1Then Jesus spake to the multitudes, and to his disciples,
1በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለሕዝቡና ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ብሎ ነገራቸው።
2saying, `On the seat of Moses sat down the scribes and the Pharisees;
2ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል።
3all, then, as much as they may say to you to observe, observe and do, but according to their works do not, for they say, and do not;
3ስለዚህ ያዘዙአችሁን ሁሉ አድርጉ ጠብቁትም፥ ነገር ግን እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ።
4for they bind together burdens heavy and grievous to be borne, and lay upon the shoulders of men, but with their finger they will not move them.
4ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ፥ እነርሱ ግን በጣታቸው ስንኳ ሊነኩት አይወዱም።
5`And all their works they do to be seen by men, and they make broad their phylacteries, and enlarge the fringes of their garments,
5ለሰውም እንዲታዩ ሥራቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፤ ስለዚህ አሽንክታባቸውን ያሰፋሉ ዘርፉንም ያስረዝማሉ፥
6they love also the chief couches in the supper, and the chief seats in the synagogues,
6በምሳም የከበሬታ ስፍራ፥ በምኵራብም የከበሬታ ወንበር፥
7and the salutations in the market-places, and to be called by men, Rabbi, Rabbi.
7በገበያም ሰላምታና። መምህር ሆይ መምህር ሆይ ተብለው እንዲጠሩ ይወዳሉ።
8`And ye — ye may not be called Rabbi, for one is your director — the Christ, and all ye are brethren;
8እናንተ ግን። መምህር ተብላችሁ አትጠሩ፤ መምህራችሁ አንድ ስለ ሆነ እናንተም ሁላችሁ ወንድማማች ናችሁ።
9and ye may not call [any] your father on the earth, for one is your Father, who is in the heavens,
9አባታችሁ አንዱ እርሱም የሰማዩ ነውና በምድር ላይ ማንንም። አባት ብላችሁ አትጥሩ።
10nor may ye be called directors, for one is your director — the Christ.
10ሊቃችሁ አንድ እርሱም ክርስቶስ ነውና። ሊቃውንት ተብላችሁ አትጠሩ።
11And the greater of you shall be your ministrant,
11ከእናንተም የሚበልጠው አገልጋያችሁ ይሆናል።
12and whoever shall exalt himself shall be humbled, and whoever shall humble himself shall be exalted.
12ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፥ ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል።
13`Wo to you, Scribes and Pharisees, hypocrites! because ye shut up the reign of the heavens before men, for ye do not go in, nor those going in do ye suffer to enter.
13እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ መንግሥተ ሰማያትን በሰው ፊት ስለምትዘጉ፥ ወዮላችሁ እናንተ አትገቡም የሚገቡትንም እንዳይገቡ ትከለክላላችሁ።
14`Wo to you, Scribes and Pharisees, hypocrites! because ye eat up the houses of the widows, and for a pretence make long prayers, because of this ye shall receive more abundant judgment.
14እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በጸሎት ርዝመት እያመካኛችሁ የመበለቶችን ቤት ስለምትበሉ፥ ወዮላችሁ፤ ስለዚህ የባሰ ፍርድ ትቀበላላችሁ።
15`Wo to you, Scribes and Pharisees, hypocrites! because ye go round the sea and the dry land to make one proselyte, and whenever it may happen — ye make him a son of gehenna twofold more than yourselves.
15እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ አንድ ሰው ልታሳምኑ በባሕርና በደረቅ ስለምትዞሩ፥ በሆነም ጊዜ ከእናንተ ይልቅ ሁለት እጥፍ የባሰ የገሃነም ልጅ ስለምታደርጉት፥ ወዮላችሁ።
16`Wo to you, blind guides, who are saying, Whoever may swear by the sanctuary, it is nothing, but whoever may swear by the gold of the sanctuary — is debtor!
16እናንተ። ማንም በቤተ መቅደስ የሚምል ምንም የለበትም፤ ማንም በቤተ መቅደስ ወርቅ የሚምል ግን በመሐላው ይያዛል የምትሉ፥ ዕውሮች መሪዎች፥ ወዮላችሁ።
17Fools and blind! for which [is] greater, the gold, or the sanctuary that is sanctifying the gold?
17እናንተ ደንቆሮዎችና ዕውሮች፥ ማናቸው ይበልጣል? ወርቁ ነውን? ወይስ ወርቁን የቀደሰው ቤተ መቅደስ?
18`And, whoever may swear by the altar, it is nothing; but whoever may swear by the gift that is upon it — is debtor!
18ደግማችሁም። ማንም በመሠዊያው የሚምል ምንም የለበትም፤ ማንም በላዩ ባለው መባ የሚምል ግን በመሐላው ይያዛል ትላላችሁ።
19Fools and blind! for which [is] greater, the gift, or the altar that is sanctifying the gift?
19እናንተ ደንቆሮዎችና ዕውሮች፥ ማናቸው ይበልጣል? መባው ነውን? ወይስ መባውን የሚቀድሰው መሠዊያው?
20`He therefore who did swear by the altar, doth swear by it, and by all things on it;
20እንግዲህ በመሠዊያው የሚምለው በእርሱና በእርሱ ላይ ባለው ሁሉ ይምላል፤
21and he who did swear by the sanctuary, doth swear by it, and by Him who is dwelling in it;
21በቤተ መቅደስም የሚምለው በእርሱና በእርሱ በሚኖረው ይምላል፤
22and he who did swear by the heaven, doth swear by the throne of God, and by Him who is sitting upon it.
22በሰማይም የሚምለው በእግዚአብሔር ዙፋንና በእርሱ ላይ በተቀመጠው ይምላል።
23`Wo to you, Scribes and Pharisees, hypocrites! because ye give tithe of the mint, and the dill, and the cumin, and did neglect the weightier things of the Law — the judgment, and the kindness, and the faith; these it behoved [you] to do, and those not to neglect.
23እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ ከአዝሙድና ከእንስላል ከከሙንም አሥራት ስለምታወጡ፥ ፍርድንና ምሕረትን ታማኝነትንም፥ በሕግ ያለውን ዋና ነገር ስለምትተዉ፥ ወዮላችሁ፤ ሌላውን ሳትተዉ ይህን ልታደርጉ ይገባችሁ ነበር።
24`Blind guides! who are straining out the gnat, and the camel are swallowing.
24እናንተ ዕውሮች መሪዎች፥ ትንኝን የምታጠሩ ግመልንም የምትውጡ።
25`Wo to you, Scribes and Pharisees, hypocrites! because ye make clean the outside of the cup and the plate, and within they are full of rapine and incontinence.
25እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በውስጡ ቅሚያና ስስት ሞልቶ ሳለ የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ስለምታጠሩ፥ ወዮላችሁ።
26`Blind Pharisee! cleanse first the inside of the cup and the plate, that the outside of them also may become clean.
26አንተ ዕውር ፈሪሳዊ፥ ውጭው ደግሞ ጥሩ እንዲሆን አስቀድመህ የጽዋውንና የወጭቱን ውስጡን አጥራ።
27`Wo to you, Scribes and Pharisees, hypocrites! because ye are like to whitewashed sepulchres, which outwardly indeed do appear beautiful, and within are full of bones of dead men, and of all uncleanness;
27እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በውጭ አምረው የሚታዩ በውስጡ ግን የሙታን አጥንት ርኩሰትም ሁሉ የተሞሉ በኖራ የተለሰኑ መቃብሮችን ስለምትመስሉ፥ ወዮላችሁ።
28so also ye outwardly indeed do appear to men righteous, and within ye are full of hypocrisy and lawlessness.
28እንዲሁ እናንተ ደግሞ በውጭ ለሰው እንደ ጻድቃን ትታያላችሁ፥ በውስጣችሁ ግን ግብዝነትና ዓመፀኝነት ሞልቶባችኋል።
29`Wo to you, Scribes and Pharisees, hypocrites! because ye build the sepulchres of the prophets, and adorn the tombs of the righteous,
29እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ የነቢያትን መቃብር ስለምትሠሩ የጻድቃንንም መቃብር ስለምታስጌጡና።
30and say, If we had been in the days of our fathers, we would not have been partakers with them in the blood of the prophets.
30በአባቶቻችን ዘመን ኖረን በሆነስ በነቢያት ደም ባልተባበርናቸውም ነበር ስለምትሉ፥ ወዮላችሁ።
31So that ye testify to yourselves, that ye are sons of them who did murder the prophets;
31እንግዲያስ የነቢያት ገዳዮች ልጆች እንደሆናችሁ በራሳችሁ ላይ ትመሰክራላችሁ።
32and ye — ye fill up the measure of your fathers.
32እናንተ ደግሞ የአባቶቻችሁን መስፈሪያ ሙሉ።
33`Serpents! brood of vipers! how may ye escape from the judgment of the gehenna?
33እናንተ እባቦች፥ የእፉኝት ልጆች፥ ከገሃነም ፍርድ እንዴት ታመልጣላችሁ?
34`Because of this, lo, I send to you prophets, and wise men, and scribes, and of them ye will kill and crucify, and of them ye will scourge in your synagogues, and will pursue from city to city;
34ስለዚህ፥ እነሆ፥ ነቢያትንና ጥበበኞችን ጻፎችንም ወደ እናንተ እልካለሁ፤ ከእነርሱም ትገድላላችሁ ትሰቅሉማላችሁ፥ ከእነርሱም በምኵራባችሁ ትገርፋላችሁ ከከተማም ወደ ከተማ ታሳድዳላችሁ፤
35that on you may come all the righteous blood being poured out on the earth from the blood of Abel the righteous, unto the blood of Zacharias son of Barachias, whom ye slew between the sanctuary and the altar:
35ከጻድቁ ከአቤል ደም ጀምሮ በቤተ መቅደስና በመሠዊያው መካከል እስከ ገደላችሁት እስከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በምድር ላይ የፈሰሰው የጻድቅ ደም ሁሉ ይደርስባችሁ ዘንድ።
36verily I say to you, all these things shall come upon this generation.
36እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ በዚህ ትውልድ ላይ ይደርሳል።
37`Jerusalem, Jerusalem, that art killing the prophets, and stoning those sent unto thee, how often did I will to gather thy children together, as a hen doth gather her own chickens under the wings, and ye did not will.
37ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርስዋ የተላኩትንም የምትወግር፥ ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፎችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም።
38Lo, left desolate to you is your house;
38እነሆ፥ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል።
39for I say to you, ye may not see me henceforth, till ye may say, Blessed [is] he who is coming in the name of the Lord.`
39እላችኋለሁና፥ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ ከእንግዲህ ወዲህ አታዩኝም።