው ይሸሻል።
14`I am the good shepherd, and I know my [sheep], and am known by mine,
14መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች ያውቁኛል፤ ነፍሴንም ስለ በጎች አኖራለሁ።
15according as the Father doth know me, and I know the Father, and my life I lay down for the sheep,
16ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።
16and other sheep I have that are not of this fold, these also it behoveth me to bring, and my voice they will hear, and there shall become one flock — one shepherd.
17ነፍሴን ደግሞ አነሣት ዘንድ አኖራለሁና ስለዚህ አብ ይወደኛል።
17`Because of this doth the Father love me, because I lay down my life, that again I may take it;
18እኔ በፈቃዴ አኖራታለሁ እንጂ ከእኔ ማንም አይወስዳትም። ላኖራት ሥልጣን አለኝ ደግሞም ላነሣት ሥልጣን አለኝ ይህችን ትእዛዝ ከአባቴ ተቀበልሁ።
18no one doth take it from me, but I lay it down of myself; authority I have to lay it down, and authority I have again to take it; this command I received from my Father.`
19እንግዲህ ከዚህ ቃል የተነሣ በአይሁድ መካከል እንደ ገና መለያየት ሆነ።
19Therefore, again, there came a division among the Jews, because of these words,
20ከእነርሱም ብዙዎች። ጋኔን አለበት አብዶአልም፤ ስለ ምንስ ትሰሙታላችሁ? አሉ።
20and many of them said, `He hath a demon, and is mad, why do ye hear him?`
21ሌሎችም። ይህ ጋኔን ያለበት ሰው ቃል አይደለም፤ ጋኔን የዕውሮችን ዓይኖች ሊከፍት ይችላልን? አሉ።
21others said, `These sayings are not those of a demoniac; is a demon able blind men`s eyes to open?`
22በኢየሩሳሌምም የመቅደስ መታደስ በዓል ሆነ፤
22And the dedication in Jerusalem came, and it was winter,
23ክረምትም ነበረ። ኢየሱስም በመቅደስ በሰሎሞን ደጅ መመላለሻ ይመላለስ ነበር።
23and Jesus was walking in the temple, in the porch of Solomon,
24አይሁድም እርሱን ከበው። እስከ መቼ ድረስ በጥርጣሪ ታቆየናለህ? አንተ ክርስቶስ እንደ ሆንህ ገልጠህ ንገረን አሉት።
24the Jews, therefore, came round about him, and said to him, `Till when our soul dost thou hold in suspense? if thou art the Christ, tell us freely.`
25ኢየሱስም መለሰላቸው፥ እንዲህ ሲል። ነገርኋችሁ አታምኑምም እኔ በአባቴ ስም የማደርገው ሥራ ይህ ስለ እኔ ይመሰክራል፤
25Jesus answered them, `I told you, and ye do not believe; the works that I do in the name of my Father, these testify concerning me;
26እናንተ ግን እንደ ነገርኋችሁ ከበጎቼ ስላልሆናችሁ አታምኑም።
26but ye do not believe, for ye are not of my sheep,
27በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ ይከተሉኝማል፤
27according as I said to you: My sheep my voice do hear, and I know them, and they follow me,
28እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።
28and life age-during I give to them, and they shall not perish — to the age, and no one shall pluck them out of my hand;
29የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ ከአባቴም እጅ ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም።
29my Father, who hath given to me, is greater than all, and no one is able to pluck out of the hand of my Father;
30እኔና አብ አንድ ነን።
30I and the Father are one.`
31አይሁድ ሊወግሩት ደግመው ድንጋይ አነሡ።
31Therefore, again, did the Jews take up stones that they may stone him;
32ኢየሱስ። ከአባቴ ብዙ መልካም ሥራ አሳየኋችሁ፤ ከእነርሱ ስለ ማናቸው ሥራ ትወግሩኛላችሁ? ብሎ መለሰላቸው።
32Jesus answered them, `Many good works did I shew you from my Father; because of which work of them do ye stone me?`
33አይሁድም። ስለ መልካም ሥራ አንወግርህም፤ ስለ ስድብ፤ አንተም ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለ ማድረግህ ነው እንጂ ብለው መለሱለት።
33The Jews answered him, saying, `For a good work we do not stone thee, but for evil speaking, and because thou, being a man, dost make thyself God.`
34ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው። እኔ። አማልክት ናችሁ አልሁ ተብሎ በሕጋችሁ የተጻፈ አይደለምን?
34Jesus answered them, `Is it not having been written in your law: I said, ye are gods?
35መጽሐፉ ሊሻር አይቻልምና እነዚያን የእግዚአብሔር ቃል የመጣላቸውን አማልክት ካላቸው፥
35if them he did call gods unto whom the word of God came, (and the Writing is not able to be broken,)
36የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ስላልሁ እናንተ አብ የቀደሰውን ወደ ዓለምም የላከውን። ትሳደባለህ ትሉታላችሁን?
36of him whom the Father did sanctify, and send to the world, do ye say — Thou speakest evil, because I said, Son of God I am?
37እኔ የአባቴን ሥራ ባላደርግ አትመኑኝ፤
37if I do not the works of my Father, do not believe me;
38ባደርገው ግን፥ እኔን ስንኳ ባታምኑ አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ።
38and if I do, even if me ye may not believe, the works believe, that ye may know and may believe that in me [is] the Father, and I in Him.`
39እንግዲህ ደግመው ሊይዙት ፈለጉ፤ ከእጃቸውም ወጣ።
39Therefore were they seeking again to seize him, and he went forth out of their hand,
40ዮሐንስም በመጀመሪያ ያጠምቅበት ወደ ነበረው ስፍራ ወደ ዮርዳኖስ ማዶ እንደ ገና ሄደ በዚያም ኖረ።
40and went away again to the other side of the Jordan, to the place where John was at first baptizing, and remained there,
41ብዙ ሰዎችም ወደ እርሱ መጥተው። ዮሐንስ አንድ ምልክት ስንኳ አላደረገም፥ ነገር ግን ዮሐንስ ስለዚህ ሰው የተናገረው ሁሉ እውነት ነበረ አሉ።
41and many came unto him, and said — `John, indeed, did no sign, and all things, as many as John said about this one were true;`
42በዚያም ብዙዎች በእርሱ አመኑ።
42and many did believe in him there.