1And passing by, he saw a man blind from birth,
1ሲያልፍም ከመወለዱ ጀምሮ ዕውር የሆነውን ሰው አየ።
2and his disciples asked him, saying, `Rabbi, who did sin, this one or his parents, that he should be born blind?`
2ደቀ መዛሙርቱም። መምህር ሆይ፥ ይህ ሰው ዕውር ሆኖ እንዲወለድ ኃጢአት የሠራ ማን ነው? እርሱ ወይስ ወላጆቹ? ብለው ጠየቁት።
3Jesus answered, `Neither did this one sin nor his parents, but that the works of God may be manifested in him;
3ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰ። የእግዚአብሔር ሥራ በእርሱ እንዲገለጥ ነው እንጂ እርሱ ወይም ወላጆቹ ኃጢአት አልሠሩም።
4it behoveth me to be working the works of Him who sent me while it is day; night doth come, when no one is able to work: —
4ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች።
5when I am in the world, I am a light of the world.`
5በዓለም ሳለሁ የዓለም ብርሃን ነኝ።
6These things saying, he spat on the ground, and made clay of the spittle, and rubbed the clay on the eyes of the blind man, and said to him,
6ይህን ብሎ ወደ መሬት እንትፍ አለ በምራቁም ጭቃ አድርጎ በጭቃው የዕውሩን ዓይኖች ቀባና።
7`Go away, wash at the pool of Siloam,` which is, interpreted, Sent. He went away, therefore, and did wash, and came seeing;
7ሂድና በሰሊሆም መጠመቂያ ታጠብ አለው፤ ትርጓሜው የተላከ ነው። ስለዚህ ሄዶ ታጠበ እያየም መጣ።
8the neighbours, therefore, and those seeing him before, that he was blind, said, `Is not this he who is sitting and begging?`
8ጐረቤቶቹም ቀድሞም ሲለምን አይተውት የነበሩ። ይህ ተቀምጦ ይለምን የነበረ አይደለምን? አሉ።
9others said — `This is he;` and others — `He is like to him;` he himself said, — `I am [he].`
9ሌሎች። እርሱ ነው አሉ፤ ሌሎች። አይደለም እርሱን ይመስላል እንጂ አሉ፤ እርሱ። እኔ ነኝ አለ።
10They said, therefore, to him, `How were thine eyes opened?`
10ታድያ። ዓይኖችህ እንዴት ተከፈቱ? አሉት።
11he answered and said, `A man called Jesus made clay, and rubbed my eyes, and said to me, Go away to the pool of Siloam, and wash; and having gone away and having washed, I received sight;`
11እርሱ መልሶ። ኢየሱስ የሚባለው ሰው ጭቃ አድርጎ አይኖቼን ቀባና። ወደ ሰሊሆም መጠመቂያ ሄደህ ታጠብ አለኝ፤ ሄጄ ታጥቤም አየሁ አለ።
12they said, therefore, to him, `Where is that one?` he saith, `I have not known.`
12ያ ሰው ወዴት ነው? አሉት። አላውቅም አለ።
13They bring him to the Pharisees who once [was] blind,
13በፊት ዕውር የነበረውን ሰው ወደ ፈሪሳውያን ወሰዱት።
14and it was a sabbath when Jesus made the clay, and opened his eyes.
14ኢየሱስም ጭቃ አድርጎ ዓይኖቹን የከፈተበት ቀን ሰንበት ነበረ።
15Again, therefore, the Pharisees also were asking him how he received sight, and he said to them, `Clay he did put upon my eyes, and I did wash — and I see.`
15ስለዚህ ፈሪሳውያን ደግሞ እንዴት እንዳየ እንደ ገና ጠየቁት። እርሱም። ጭቃ በዓይኖቼ አኖረ ታጠብሁም አያለሁም አላቸው።
16Of the Pharisees, therefore, certain said, `This man is not from God, because the sabbath he doth not keep;` others said, `How is a man — a sinful one — able to do such signs?` and there was a division among them.
16ከፈሪሳውያንም አንዳንዶቹ። ይህ ሰው ሰንበትን አያከብርምና ከእግዚአብሔር አይደለም አሉ። ሌሎች ግን። ኃጢአትኛ ሰው እንደነዚህ ያሉ ምልክቶች ሊያደርግ እንዴት ይችላል? አሉ።
17They said to the blind man again, `Thou — what dost thou say of him — that he opened thine eyes?`
17በመካከላቸውም መለያየት ሆነ። ከዚህም የተነሣ ዕውሩን። አንተ ዓይኖችህን ስለ ከፈተ ስለ እርሱ ምን ትላለህ? ደግሞ አሉት። እርሱም። ነቢይ ነው አለ።
18and he said — `He is a prophet.` The Jews, therefore, did not believe concerning him that he was blind and did receive sight, till that they called the parents of him who received sight,
18አይሁድ የዚያን ያየውን ወላጆች እስኪጠሩ ድረስ ዕውር እንደ ነበረ እንዳየም ስለ እርሱ አላመኑም፥
19and they asked them, saying, `Is your son, of whom ye say that he was born blind? how then now doth he see?`
19እነርሱንም። እናንተ ዕውር ሆኖ ተወለደ የምትሉት ልጃችሁ ይህ ነውን? ታድያ አሁን እንዴት ያያል? ብለው ጠየቁአቸው።
20His parents answered them and said, `We have known that this is our son, and that he was born blind;
20ወላጆቹም መልሰው። ይህ ልጃችን እንደ ሆነ ዕውርም ሆኖ እንደ ተወለደ አናውቃለን፤
21and how he now seeth, we have not known; or who opened his eyes, we have not known; himself is of age, ask him; he himself shall speak concerning himself.`
21ዳሩ ግን አሁን እንዴት እንዳየ አናውቅም፥ ወይም ዓይኖቹን ማን እንደ ከፈተ እኛ አናውቅም፤ ጠይቁት እርሱ ሙሉ ሰው ነው፤ እርሱ ስለ ራሱ ይናገራል አሉ።
22These things said his parents, because they were afraid of the Jews, for already had the Jews agreed together, that if any one may confess him — Christ, he may be put out of the synagogue;
22ወላጆቹ አይሁድን ስለ ፈሩ ይህን አሉ፤ እርሱ ክርስቶስ ነው ብሎ የሚመሰክር ቢኖር ከምኵራብ እንዲያወጡት አይሁድ ከዚህ በፊት ተስማምተው ነበርና።
23because of this his parents said — `He is of age, ask him.`
23ስለዚህ ወላጆቹ። ሙሉ ሰው ነው፥ ጠይቁት አሉ።
24They called, therefore, a second time the man who was blind, and they said to him, `Give glory to God, we have known that this man is a sinner;`
24ስለዚህ ዕውር የነበረውን ሰው ሁለተኛ ጠርተው። እግዚአብሔርን አክብር፤ ይህ ሰው ኃጢአተኛ መሆኑን እኛ እናውቃለን አሉት።
25he answered, therefore, and said, `If he be a sinner — I have not known, one thing I have known, that, being blind, now I see.`
25እርሱም መልሶ። ኃጢአተኛ መሆኑን አላውቅም፤ ዕውር እንደ ነበርሁ አሁንም እንዳይ ይህን አንድ ነገር አውቃለሁ አለ።
26And they said to him again, `What did he to thee? how did he open thine eyes?`
26ደግመውም። ምን አደረገልህ? እንዴትስ ዓይኖችህን ከፈተ? አሉት።
27He answered them, `I told you already, and ye did not hear; why again do ye wish to hear? do ye also wish to become his disciples?`
27እርሱም መልሶ። አስቀድሜ ነገርኋችሁ አልሰማችሁምም፤ ስለ ምን ዳግመኛ ልትሰሙ ትወዳላችሁ? እናንተ ደግሞ ደቀ መዛሙርቱ ልትሆኑ ትወዳላችሁን? አላቸው።
28They reviled him, therefore, and said, `Thou art his disciple, and we are Moses` disciples;
28ተሳድበውም። አንተ የእርሱ ደቀ መዝሙር ነህ፥ እኛ ግን የሙሴ ደቀ መዛሙርት ነን፤
29we have known that God hath spoken to Moses, but this one — we have not known whence he is.`
29እግዚአብሔር ሙሴን እንደ ተናገረው እኛ እናውቃለን፥ ይህ ሰው ግን ከወዴት እንደ ሆነ አናውቅም አሉት።
30The man answered and said to them, `Why, in this is a wonderful thing, that ye have not known whence he is, and he opened my eyes!
30ሰውዬው መለሰ እንዲህም አላቸው። ከወዴት እንደ ሆነ እናንተ አለማወቃችሁ ይህ ድንቅ ነገር ነው፥ ዳሩ ግን ዓይኖቼን ከፈተ።
31and we have known that God doth not hear sinners, but, if any one may be a worshipper of God, and may do His will, him He doth hear;
31እግዚአብሔርን የሚፈራ ፈቃዱንም የሚያደርግ ቢኖር ያንን እግዚአብሔር ይሰማዋል እንጂ ኃጢአተኞችን እንዳይሰማ እናውቃለን።
32from the age it was not heard, that any one did open eyes of one who hath been born blind;
32ዕውር ሆኖ የተወለደውን ዓይኖች ማንም እንደ ከፈተ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ አልተሰማም፤
33if this one were not from God, he were not able to do anything.`
33ይህ ሰው ከእግዚአብሔር ባይሆን ምንም ሊያደርግ ባልቻለም ነበር።
34They answered and said to him, `In sins thou wast born altogether, and thou dost teach us!` and they cast him forth without.
34መልሰው። አንተ ሁለንተናህ በኃጢአት ተወለድህ፥ አንተም እኛን ታስተምረናለህን? አሉት። ወደ ውጭም አወጡት።
35Jesus heard that they cast him forth without, and having found him, he said to him, `Dost thou believe in the Son of God?`
35ኢየሱስም ወደ ውጭ እንዳወጡት ሰማ ሲያገኘውም። አንተ በእግዚአብሔር ልጅ ታምናለህን? አለው።
36he answered and said, `Who is he, sir, that I may believe in him?`
36እርሱም መልሶ። ጌታ ሆይ፥ በእርሱ አምን ዘንድ ማን ነው? አለ።
37And Jesus said to him, `Thou hast both seen him, and he who is speaking with thee is he;`
37ኢየሱስም። አይተኸዋልም ከአንተ ጋርም የሚናገረው እርሱ ነው አለው።
38and he said, `I believe, sir,` and bowed before him.
38እርሱም። ጌታ ሆይ፥ አምናለሁ አለ፤ ሰገደለትም።
39And Jesus said, `For judgment I to this world did come, that those not seeing may see, and those seeing may become blind.`
39ኢየሱስም። የማያዩ እንዲያዩ የሚያዩም እንዲታወሩ እኔ ወደዚህ ዓለም ለፍርድ መጣሁ አለ።
40And those of the Pharisees who were with him heard these things, and they said to him, `Are we also blind?`
40ከፈሪሳውያንም ከእርሱ ጋር የነበሩት ይህን ሰምተው። እኛ ደግሞ ዕውሮች ነንን? አሉት።
41Jesus said to them, `If ye were blind, ye were not having had sin, but now ye say — We see, therefore doth your sin remain.
41ኢየሱስም አላቸው። ዕውሮችስ ብትሆኑ ኃጢአት ባልሆነባችሁም ነበር፤ አሁን ግን። እናያለን ትላላችሁ፤ ኃጢአታችሁ ይኖራል።