1After these things there was a feast of the Jews, and Jesus went up to Jerusalem,
1ከዚህ በኋላ የአይሁድ በዓል ነበረ፥ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ።
2and there is in Jerusalem by the sheep-[gate] a pool that is called in Hebrew Bethesda, having five porches,
2በኢየሩሳሌምም በበጎች በር አጠገብ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ የምትባል አንዲት መጠመቂያ ነበረች፤ አምስትም መመላለሻ ነበረባት።
3in these were lying a great multitude of the ailing, blind, lame, withered, waiting for the moving of the water,
3በእነዚህ ውስጥ የውኃውን መንቀሳቀስ እየጠበቁ በሽተኞችና ዕውሮች አንካሶችም ሰውነታቸውም የሰለለ ብዙ ሕዝብ ይተኙ ነበር።
4for a messenger at a set time was going down in the pool, and was troubling the water, the first then having gone in after the troubling of the water, became whole of whatever sickness he was held.
4አንዳንድ ጊዜ የጌታ መልአክ ወደ መጠመቂያይቱ ወርዶ ውኃውን ያናውጥ ነበርና፤ እንግዲህ ከውኃው መናወጥ በኋላ በመጀመሪያ የገባ ከማናቸው ካለበት ደዌ ጤናማ ይሆን ነበር።
5and there was a certain man there being in ailment thirty and eight years,
5በዚያም ከሠላሳ ስምንት ዓመት ጀምሮ የታመመ አንድ ሰው ነበረ፤
6him Jesus having seen lying, and having known that he is already a long time, he saith to him, `Dost thou wish to become whole?`
6ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥ እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ። ልትድን ትወዳለህን? አለው።
7The ailing man answered him, `Sir, I have no man, that, when the water may be troubled, he may put me into the pool, and while I am coming, another doth go down before me.`
7ድውዩም። ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ መለሰለት።
8Jesus saith to him, `Rise, take up thy couch, and be walking;`
8ኢየሱስ። ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው።
9and immediately the man became whole, and he took up his couch, and was walking, and it was a sabbath on that day,
9ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ።
10the Jews then said to him that hath been healed, `It is a sabbath; it is not lawful to thee to take up the couch.`
10ያም ቀን ሰንበት ነበረ። ስለዚህ አይሁድ የተፈወሰውን ሰው። ሰንበት ነው አልጋህንም ልትሸከም አልተፈቀደልህም አሉት።
11He answered them, `He who made me whole — that one said to me, Take up thy couch, and be walking;`
11እርሱ ግን። ያዳነኝ ያ ሰው። አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለኝ ብሎ መለሰላቸው።
12they questioned him, then, `Who is the man who is saying to thee, Take up thy couch and be walking?`
12እነርሱም። አልጋህን ተሸክመህ ሂድ ያለህ ሰው ማን ነው? ብለው ጠየቁት።
13But he that was healed had not known who he is, for Jesus did move away, a multitude being in the place.
13ዳሩ ግን በዚያ ስፍራ ሕዝብ ሰለ ነበሩ ኢየሱስ ፈቀቅ ብሎ ነበርና የተፈወሰው ሰው ማን እንደ ሆነ አላወቀም።
14After these things, Jesus findeth him in the temple, and said to him, `Lo, thou hast become whole; sin no more, lest something worse may happen to thee.`
14ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና። እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ አለው።
15The man went away, and told the Jews that it is Jesus who made him whole,
15ሰውዬው ሄዶ ያዳነው ኢየሱስ እንደ ሆነ ለአይሁድ ነገረ።
16and because of this were the Jews persecuting Jesus, and seeking to kill him, because these things he was doing on a sabbath.
16ስለዚህም በሰንበት ይህን ስላደረገ አይሁድ ኢየሱስን ያሳድዱት ነበር ሊገድሉትም ይፈልጉ ነበር።
17And Jesus answered them, `My Father till now doth work, and I work;`
17ኢየሱስ ግን። አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል እኔም ደግሞ እሠራለሁ ብሎ መለሰላቸው።
18because of this, then, were the Jews seeking the more to kill him, because not only was he breaking the sabbath, but he also called God his own Father, making himself equal to God.
18እንግዲህ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ደግሞ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ። እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ፥ ስለዚህ አይሁድ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር።
19Jesus therefore responded and said to them, `Verily, verily, I say to you, The Son is not able to do anything of himself, if he may not see the Father doing anything; for whatever things He may do, these also the Son in like manner doth;
19ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብ ሲያደርግ ያየውን ነው እንጂ ወልድ ከራሱ ሊያደርግ ምንም አይችልም፤ ያ የሚያደርገውን ሁሉ ወልድ ደግሞ ይህን እንዲሁ ያደርጋልና።
20for the Father doth love the Son, and doth shew to him all things that He himself doth; and greater works than these He will shew him, that ye may wonder.
20አብ ወልድን ይወዳልና፥ የሚያደርገውንም ሁሉ ያሳየዋል፤ እናንተም ትደነቁ ዘንድ ከዚህ የሚበልጥ ሥራ ያሳየዋል።
21`For, as the Father doth raise the dead, and doth make alive, so also the Son doth make alive whom he willeth;
21አብ ሙታንን እንደሚያነሣ ሕይወትም እንደሚሰጣቸው፥ እንዲሁ ወልድ ደግሞ ለሚወዳቸው ሕይወትን ይሰጣቸዋል።
22for neither doth the Father judge any one, but all the judgment He hath given to the Son,
22ሰዎች ሁሉ አብን እንደሚያከብሩት ወልድን ያከብሩት ዘንድ፥ ፍርድን ሁሉ ለወልድ ሰጠው እንጂ አብ በአንድ ሰው ስንኳ አይፈርድም። ወልድን የማያከብር የላከውን አብን አያከብርም።
23that all may honour the Son according as they honour the Father; he who is not honouring the Son, doth not honour the Father who sent him.
24እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።
24`Verily, verily, I say to you — He who is hearing my word, and is believing Him who sent me, hath life age-during, and to judgment he doth not come, but hath passed out of the death to the life.
25እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሙታን የእግዚአብሔርን ልጅ ድምፅ የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል እርሱም አሁን ነው፤ የሚሰሙትም በሕይወት ይኖራሉ።
25`Verily, verily, I say to you — There cometh an hour, and it now is, when the dead shall hear the voice of the Son of God, and those having heard shall live;
26አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው እንዲሁ ደግሞ ለወልድ በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታልና።
26for, as the Father hath life in himself, so He gave also to the Son to have life in himself,
27የሰው ልጅም ስለ ሆነ ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን ሰጠው።
27and authority He gave him also to do judgment, because he is Son of Man.
28በመቃብር ያሉቱ ሁሉ ድምፁን የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል፤ መልካምም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይወጣሉና በዚህ አታድንቁ።
28`Wonder not at this, because there doth come an hour in which all those in the tombs shall hear his voice,
30እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና።
29and they shall come forth; those who did the good things to a rising again of life, and those who practised the evil things to a rising again of judgment.
31እኔ ስለ እኔ ስለ ራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት አይደለም፤
30`I am not able of myself to do anything; according as I hear I judge, and my judgment is righteous, because I seek not my own will, but the will of the Father who sent me.
32ስለ እኔ የሚመሰክር ሌላ ነው፥ እርሱም ስለ እኔ የሚመሰክረው ምስክር እውነት እንደ ሆነ አውቃለሁ።
31`If I testify concerning myself, my testimony is not true;
33እናንተ ወደ ዮሐንስ ልካችኋል እርሱም ለእውነት መስክሮአል።
32another there is who is testifying concerning me, and I have known that the testimony that he doth testify concerning me is true;
34እኔ ግን ከሰው ምስክር አልቀበልም፥ እናንተ እንድትድኑ ይህን እላለሁ እንጂ።
33ye have sent unto John, and he hath testified to the truth.
35እርሱ የሚነድና የሚያበራ መብራት ነበረ፥ እናንተም ጥቂት ዘመን በብርሃኑ ደስ ሊላችሁ ወደዳችሁ።
34`But I do not receive testimony from man, but these things I say that ye may be saved;
36እኔ ግን ከዮሐንስ ምስክር የሚበልጥ ምስክር አለኝ፤ አብ ልፈጽመው የሰጠኝ ሥራ፥ ይህ የማደርገው ሥራ፥ አብ እንደ ላከኝ ስለ እኔ ይመሰክራልና።
35he was the burning and shining lamp, and ye did will to be glad, for an hour, in his light.
37የላከኝ አብም እርሱ ስለ እኔ መስክሮአል። ድምፁን ከቶ አልሰማችሁም፥ መልኩንም አላያችሁም፤
36`But I have the testimony greater than John`s, for the works that the Father gave me, that I might finish them, the works themselves that I do, they testify concerning me, that the Father hath sent me.
38እርሱም የላከውን እናንተ አታምኑምና በእናንተ ዘንድ የሚኖር ቃሉ የላችሁም።
37`And the Father who sent me Himself hath testified concerning me; ye have neither heard His voice at any time, nor His appearance have ye seen;
39እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤
38and His word ye have not remaining in you, because whom He sent, him ye do not believe.
40ነገር ግን ሕይወት እንዲሆንላችሁ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም።
39`Ye search the Writings, because ye think in them to have life age-during, and these are they that are testifying concerning me;
41ከሰው ክብርን አልቀበልም፤ ዳሩ ግን የእግዚአብሔር ፍቅር በራሳችሁ እንደ ሌላችሁ አውቃችኋለሁ።
40and ye do not will to come unto me, that ye may have life;
43እኔ በአባቴ ስም መጥቻለሁ አልተቀበላችሁኝምም፤ ሌላው በራሱ ስም ቢመጣ እርሱን ትቀበሉታላችሁ።
41glory from man I do not receive,
44እናንተ እርስ በርሳችሁ ክብር የምትቀባበሉ ከአንዱም ከእግዚአብሔር ያለውን ክብር የማትፈልጉ፥ እንዴት ልታምኑ ትችላላችሁ?
42but I have known you, that the love of God ye have not in yourselves.
45እኔ በአብ ዘንድ የምከሳችሁ አይምሰላችሁ፤ የሚከሳችሁ አለ፤ እርሱም ተስፋ የምታደርጉት ሙሴ ነው።
43`I have come in the name of my Father, and ye do not receive me; if another may come in his own name, him ye will receive;
46ሙሴንስ ብታምኑት እኔን ባመናችሁ ነበር፤ እርሱ ስለ እኔ ጽፎአልና።
44how are ye able — ye — to believe, glory from one another receiving, and the glory that [is] from God alone ye seek not?
47መጻሕፍትን ካላመናችሁ ግን ቃሌን እንዴት ታምናላችሁ?
45`Do not think that I will accuse you unto the Father; there is who is accusing you, Moses — in whom ye have hoped;
46for if ye were believing Moses, ye would have been believing me, for he wrote concerning me;
47but if his writings ye believe not, how shall ye believe my sayings?`