1And having gone to the boat, he passed over, and came to his own city,
1በታንኳም ገብቶ ተሻገረና ወደ ገዛ ከተማው መጣ።
2and lo, they were bringing to him a paralytic, laid upon a couch, and Jesus having seen their faith, said to the paralytic, `Be of good courage, child, thy sins have been forgiven thee.`
2እነሆም፥ በአልጋ የተኛ ሽባ ወደ እርሱ አመጡ። ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን። አንተ ልጅ፥ አይዞህ፥ ኃጢአትህ ተሰረየችልህ አለው።
3And lo, certain of the scribes said within themselves, `This one doth speak evil.`
3እነሆም፥ ከጻፎቹ አንዳንዱ በልባቸው። ይህስ ይሳደባል አሉ።
4And Jesus, having known their thoughts, said, `Why think ye evil in your hearts?
4ኢየሱስም አሳባቸውን አውቆ እንዲህ አለ። ስለ ምን በልባችሁ ክፉ ታስባላችሁ?
5for which is easier? to say, The sins have been forgiven to thee; or to say, Rise, and walk?
5ኃጢአትህ ተሰረየችልህ ከማለት ወይስ። ተነሣና ሂድ ከማለት ማናቸው ይቀላል?
6`But, that ye may know that the Son of Man hath power upon the earth to forgive sins — (then saith he to the paralytic) — having risen, take up thy couch, and go to thy house.`
6ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢአትን ያስተሰርይ ዘንድ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ፥ በዚያን ጊዜ ሽባውን። ተነሣ፤ አልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ አለው።
7And he, having risen, went to his house,
7ተነሥቶም ወደ ቤቱ ሄደ።
8and the multitudes having seen, wondered, and glorified God, who did give such power to men.
8ሕዝቡም አይተው ተደነቁ፥ ለሰውም እንዲህ ያለ ሥልጣን የሰጠ እግዚአብሔርን አከበሩ።
9And Jesus passing by thence, saw a man sitting at the tax-office, named Matthew, and saith to him, `Be following me,` and he, having risen, did follow him.
9ኢየሱስም ከዚያ አልፎ በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረ ማቴዎስ የሚባል አንድ ሰው አየና። ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው።
10And it came to pass, he reclining (at meat) in the house, that lo, many tax-gatherers and sinners having come, were lying (at meat) with Jesus and his disciples,
10በቤቱም በማዕድ ተቀምጦ ሳለ፥ እነሆ፥ ብዙ ቀራጮችና ኃጢአተኞች መጥተው ከኢየሱስና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አብረው ተቀመጡ።
11and the Pharisees having seen, said to his disciples, `Wherefore with the tax-gatherers and sinners doth your teacher eat?`
11ፈሪሳውያንም አይተው ደቀ መዛሙርቱን። መምህራችሁ ከቀራጮችና ከኃጢአተኞች ጋር አብሮ ስለ ምን ይበላል? አሉአቸው።
12And Jesus having heard, said to them, `They who are whole have no need of a physician, but they who are ill;
12ኢየሱስም ሰምቶ። ሕመምተኞች እንጂ ባለ ጤናዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም፤
13but having gone, learn ye what is, Kindness I will, and not sacrifice, for I did not come to call righteous men, but sinners, to reformation.`
13ነገር ግን ሄዳችሁ። ምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም ያለው ምን እንደ ሆነ ተማሩ፤ ኃጢአተኞችን ወደ ንስሐ እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁምና አላቸው።
14Then come to him do the disciples of John, saying, `Wherefore do we and the Pharisees fast much, and thy disciples fast not?`
14በዚያን ጊዜ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው። እኛና ፈሪሳውያን፥ ብዙ ጊዜ የምንጦመው፥ ደቀ መዛሙርትህ ግን የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው? አሉት።
15And Jesus said to them, `Can the sons of the bride-chamber mourn, so long as the bridegroom is with them? but days shall come when the bridegroom may be taken from them, and then they shall fast.
15ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ።
16`And no one doth put a patch of undressed cloth on an old garment, for its filling up doth take from the garment, and a worse rent is made.
16በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፥ መቀደዱም የባሰ ይሆናል።
17`Nor do they put new wine into old skins, and if not — the skins burst, and the wine doth run out, and the skins are destroyed, but they put new wine into new skins, and both are preserved together.`
17በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን፥ አቁማዳው ይፈነዳል፥ የወይን ጠጁም ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል፤ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል፥ ሁለቱም ይጠባበቃሉ።
18While he is speaking these things to them, lo, a ruler having come, was bowing to him, saying that `My daughter just now died, but, having come, lay thy hand upon her, and she shall live.`
18ይህንም ሲነግራቸው፥ አንድ መኰንን መጥቶ። ልጄ አሁን ሞተች፤ ነገር ግን መጥተህ እጅህን ጫንባት፥ በሕይወትም ትኖራለች እያለ ሰገደለት።
19And Jesus having risen, did follow him, also his disciples,
19ኢየሱስም ተነሥቶ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተከተለው።
20and lo, a woman having an issue of blood twelve years, having come to him behind, did touch the fringe of his garments,
20እነሆም፥ ከአሥራ ሁለት ዓመት ጀምሮ ደም የሚፈስሳት ሴት በኋላው ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች፤
21for she said within herself, `If only I may touch his garment, I shall be saved.`
21በልብዋ። ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ፥ እድናለሁ ትል ነበረችና።
22And Jesus having turned about, and having seen her, said, `Be of good courage, daughter, thy faith hath saved thee,` and the woman was saved from that hour.
22ኢየሱስም ዘወር ብሎ አያትና። ልጄ ሆይ፥ አይዞሽ፤ እምነትሽ አድኖሻል አላት። ሴቲቱም ከዚያች ሰዓት ጀምራ ዳነች።
23And Jesus having come to the house of the ruler, and having seen the minstrels and the multitude making tumult,
23ኢየሱስም ወደ መኰንኑ ቤት በደረሰ ጊዜ፥ እምቢልተኞችንና የሚንጫጫውን ሕዝብ አይቶ።
24he saith to them, `Withdraw, for the damsel did not die, but doth sleep,` and they were deriding him;
24ብላቴናይቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችምና ፈቀቅ በሉ አላቸው። በጣምም ሳቁበት።
25but, when the multitude was put forth, having gone in, he took hold of her hand, and the damsel arose,
25ሕዝቡን ግን ከአስወጡ በኋላ ገብቶ እጅዋን ያዛት፥ ብላቴናይቱም ተነሣች።
26and the fame of this went forth to all the land.
26ያም ዝና ወደዚያ አገር ሁሉ ወጣ።
27And Jesus passing on thence, two blind men followed him, calling and saying, `Deal kindly with us, Son of David.`
27ኢየሱስም ከዚያ ሲያልፍ ሁለት ዕውሮች። የዳዊት ልጅ ሆይ፥ ማረን ብለው እየጮሁ ተከተሉት።
28And he having come to the house, the blind men came to him, and Jesus saith to them, `Believe ye that I am able to do this?` They say to him, `Yes, sir.`
28ወደ ቤትም በገባ ጊዜ ዕውሮቹ ወደ እርሱ ቀረቡ፥ ኢየሱስም። ይህን ማድረግ እንድችል ታምናላችሁን? አላቸው። አዎን፥ ጌታ ሆይ አሉት።
29Then touched he their eyes, saying, `According to your faith let it be to you,`
29በዚያን ጊዜ። እንደ እምነታችሁ ይሁንላችሁ ብሎ ዓይኖቻቸውን ዳሰሰ።
30and their eyes were opened, and Jesus strictly charged them, saying, `See, let no one know;`
30ዓይኖቻቸውም ተከፈቱ።
31but they, having gone forth, did spread his fame in all that land.
31ኢየሱስም። ማንም እንዳያውቅ ተጠንቀቁ ብሎ በብርቱ አዘዛቸው። እነርሱ ግን ወጥተው በዚያ አገር ሁሉ ስለ እርሱ አወሩ።
32And as they are coming forth, lo, they brought to him a man dumb, a demoniac,
32እነርሱም ሲወጡ እነሆ፥ ጋኔን ያደረበትን ዲዳ ሰው ወደ እርሱ አመጡ።
33and the demon having been cast out, the dumb spake, and the multitude did wonder, saying that `It was never so seen in Israel:`
33ጋኔኑንም ካወጣው በኋላ ዲዳው ተናገረ። ሕዝቡም። እንዲህ ያለ በእስራኤል ዘንድ ከቶ አልታየም እያሉ ተደነቁ።
34but the Pharisees said, `By the ruler of the demons he doth cast out the demons.`
34ፈሪሳውያን ግን። በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል አሉ።
35And Jesus was going up and down all the cities and the villages, teaching in their synagogues, and proclaiming the good news of the reign, and healing every sickness and every malady among the people.
35ኢየሱስም በምኩራቦቻቸው እያስተማረ፥ የመንግሥትንም ወንጌል እየሰበከ፥ በሕዝብም ያለውን ደዌና ሕማም ሁሉ እየፈወሰ፥ በከተማዎችና በመንደሮች ሁሉ ይዞር ነበር።
36And having seen the multitudes, he was moved with compassion for them, that they were faint and cast aside, as sheep not having a shepherd,
36ብዙ ሕዝብም ባየ ጊዜ፥ እረኛ እንደ ሌላቸው በጎች ተጨንቀው ተጥለውም ነበርና አዘነላቸው።
37then saith he to his disciples, `The harvest indeed [is] abundant, but the workmen few;
37በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤
38beseech ye therefore the Lord of the harvest, that he may put forth workmen to His harvest.`
38እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት አላቸው።