Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Matthew

10

1And having called to him his twelve disciples, he gave to them power over unclean spirits, so as to be casting them out, and to be healing every sickness, and every malady.
1አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ወደ እርሱ ጠርቶ፥ እንዲያወጡአቸው በርኩሳን መናፍስት ላይ ደዌንና ሕማምንም ሁሉ እንዲፈውሱ ሥልጣን ሰጣቸው።
2And of the twelve apostles the names are these: first, Simon, who is called Peter, and Andrew his brother; James of Zebedee, and John his brother;
2የአሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ስም ይህ ነው፤ መጀመሪያው ጴጥሮስ የተባለው ስምዖን ወንድሙ እንድርያስም፥ የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብም ወንድሙ ዮሐንስም፥
3Philip, and Bartholomew; Thomas, and Matthew the tax-gatherer; James of Alpheus, and Lebbeus who was surnamed Thaddeus;
3ፊልጶስም በርተሎሜዎስም፥ ቶማስም ቀራጩ ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም ታዴዎስም የተባለው ልብድዮስ፥
4Simon the Cananite, and Judas Iscariot, who did also deliver him up.
4ቀነናዊውም ስምዖን ደግሞም አሳልፎ የሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ።
5These twelve did Jesus send forth, having given command to them, saying, `To the way of the nations go not away, and into a city of the Samaritans go not in,
5እነዚህን አሥራ ሁለቱን ኢየሱስ ላካቸው፥ አዘዛቸውም፥ እንዲህም አለ። በአሕዛብ መንገድ አትሂዱ፥ ወደ ሳምራውያንም ከተማ አትግቡ፤
6and be going rather unto the lost sheep of the house of Israel.
6ይልቅስ የእስራኤል ቤት ወደሚሆኑ ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ እንጂ።
7`And, going on, proclaim saying that, the reign of the heavens hath come nigh;
7ሄዳችሁም። መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች ብላችሁ ስበኩ።
8infirm ones be healing, lepers be cleansing, dead be raising, demons be casting out — freely ye did receive, freely give.
8ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ።
9`Provide not gold, nor silver, nor brass in your girdles,
9ወርቅ ወይም ብር ወይም ናስ በመቀነታችሁ፥
10nor scrip for the way, nor two coats, nor sandals, nor staff — for the workman is worthy of his nourishment.
10ወይም ለመንገድ ከረጢት ወይም ሁለት እጀ ጠባብ ወይም ጫማ ወይም በትር አታግኙ፤ ለሠራተኛ ምግቡ ይገባዋልና።
11`And into whatever city or village ye may enter, inquire ye who in it is worthy, and there abide, till ye may go forth.
11በምትገቡባትም በማናቸይቱም ከተማ ወይም መንደር፥ በዚያ የሚገባው ማን እንደ ሆነ በጥንቃቄ መርምሩ፤ እስክትወጡም ድረስ በዚያ ተቀመጡ።
12And coming to the house salute it,
12ወደ ቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ፤
13and if indeed the house be worthy, let your peace come upon it; and if it be not worthy, let your peace turn back to you.
13ቤቱም የሚገባው ቢሆን ሰላማችሁ ይድረስለት፤ ባይገባው ግን ሰላማችሁ ይመለስላችሁ።
14`And whoever may not receive you nor hear your words, coming forth from that house or city, shake off the dust of your feet,
14ከማይቀበላችሁም ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ፥ ከዚያ ቤት ወይም ከዚያች ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ።
15verily I say to you, It shall be more tolerable for the land of Sodom and Gomorrah in the day of judgment than for that city.
15እውነት እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ይቀልላቸዋል።
16`Lo, I do send you forth as sheep in the midst of wolves, be ye therefore wise as the serpents, and simple as the doves.
16እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ።
17And, take ye heed of men, for they will give you up to sanhedrims, and in their synagogues they will scourge you,
17ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤
18and before governors and kings ye shall be brought for my sake, for a testimony to them and to the nations.
18ለእነርሱና ለአሕዛብም ምስክር እንዲሆን፥ ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ።
19`And whenever they may deliver you up, be not anxious how or what ye may speak, for it shall be given you in that hour what ye shall speak;
19አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤
20for ye are not the speakers, but the Spirit of your Father that is speaking in you.
20በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና።
21`And brother shall deliver up brother to death, and father child, and children shall rise up against parents, and shall put them to death,
21ወንድምም ወንድሙን፥ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ ይገድሉአቸውማል።
22and ye shall be hated by all because of my name, but he who hath endured to the end, he shall be saved.
22በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።
23`And whenever they may persecute you in this city, flee to the other, for verily I say to you, ye may not have completed the cities of Israel till the Son of Man may come.
23በአንዲቱ ከተማም መከራ ቢያሳዩአችሁ ወደ ሌላይቱ ሽሹ፤ እውነት እላችኋለሁና፥ የሰው ልጅ እስኪመጣ ድረስ የእስራኤልን ከተማዎች አትዘልቁም።
24`A disciple is not above the teacher, nor a servant above his lord;
24ደቀ መዝሙር ከመምህሩ፥ ባሪያም ከጌታው አይበልጥም።
25sufficient to the disciple that he may be as his teacher, and the servant as his lord; if the master of the house they did call Beelzeboul, how much more those of his household?
25ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ፥ ባሪያም እንደ ጌታው መሆኑ ይበቃዋል። ባለቤቱን ብዔል ዜቡል ካሉት፥ ቤተሰዎቹንማ እንዴት አብዝተው አይሉአቸው!
26`Ye may not, therefore, fear them, for there is nothing covered, that shall not be revealed, and hid, that shall not be known;
26እንግዲህ አትፍሩአቸው፤ የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለምና።
27that which I tell you in the darkness, speak in the light, and that which you hear at the ear, proclaim on the house-tops.
27በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ፤ በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ።
28`And be not afraid of those killing the body, and are not able to kill the soul, but fear rather Him who is able both soul and body to destroy in gehenna.
28ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ።
29`Are not two sparrows sold for an assar? and one of them shall not fall on the ground without your Father;
29ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም።
30and of you — even the hairs of the head are all numbered;
30የእናንተስ የራሳችሁ ጠጉር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል።
31be not therefore afraid, than many sparrows ye are better.
31እንግዲህ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ።
32`Every one, therefore, who shall confess in me before men, I also will confess in him before my Father who is in the heavens;
32ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤
33and whoever shall deny me before men, I also will deny him before my Father who is in the heavens.
33በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ።
34`Ye may not suppose that I came to put peace on the earth; I did not come to put peace, but a sword;
34በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም።
35for I came to set a man at variance against his father, and a daughter against her mother, and a daughter-in-law against her mother-in-law,
35ሰውን ከአባቱ፥ ሴት ልጅንም ከእናትዋ፥ ምራትንም ከአማትዋ እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና፤
36and the enemies of a man are those of his household.
36ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል።
37`He who is loving father or mother above me, is not worthy of me, and he who is loving son or daughter above me, is not worthy of me,
37ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤
38and whoever doth not receive his cross and follow after me, is not worthy of me.
38መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።
39`He who found his life shall lose it, and he who lost his life for my sake shall find it.
39ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም ስለ እኔ የሚያጠፋ ያገኛታል።
40`He who is receiving you doth receive me, and he who is receiving me doth receive Him who sent me,
40እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።
41he who is receiving a prophet in the name of a prophet, shall receive a prophet`s reward, and he who is receiving a righteous man in the name of a righteous man, shall receive a righteous man`s reward,
41ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።
42and whoever may give to drink to one of these little ones a cup of cold water only in the name of a disciple, verily I say to you, he may not lose his reward.`
42ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።