Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

John

6

1After these things Jesus went away beyond the sea of Galilee (of Tiberias),
1ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ ተሻገረ፤ እርሱም የጥብርያዶስ ባሕር ነው።
2and there was following him a great multitude, because they were seeing his signs that he was doing on the ailing;
2በበሽተኞችም ያደረገውን ምልክቶች ስላዩ ብዙ ሕዝብ ተከተሉት።
3and Jesus went up to the mount, and he was there sitting with his disciples,
3ኢየሱስም ወደ ተራራ ወጣና በዚያ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጠ።
4and the passover was nigh, the feast of the Jews.
4የአይሁድ በዓልም ፋሲካ ቀርቦ ነበር።
5Jesus then having lifted up [his] eyes and having seen that a great multitude doth come to him, saith unto Philip, `Whence shall we buy loaves, that these may eat?` —
5ኢየሱስም ዓይኖቹን አንሥቶ ብዙ ሕዝብ ወደ እርሱ ሲመጣ አየና ፊልጶስን። እነዚህ እንዲበሉ እንጀራ ከወዴት እንገዛለን? አለው።
6and this he said, trying him, for he himself had known what he was about to do.
6ራሱ ሊያደርግ ያለውን ያውቅ ነበርና ሊፈትነው ይህን ተናገረ።
7Philip answered him, `Two hundred denaries` worth of loaves are not sufficient to them, that each of them may receive some little;`
7ፊልጶስ። እያንዳንዳቸው ትንሽ ትንሽ እንኳ እንዲቀበሉ የሁለት መቶ ዲናር እንጀራ አይበቃቸውም ብሎ መለሰለት።
8one of his disciples — Andrew, the brother of Simon Peter — saith to him,
8ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የስምዖን ጴጥሮስ ወንድም እንድርያስ።
9`There is one little lad here who hath five barley loaves, and two fishes, but these — what are they to so many?`
9አምስት የገብስ እንጀራና ሁለት ዓሣ የያዘ ብላቴና በዚህ አለ፤ ነገር ግን እነዚህን ለሚያህሉ ሰዎች ይህ ምን ይሆናል? አለው።
10And Jesus said, `Make the men to sit down;` and there was much grass in the place, the men then sat down, in number, as it were, five thousand,
10ኢየሱስም። ሰዎቹን እንዲቀመጡ አድርጉ አለ። በዚያም ስፍራ ብዙ ሣር ነበረበት። ወንዶችም ተቀመጡ ቍጥራቸውም አምስት ሺህ የሚያህል ነበር።
11and Jesus took the loaves, and having given thanks he distributed to the disciples, and the disciples to those reclining, in like manner, also of the little fishes as much as they wished.
11ኢየሱስም እንጀራውን ያዘ፥ አመስግኖም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለተቀመጡት ሰዎች ሰጡአቸው እንዲሁም ከዓሣው በፈለጉት መጠን።
12And when they were filled, he saith to his disciples, `Gather together the broken pieces that are over, that nothing may be lost;`
12ከጠገቡም በኋላ ደቀ መዛሙርቱን። አንድ ስንኳ እንዳይጠፋ የተረፈውን ቍርስራሽ አከማቹ አላቸው።
13they gathered together, therefore, and filled twelve hand-baskets with broken pieces, from the five barley loaves that were over to those having eaten.
13ሰለዚህ አከማቹ፥ ከበሉትም ከአምስቱ የገብስ እንጀራ የተረፈውን ቍርስራሽ አሥራ ሁለት መሶብ ሞሉ።
14The men, then, having seen the sign that Jesus did, said — `This is truly the Prophet, who is coming to the world;`
14ከዚህ የተነሣ ሰዎቹ ኢየሱስ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ። ይህ በእውነት ወደ ዓለም የሚመጣው ነቢይ ነው አሉ።
15Jesus, therefore, having known that they are about to come, and to take him by force that they may make him king, retired again to the mountain himself alone.
15በዚህም ምክንያት ኢየሱስ ያነግሡት ዘንድ ሊመጡና ሊነጥቁት እንዳላቸው አውቆ ደግሞ ወደ ተራራ ብቻውን ፈቀቅ አለ።
16And when evening came, his disciples went down to the sea,
16በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ ባሕር ወረዱ፥
17and having entered into the boat, they were going over the sea to Capernaum, and darkness had already come, and Jesus had not come unto them,
17በታንኳም ገብተው በባሕር ማዶ ወደ ቅፍርናሆም ይመጡ ነበር። አሁንም ጨልሞ ነበር፤ ኢየሱስም ገና ወደ እነርሱ አልመጣም ነበር፤
18the sea also — a great wind blowing — was being raised,
18ብርቱ ነፋስም ስለ ነፈሰ ባሕሩ ተናወጠ።
19having pushed onwards, therefore, about twenty-five or thirty furlongs, they behold Jesus walking on the sea, and coming nigh to the boat, and they were afraid;
19ሀያ አምስት ወይም ሠላሳ ምዕራፍ ከቀዘፉ በኋላም፥ ኢየሱስ በባሕር ላይ እየሄደ ወደ ታንኳይቱ ሲቀርብ አይተው ፈሩ።
20and he saith to them, `I am [he], be not afraid;`
20እርሱ ግን። እኔ ነኝ፤ አትፍሩ አላቸው።
21they were willing then to receive him into the boat, and immediately the boat came unto the land to which they were going.
21ስለዚህ በታንኳይቱ ሊቀበሉት ወደዱ፤ ወዲያውም ታንኳይቱ ወደሚሄዱበት ምድር ደረሰች።
22On the morrow, the multitude that was standing on the other side of the sea, having seen that there was no other little boat there except one — that into which his disciples entered — and that Jesus went not in with his disciples into the little boat, but his disciples went away alone,
22በነገው በባሕር ማዶ ቆመው የነበሩ ሕዝቡ ከአንዲት ጀልባ በቀር በዚያ ሌላ ጀልባ እንዳልነበረች፥ ደቀ መዛሙርቱም ለብቻቸው እንደ ሄዱ እንጂ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ታንኳይቱ እንዳልገባ አዩ፤
23(and other little boats came from Tiberias, nigh the place where they did eat the bread, the Lord having given thanks),
23ዳሩ ግን ሌሎች ጀልባዎች ጌታ የባረከውን እንጀራ ወደ በሉበት ስፍራ አጠገብ ከጥብርያዶስ መጡ።
24when therefore the multitude saw that Jesus is not there, nor his disciples, they also themselves did enter into the boats, and came to Capernaum seeking Jesus;
24ሕዝቡም ኢየሱስ ወይም ደቀ መዛሙርቱ በዚያ እንዳልነበሩ ባዩ ጊዜ፥ ራሳቸው በጀልባዎቹ ገብተው ኢየሱስን እየፈለጉ ወደ ቅፍርናሆም መጡ።
25and having found him on the other side of the sea, they said to him, `Rabbi, when hast thou come hither?`
25በባሕር ማዶም ሲያገኙት። መምህር ሆይ፥ ወደዚህ መቼ መጣህ? አሉት።
26Jesus answered them and said, `Verily, verily, I say to you, Ye seek me, not because ye saw signs, but because ye did eat of the loaves, and were satisfied;
26ኢየሱስም መልሶ። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የምትፈልጉኝ እንጀራን ስለ በላችሁና ስለ ጠገባችሁ ነው እንጂ ምልክቶችን ስላያችሁ አይደለም።
27work not for the food that is perishing, but for the food that is remaining to life age-during, which the Son of Man will give to you, for him did the Father seal — [even] God.`
27ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፤ እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና።
28They said therefore unto him, `What may we do that we may work the works of God?`
28እንግዲህ። የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ምን እናድርግ? አሉት።
29Jesus answered and said to them, `This is the work of God, that ye may believe in him whom He did send.`
29ኢየሱስ መልሶ። ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው አላቸው።
30They said therefore to him, `What sign, then, dost thou, that we may see and may believe thee? what dost thou work?
30እንግዲህ። እንኪያ አይተን እንድናምንህ አንተ ምን ምልክት ታደርጋለህ? ምንስ ትሠራለህ?
31our fathers the manna did eat in the wilderness, according as it is having been written, Bread out of the heaven He gave them to eat.`
31ይበሉ ዘንድ ከሰማይ እንጀራ ሰጣቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ አባቶቻችን በምድረ በዳ መና በሉ አሉት።
32Jesus, therefore, said to them, `Verily, verily, I say to you, Moses did not give you the bread out of the heaven; but my Father doth give you the true bread out of the heaven;
32ኢየሱስም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እውነተኛ እንጀራ ከሰማይ የሚሰጣችሁ አባቴ ነው እንጂ ከሰማይ እንጀራ የሰጣችሁ ሙሴ አይደለም፤
33for the bread of God is that which is coming down out of the heaven, and giving life to the world.`
33የእግዚአብሔር እንጀራ ከሰማይ የሚወርድ ለዓለምም ሕይወትን የሚሰጥ ነውና አላቸው።
34They said, therefore, unto him, `Sir, always give us this bread.`
34ስለዚህ። ጌታ ሆይ፥ ይህን እንጀራ ዘወትር ስጠን አሉት።
35And Jesus said to them, `I am the bread of the life; he who is coming unto me may not hunger, and he who is believing in me may not thirst — at any time;
35ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም።
36but I said to you, that ye also have seen me, and ye believe not;
36ነገር ግን አይታችሁኝ እንዳላመናችሁ አልኋችሁ።
37all that the Father doth give to me will come unto me; and him who is coming unto me, I may in no wise cast without,
37አብ የሚሰጠኝ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፥ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም፤
38because I have come down out of the heaven, not that I may do my will, but the will of Him who sent me.
38ፈቃዴን ለማድረግ አይደለም እንጂ የላከኝን ፈቃድ ለማድረግ ከሰማይ ወርጃለሁና።
39`And this is the will of the Father who sent me, that all that He hath given to me I may not lose of it, but may raise it up in the last day;
39ከሰጠኝም ሁሉ አንድን ስንኳ እንዳላጠፋ በመጨረሻው ቀን እንዳስነሣው እንጂ የላከኝ የአብ ፈቃድ ይህ ነው።
40and this is the will of Him who sent me, that every one who is beholding the Son, and is believing in him, may have life age-during, and I will raise him up in the last day.`
40ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
41The Jews, therefore, were murmuring at him, because he said, `I am the bread that came down out of the heaven;`
41እንግዲህ አይሁድ። ከሰማይ የወረደ እንጀራ እኔ ነኝ ስላለ ስለ እርሱ አንጐራጐሩና።
42and they said, `Is not this Jesus, the son of Joseph, whose father and mother we have known? how then saith this one — Out of the heaven I have come down?`
42አባቱንና እናቱን የምናውቃቸው ይህ የዮሴፍ ልጅ ኢየሱስ አይደለምን? እንግዲህ። ከሰማይ ወርጃለሁ እንዴት ይላል? አሉ።
43Jesus answered, therefore, and said to them, `Murmur not one with another;
43ኢየሱስ መለሰ አላቸውም። እርስ በርሳችሁ አታንጐራጕሩ።
44no one is able to come unto me, if the Father who sent me may not draw him, and I will raise him up in the last day;
44የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
45it is having been written in the prophets, And they shall be all taught of God; every one therefore who heard from the Father, and learned, cometh to me;
45ሁሉም ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ ተብሎ በነቢያት ተጽፎአል፤ እንግዲህ ከአብ የሰማ የተማረም ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል።
46not that any one hath seen the Father, except he who is from God, he hath seen the Father.
46አብን ያየ ማንም የለም፤ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር፥ እርሱ አብን አይቶአል።
47`Verily, verily, I say to you, He who is believing in me, hath life age-during;
47እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው።
48I am the bread of the life;
48የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ።
49your fathers did eat the manna in the wilderness, and they died;
49አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱም፤
50this is the bread that out of the heaven is coming down, that any one may eat of it, and not die.
50ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው።
51`I am the living bread that came down out of the heaven; if any one may eat of this bread he shall live — to the age; and the bread also that I will give is my flesh, that I will give for the life of the world.`
51ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው።
52The Jews, therefore, were striving with one another, saying, `How is this one able to give us [his] flesh to eat?`
52እንግዲህ አይሁድ። ይህ ሰው ሥጋውን ልንበላ ይሰጠን ዘንድ እንዴት ይችላል? ብለው እርስ በርሳቸው ተከራከሩ።
53Jesus, therefore, said to them, `Verily, verily, I say to you, If ye may not eat the flesh of the Son of Man, and may not drink his blood, ye have no life in yourselves;
53ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም።
54he who is eating my flesh, and is drinking my blood, hath life age-during, and I will raise him up in the last day;
54ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
55for my flesh truly is food, and my blood truly is drink;
55ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና።
56he who is eating my flesh, and is drinking my blood, doth remain in me, and I in him.
56ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።
57`According as the living Father sent me, and I live because of the Father, he also who is eating me, even that one shall live because of me;
57ሕያው አብ እንደ ላከኝ እኔም ከአብ የተነሣ ሕያው እንደምሆን፥ እንዲሁ የሚበላኝ ደግሞ ከእኔ የተነሣ ሕያው ይሆናል።
58this is the bread that came down out of the heaven; not as your fathers did eat the manna, and died; he who is eating this bread shall live — to the age.`
58ከሰማይ የወረደ እንጀራ ይህ ነው፤ አባቶቻችሁ መና በልተው እንደ ሞቱ አይደለም፤ ይህን እንጀራ የሚበላ ለዘላለም ይኖራል
59These things he said in a synagogue, teaching in Capernaum;
59በቅፍርናሆም ሲያስተምር ይህን በምኵራብ አለ።
60many, therefore, of his disciples having heard, said, `This word is hard; who is able to hear it?`
60ከደቀ መዛሙርቱም ብዙዎች በሰሙ ጊዜ። ይህ የሚያስጨንቅ ንግግር ነው፤ ማን ሊሰማው ይችላል? አሉ።
61And Jesus having known in himself that his disciples are murmuring about this, said to them, `Doth this stumble you?
61ኢየሱስ ግን ደቀ መዛሙርቱ ስለዚህ እንዳንጐራጐሩ በልቡ አውቆ አላቸው። ይህ ያሰናክላችኋልን?
62if then ye may behold the Son of Man going up where he was before?
62እንግዲህ የሰው ልጅ አስቀድሞ ወደ ነበረበት ሲወጣ ብታዩ እንዴት ይሆናል?
63the spirit it is that is giving life; the flesh doth not profit anything; the sayings that I speak to you are spirit, and they are life;
63ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው፤ ሥጋ ምንም አይጠቅምም፤ እኔ የነገርኋችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወትም ነው።
64but there are certain of you who do not believe;` for Jesus had known from the beginning who they are who are not believing, and who is he who will deliver him up,
64ነገር ግን ከእናንተ የማያምኑ አሉ። ኢየሱስ የማያምኑት እነማን እንደ ሆኑ አሳልፎ የሚሰጠውም ማን እንደ ሆነ ከመጀመሪያ ያውቅ ነበርና።
65and he said, `Because of this I have said to you — No one is able to come unto me, if it may not have been given him from my Father.`
65ደግሞ። ስለዚህ አልኋችሁ፥ ከአብ የተሰጠው ካልሆነ ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም አለ።
66From this [time] many of his disciples went away backward, and were no more walking with him,
66ከዚህም የተነሣ ከደቀ መዛሙርቱ ብዙዎች ወደ ኋላ ተመለሱ፤ ወደ ፊትም ከእርሱ ጋር አልሄዱም።
67Jesus, therefore, said to the twelve, `Do ye also wish to go away?`
67ኢየሱስም ለአሥራ ሁለቱ። እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁን? አለ።
68Simon Peter, therefore, answered him, `Sir, unto whom shall we go? thou hast sayings of life age-during;
68ስምዖን ጴጥሮስ። ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤
69and we have believed, and we have known, that thou art the Christ, the Son of the living God.`
69እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ አምነናል አውቀናልም ብሎ መለሰለት።
70Jesus answered them, `Did not I choose you — the twelve? and of you — one is a devil.
70ኢየሱስም። እኔ እናንተን አሥራ ሁለታችሁን የመረጥኋችሁ አይደለምን? ከእናንተም አንዱ ዲያብሎስ ነው ብሎ መለሰላቸው።
71And he spake of Judas, Simon`s [son], Iscariot, for he was about to deliver him up, being one of the twelve.
71ስለ ስምዖንም ልጅ ስለ አስቆሮቱ ይሁዳ ተናገረ፤ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ የሆነ እርሱ አሳልፎ ይሰጠው ዘንድ አለውና።