Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Mark

2

1And again he entered into Capernaum, after [some] days, and it was heard that he is in the house,
1ከጥቂት ቀን በኋላ ወደ ቅፍርናሆም ደግሞ ገብቶ በቤት እንደ ሆነ ተሰማ።
2and immediately many were gathered together, so that there was no more room, not even at the door, and he was speaking to them the word.
2በደጅ ያለው ስፍራም እስኪጠባቸው ድረስ ብዙ ሰዎች ተሰበሰቡ፤ ቃሉንም ይነግራቸው ነበር።
3And they come unto him, bringing a paralytic, borne by four,
3አራት ሰዎችም የተሸከሙትን ሽባ አመጡለት።
4and not being able to come near to him because of the multitude, they uncovered the roof where he was, and, having broken [it] up, they let down the couch on which the paralytic was lying,
4ስለ ሕዝቡም ብዛት ወደ እርሱ ማቅረብ ቢያቅታቸው እርሱ ያለበትን የቤቱን ጣራ አነሡ፥ ነድለውም ሽባው የተኛበትን አልጋ አወረዱ።
5and Jesus having seen their faith, saith to the paralytic, `Child, thy sins have been forgiven thee.`
5ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን። አንተ ልጅ፥ ኃጢአትህ ተሰረየችልህ አለው።
6And there were certain of the scribes there sitting, and reasoning in their hearts,
6ከጻፎችም አንዳንዶቹ በዚያ ተቀምጠው ነበር በልባቸውም። ይህ ሰው ስለ ምን እንደዚህ ያለ ስድብ ይናገራል?
7`Why doth this one thus speak evil words? who is able to forgive sins except one — God?`
7ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ኃጢአት ሊያስተሰርይ ማን ይችላል? ብለው አሰቡ።
8And immediately Jesus, having known in his spirit that they thus reason in themselves, said to them, `Why these things reason ye in your hearts?
8ወዲያውም ኢየሱስ በልባቸው እንዲህ እንዳሰቡ በመንፈስ አውቆ እንዲህ አላቸው። በልባችሁ ይህን ስለ ምን ታስባላችሁ?
9which is easier, to say to the paralytic, The sins have been forgiven to thee? or to say, Rise, and take up thy couch, and walk?
9ሽባውን። ኃጢአትህ ተሰረየችልህ ከማለት ወይስ። ተነሣ አልጋህንም ተሸከምና ሂድ ከማለት ማናቸው ይቀላል?
10`And, that ye may know that the Son of Man hath authority on the earth to forgive sins — (he saith to the paralytic) —
10ነገር ግን ለሰው ልጅ በምድር ላይ ኃጢአትን ሊያስተሰርይ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ፤
11I say to thee, Rise, and take up thy couch, and go away to thy house;`
11ሽባውን። አንተን እልሃለሁ፥ ተነሣ፥ አልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ አለው።
12and he rose immediately, and having taken up the couch, he went forth before all, so that all were astonished, and do glorify God, saying — `Never thus did we see.`
12ተነሥቶም ወዲያው አልጋውን ተሸክሞ በሁሉ ፊት ወጣ፥ ስለዚህም ሰዎች ሁሉ ተገረሙና። እንዲህ ያለ ከቶ አላየንም ብለው እግዚአብሔርን አከበሩ።
13And he went forth again by the sea, and all the multitude was coming unto him, and he was teaching them,
13ደግሞም በባሕር አጠገብ ወጣ፤ ሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ መጡና አስተማራቸው።
14and passing by, he saw Levi of Alpheus sitting at the tax-office, and saith to him, `Be following me,` and he, having risen, did follow him.
14ሲያልፍም በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረውን የእልፍዮስን ልጅ ሌዊን አየና። ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው።
15And it came to pass, in his reclining (at meat) in his house, that many tax-gatherers and sinners were reclining (at meat) with Jesus and his disciples, for there were many, and they followed him.
15በቤቱም በማዕድ ተቀምጦ ሳለ፥ ብዙ ቀራጮችና ኃጢአተኞች ከኢየሱስና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጡ፤ ብዙ ነበሩ ይከተሉትም ነበር።
16And the scribes and the Pharisees, having seen him eating with the tax-gatherers and sinners, said to his disciples, `Why — that with the tax-gatherers and sinners he doth eat and drink?`
16ጻፎችና ፈሪሳውያንም ከቀራጮችና ከኃጢአተኞች ጋር ሲበላ አይተው ለደቀ መዛሙርቱ። ከቀራ ጮችና ከኃጢአተኞች ጋር የሚበላና የሚጠጣ ስለ ምንድር ነው? አሉ።
17And Jesus, having heard, saith to them, `They who are strong have no need of a physician, but they who are ill; I came not to call righteous men, but sinners to reformation.`
17ኢየሱስም ሰምቶ። ሕመምተኞች እንጂ ብርቱዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም ኃጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም አላቸው።
18And the disciples of John and those of the Pharisees were fasting, and they come and say to him, `Wherefore do the disciples of John and those of the Pharisees fast, and thy disciples do not fast?`
18የዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና ፈሪሳውያን ይጦሙ ነበር። መጥተውም። የዮሐንስና የፈሪሳውያን ደቀ መዛሙርት የሚጦሙት የአንተ ደቀ መዛሙርት ግን የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው? አሉት።
19And Jesus said to them, `Are the sons of the bride-chamber able, while the bridegroom is with them, to fast? so long time as they have the bridegroom with them they are not able to fast;
19ኢየሱስም አላቸው። ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሚዜዎች ሊጦሙ ይችላሉን? ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊጦሙ አይችሉም።
20but days shall come when the bridegroom may be taken from them, and then they shall fast — in those days.
20ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ወራትም ይጦማሉ።
21`And no one a patch of undressed cloth doth sew on an old garment, and if not — the new filling it up doth take from the old and the rent doth become worse;
21በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚጥፍ የለም፤ ቢደረግ ግን፥ አዲሱ መጣፊያ አሮጌውን ይቦጭቀዋል፥ መቀደዱም የባሰ ይሆናል።
22and no one doth put new wine into old skins, and if not — the new wine doth burst the skins, and the wine is poured out, and the skins will be destroyed; but new wine into new skins is to be put.`
22በአረጀ አቁማዳም አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን፥ የወይን ጠጁ አቁማዳውን ያፈነዳል የወይኑም ጠጅ ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል አዲሱን የወይን ጠጅ ግን በአዲስ አቁማዳ ያኖራሉ።
23And it came to pass — he is going along on the sabbaths through the corn-fields — and his disciples began to make a way, plucking the ears,
23በሰንበትም በእርሻ መካከል ሲያልፍ ደቀ መዛሙርቱ እየሄዱ እሸት ይቀጥፉ ጀመር።
24and the Pharisees said to him, `Lo, why do they on the sabbaths that which is not lawful?`
24ፈሪሳውያንም። እነሆ፥ በሰንበት ያልተፈቀደውን ስለ ምን ያደርጋሉ? አሉት።
25And he said to them, `Did ye never read what David did, when he had need and was hungry, he and those with him?
25እርሱም። ዳዊት ባስፈለገውና በተራበ ጊዜ፥ እርሱ አብረውት ከነበሩት ጋር ያደረገውን፥ አብያተር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ፥
26how he went into the house of God, (at `Abiathar the chief priest,`) and the loaves of the presentation did eat, which it is not lawful to eat, except to the priests, and he gave also to those who were with him?`
26ከካህናት በቀር መብላት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕትን እንጀራ እንደ በላ፥ ከእርሱም ጋር ለነበሩት እንደ ሰጣቸው ከቶ አላነበባችሁምን? አላቸው።
27And he said to them, `The sabbath for man was made, not man for the sabbath,
27ደግሞ። ሰንበት ስለ ሰው ተፈጥሮአል እንጂ ሰው ስለ ሰንበት አልተፈጠረም፤
28so that the son of man is lord also of the sabbath.`
28እንዲሁም የሰው ልጅ ለሰንበት እንኳ ጌታዋ ነው አላቸው።