Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

John

8

1And at dawn he came again to the temple,
1ኢየሱስ ግን ወደ ደብረ ዘይት ሄደ።
2and all the people were coming unto him, and having sat down, he was teaching them;
2ማለዳም ደግሞ ወደ መቅደስ ደረሰ ሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ መጡ። ተቀምጦም ያስተምራቸው ነበር።
3and the scribes and the Pharisees bring unto him a woman having been taken in adultery, and having set her in the midst,
3ጻፎችና ፈሪሳውያንም በምንዝር የተያዘችን ሴት ወደ እርሱ አመጡ በመካከልም እርሱዋን አቁመው።
4they say to him, `Teacher, this woman was taken in the very crime — committing adultery,
4መምህር ሆይ፥ ይህች ሴት ስታመነዝር ተገኝታ ተያዘች።
5and in the law, Moses did command us that such be stoned; thou, therefore, what dost thou say?`
5ሙሴም እንደነዚህ ያሉት እንዲወገሩ በሕግ አዘዘን፤ አንተስ ስለ እርስዋ ምን ትላለህ? አሉት።
6and this they said, trying him, that they might have to accuse him. And Jesus, having stooped down, with the finger he was writing on the ground,
6የሚከሱበትንም እንዲያገኙ ሊፈትኑት ይህን አሉ። ኢየሱስ ግን ጐንበስ ብሎ በጣቱ በምድር ላይ ጻፈ፤
7and when they continued asking him, having bent himself back, he said unto them, `The sinless of you — let him first cast the stone at her;`
7መላልሰው በጠየቁት ጊዜ ግን ቀና ብሎ። ከእናንተ ኃጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት አላቸው።
8and again having stooped down, he was writing on the ground,
8ደግሞም ጐንበስ ብሎ በጣቱ በምድር ላይ ጻፈ።
9and they having heard, and by the conscience being convicted, were going forth one by one, having begun from the elders — unto the last; and Jesus was left alone, and the woman standing in the midst.
9እነርሱም ይህን ሲሰሙ ሕሊናቸው ወቀሳቸውና ከሽማግሌዎች ጀምረው እስከ ኋለኞች አንድ አንድ እያሉ ወጡ፤ ኢየሱስም ብቻውን ቀረ ሴቲቱም በመካከል ቆማ ነበረች።
10And Jesus having bent himself back, and having seen no one but the woman, said to her, `Woman, where are those — thine accusers? did no one pass sentence upon thee?`
10ኢየሱስም ቀና ብሎ ከሴቲቱ በቀር ማንንም ባላየ ጊዜ። አንቺ ሴት፥ እነዚያ ከሳሾችሽ ወዴት አሉ? የፈረደብሽ የለምን? አላት።
11and she said, `No one, Sir;` and Jesus said to her, `Neither do I pass sentence on thee; be going on, and no more sin.`
11እርስዋም። ጌታ ሆይ፥ አንድ ስንኳ አለች። ኢየሱስም። እኔም አልፈርድብሽም፤ ሂጂ ከአሁንም ጀምሮ ደግመሽ ኃጢአት አትሥሪ አላት።
12Again, therefore, Jesus spake to them, saying, `I am the light of the world; he who is following me shall not walk in the darkness, but he shall have the light of the life.`
12ደግሞም ኢየሱስ። እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው።
13The Pharisees, therefore, said to him, `Thou of thyself dost testify, thy testimony is not true;`
13ፈሪሳውያንም። አንተ ስለ ራስህ ትመሰክራለህ፤ ምስክርነትህ እውነት አይደለም አሉት።
14Jesus answered and said to them, `And if I testify of myself — my testimony is true, because I have known whence I came, and whither I go, and ye — ye have not known whence I come, or whither I go.
14ኢየሱስ መለሰ አላቸውም። እኔ ስለ ራሴ ምንም እንኳ ብመሰክር ከወዴት እንደመጣሁ ወዴትም እንድሄድ አውቃለሁና ምስክርነቴ እውነት ነው፤ እናንተ ግን ከወዴት እንደ መጣሁ ወዴትም እንድሄድ አታውቁም።
15`Ye according to the flesh do judge; I do not judge any one,
15እናንተ ሥጋዊ ፍርድን ትፈርዳላችሁ፤ እኔ በአንድ ሰው ስንኳ አልፈርድም።
16and even if I do judge my judgment is true, because I am not alone, but I and the Father who sent me;
16የላከኝ አብ ከእኔ ጋር ነው እንጂ ብቻዬን አይደለሁምና እኔ ብፈርድ ፍርዴ እውነት ነው።
17and also in your law it hath been written, that the testimony of two men are true;
17የሁለት ሰዎችም ምስክርነት እውነት እንደ ሆነ በሕጋችሁ ተጽፎአል።
18I am [one] who is testifying of myself, and the Father who sent me doth testify of me.`
18ስለ ራሴ የምመሰክር እኔ ነኝ፥ የላከኝም አብ ስለ እኔ ይመሰክራል።
19They said, therefore, to him, `Where is thy father?` Jesus answered, `Ye have neither known me nor my Father: if me ye had known, my Father also ye had known.`
19እንግዲህ። አባትህ ወዴት ነው? አሉት። ኢየሱስ መልሶ። እኔንም ወይም አባቴንም አታውቁም፤ እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር አላቸው።
20These sayings spake Jesus in the treasury, teaching in the temple, and no one seized him, because his hour had not yet come;
20ኢየሱስ በመቅደስ ሲያስተምር በግምጃ ቤት አጠገብ ይህን ነገር ተናገረ፤ ጊዜው ገና አልደረሰምና ማንም አልያዘውም።
21therefore said Jesus again to them, `I go away, and ye will seek me, and in your sin ye shall die; whither I go away, ye are not able to come.`
21ኢየሱስም ደግሞ። እኔ እሄዳለሁ ትፈልጉኛላችሁም በኃጢአታችሁም ትሞታላችሁ እኔ ወደምሄድበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም አላቸው።
22The Jews, therefore, said, `Will he kill himself, because he saith, Whither I go away, ye are not able to come?`
22አይሁድም። እኔ ወደ ምሄድበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም ማለቱ ራሱን ይገድላልን? እንጃ አሉ።
23and he said to them, `Ye are from beneath, I am from above; ye are of this world, I am not of this world;
23እናንተ ከታች ናችሁ፥ እኔ ከላይ ነኝ፤ እናንተ ከዚህ ዓለም ናችሁ፥ እኔ ከዚህ ዓለም አይደለሁም።
24I said, therefore, to you, that ye shall die in your sins, for if ye may not believe that I am [he], ye shall die in your sins.`
24እንግዲህ። በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ አልኋችሁ፤ እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁና አላቸው።
25They said, therefore, to him, `Thou — who art thou?` and Jesus said to them, `Even what I did speak of to you at the beginning;
25እንግዲህ። አንተ ማን ነህ? አሉት። ኢየሱስም። ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ።
26many things I have to speak concerning you and to judge, but He who sent me is true, and I — what things I heard from Him — these I say to the world.`
26ስለ እናንተ የምናገረው የምፈርደውም ብዙ ነገር አለኝ፤ ዳሩ ግን የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም ከእርሱ የሰማሁትን ይህን ለዓለም እናገራለሁ አላቸው።
27They knew not that of the Father he spake to them;
27ስለ አብ እንደ ነገራቸው አላስተዋሉም።
28Jesus, therefore, said to them, `When ye may lift up the Son of Man then ye will know that I am [he]; and of myself I do nothing, but according as my Father did teach me, these things I speak;
28ስለዚህም ኢየሱስ። የሰውን ልጅ ከፍ ከፍ ባደረጋችሁት ጊዜ እኔ እሆን ዘንድ አባቴም እንዳስተማረኝ እነዚህን እናገር ዘንድ እንጂ ከራሴ አንዳች እንዳላደርግ በዚያን ጊዜ ታውቃላችሁ።
29and He who sent me is with me; the Father did not leave me alone, because I, the things pleasing to Him, do always.`
29የላከኝም ከእኔ ጋር ነው፤ እኔ ደስ የሚያሰኘውን ዘወትር አደርጋለሁና አብ ብቻዬን አይተወኝም አላቸው።
30As he is speaking these things, many believed in him;
30ይህን ሲናገር ብዙዎች በእርሱ አመኑ።
31Jesus, therefore, said unto the Jews who believed in him, `If ye may remain in my word, truly my disciples ye are, and ye shall know the truth,
31ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ። እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤
32and the truth shall make you free.`
32እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው።
33They answered him, `Seed of Abraham we are; and to no one have we been servants at any time; how dost thou say — Ye shall become free?`
33እነርሱም መልሰው። የአብርሃም ዘር ነን ለአንድም ስንኳ ከቶ ባሪያዎች አልሆንም፤ አንተ። አርነት ትወጣላችሁ እንዴት ትላለህ? አሉት።
34Jesus answered them, `Verily, verily, I say to you — Every one who is committing sin, is a servant of the sin,
34ኢየሱስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ኃጢአት የሚያደርግ ሁሉ የኃጢአት ባርያ ነው።
35and the servant doth not remain in the house — to the age, the son doth remain — to the age;
35ባርያም ለዘላለም በቤት አይኖርም፤ ልጁ ለዘላለም ይኖራል።
36if then the son may make you free, in reality ye shall be free.
36እንግዲህ ልጁ አርነት ቢያወጣችሁ በእውነት አርነት ትወጣላችሁ።
37`I have known that ye are seed of Abraham, but ye seek to kill me, because my word hath no place in you;
37የአብርሃም ዘር መሆናችሁንስ አውቃለሁ ነገር ግን ቃሌ በእናንተ አይኖርምና ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ።
38I — that which I have seen with my Father do speak, and ye, therefore, that which ye have seen with your father — ye do.`
38እኔ በአባቴ ዘንድ ያየሁትን እናገራለሁ፤ እናንተም ደግሞ በአባታችሁ ዘንድ ያያችሁትን ታደርጋላችሁ።
39They answered and said to him, `Our father is Abraham;` Jesus saith to them, `If children of Abraham ye were, the works of Abraham ye were doing;
39መልሰውም። አባታችንስ አብርሃም ነው አሉት። ኢየሱስም። የአብሃም ልጆች ብትሆኑ የአብርሃምን ሥራ ባደረጋችሁ ነበር።
40and now, ye seek to kill me — a man who hath spoken to you the truth I heard from God; this Abraham did not;
40ነገር ግን አሁን ከእግዚእብሔር የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ፤ አብርሃም እንዲህ አላደረገም።
41ye do the works of your father.` They said, therefore, to him, `We of whoredom have not been born; one Father we have — God;`
41እናንተ የአባታችሁን ሥራ ታደርጋላችሁ አላቸው። እኛስ ከዝሙት አልተወለድንም አንድ አባት አለን እርሱም እግዚአብሔር ነው አሉት።
42Jesus then said to them, `If God were your father, ye were loving me, for I came forth from God, and am come; for neither have I come of myself, but He sent me;
42ኢየሱስም አላቸው። እግዚአብሔርስ አባታችሁ ከሆነ በወደዳችሁኝ ነበር፤ እኔ ከእግዚአብሔር ወጥቼ መጥቻለሁና፤ እርሱ ላከኝ እንጂ ከራሴ አልመጣሁምና።
43wherefore do ye not know my speech? because ye are not able to hear my word.
43ንግግሬን የማታስተውሉ ስለ ምንድር ነው? ቃሌን ልትሰሙ ስለማትችሉ ነው።
44`Ye are of a father — the devil, and the desires of your father ye will to do; he was a man-slayer from the beginning, and in the truth he hath not stood, because there is no truth in him; when one may speak the falsehood, of his own he speaketh, because he is a liar — also his father.
44እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና።
45`And because I say the truth, ye do not believe me.
45እኔ ግን እውነትን የምናገር ስለ ሆንሁ አታምኑኝም።
46Who of you doth convict me of sin? and if I speak truth, wherefore do ye not believe me?
46ከእናንተ ስለ ኃጢአት የሚወቅሰኝ ማን ነው? እውነት የምናገር ከሆንሁ እናንተ ስለ ምን አታምኑኝም?
47he who is of God, the sayings of God he doth hear; because of this ye do not hear, because of God ye are not.`
47ከእግዚአብሔር የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ይሰማል፤ እናንተ ከእግዚአብሔር አይደላችሁምና ስለዚህ አትሰሙም።
48The Jews, therefore, answered and said to him, `Do we not say well, that thou art a Samaritan, and hast a demon?`
48አይሁድ መልሰው። ሳምራዊ እንደ ሆንህ ጋኔንም እንዳለብህ በማለታችን እኛ መልካም እንል የለምን? አሉት።
49Jesus answered, `I have not a demon, but I honour my Father, and ye dishonour me;
49ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል። እኔስ ጋኔን የለብኝም ነገር ግን አባቴን አከብራለሁ እናንተም ታዋርዱኛላችሁ።
50and I do not seek my own glory; there is who is seeking and is judging;
50እኔ ግን የራሴን ክብር አልፈልግም፤ የሚፈልግ የሚፈርድም አለ።
51verily, verily, I say to you, If any one may keep my word, death he may not see — to the age.`
51እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም።
52The Jews, therefore, said to him, `Now we have known that thou hast a demon; Abraham did die, and the prophets, and thou dost say, If any one may keep my word, he shall not taste of death — to the age!
52አይሁድ። ጋኔን እንዳለብህ አሁን አወቅን። አብርሃም ስንኳ ሞተ ነቢያትም፤ አንተም። ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አይቀምስም ትላለህ።
53Art thou greater than our father Abraham, who died? and the prophets died; whom dost thou make thyself?`
53በእውኑ አንተ ከሞተው ከአባታችን ከአብርሃም ትበልጣለህን? ነቢያትም ሞቱ፤ ራስህን ማንን ታደርጋለህ? አሉት።
54Jesus answered, `If I glorify myself, my glory is nothing; it is my Father who is glorifying me, of whom ye say that He is your God;
54ኢየሱስም መለሰ አለም። እኔ ራሴን ባከብር ክብሬ ከንቱ ነው፤ የሚያከብረኝ እናንተ አምላካችን የምትሉት አባቴ ነው፤
55and ye have not known Him, and I have known Him, and if I say that I have not known Him, I shall be like you — speaking falsely; but I have known Him, and His word I keep;
55አላወቃችሁትምም፥ እኔ ግን አውቀዋለሁ። አላውቀውም ብል እንደ እናንተ ሐሰተኛ በሆንሁ፤ ዳሩ ግን አውቀዋለሁ ቃሉንም እጠብቃለሁ።
56Abraham, your father, was glad that he might see my day; and he saw, and did rejoice.`
56አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፥ አየም ደስም አለው።
57The Jews, therefore, said unto him, `Thou art not yet fifty years old, and Abraham hast thou seen?`
57አይሁድም። ገና አምሳ ዓመት ያልሆነህ አብርሃምን አይተሃልን? አሉት።
58Jesus said to them, `Verily, verily, I say to you, Before Abraham`s coming — I am;`
58ኢየሱስም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ አላቸው።
59they took up, therefore, stones that they may cast at him, but Jesus hid himself, and went forth out of the temple, going through the midst of them, and so passed by.
59ስለዚህ ሊወግሩት ድንጋይ አነሡ፤ ኢየሱስ ግን ተሰወራቸው ከመቅደስም ወጥቶ በመካከላቸው አልፎ ሄደ።