Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Romans

11

1I say, then, Did God cast away His people? let it not be! for I also am an Israelite, of the seed of Abraham, of the tribe of Benjamin:
1እንግዲህ። እግዚአብሔር ሕዝቡን ጣላቸውን? እላለሁ። አይደለም እኔ ደግሞ እስራኤላዊና ከአብርሃም ዘር ከብንያምም ወገን ነኝና።
2God did not cast away His people whom He knew before; have ye not known — in Elijah — what the Writing saith? how he doth plead with God concerning Israel, saying,
2እግዚአብሔር አስቀድሞ ያወቃቸውን ሕዝብ አልጣላቸውም። መጽሐፍ ስለ ኤልያስ በተጻፈው የሚለውን፥ በእግዚአብሔር ፊት እስራኤልን እንዴት እንደሚከስ፥ አታውቁምን?
3`Lord, Thy prophets they did kill, and Thy altars they dug down, and I was left alone, and they seek my life;`
3ጌታ ሆይ፥ ነቢያትህን ገደሉ መሠዊያዎችህንም አፈረሱ እኔም ብቻዬን ቀረሁ ነፍሴንም ይሹአታል።
4but what saith the divine answer to him? `I left to Myself seven thousand men, who did not bow a knee to Baal.`
4ነገር ግን አምላካዊ መልስ ምን አለው? ለበአል ያልሰገዱትን ሰባት ሺህ ሰዎች ለእኔ አስቀርቼአለሁ።
5So then also in the present time a remnant according to the choice of grace there hath been;
5እንደዚሁም በአሁን ዘመን ደግሞ በጸጋ የተመረጡ ቅሬታዎች አሉ።
6and if by grace, no more of works, otherwise the grace becometh no more grace; and if of works, it is no more grace, otherwise the work is no more work.
6በጸጋ ከሆነ ግን ከሥራ መሆኑ ቀርቶአል፤ ጸጋ ያለዚያ ጸጋ መሆኑ ቀርቶአል።
7What then? What Israel doth seek after, this it did not obtain, and the chosen did obtain, and the rest were hardened,
7እንግዲህ ምንድር ነው? እስራኤል የሚፈልጉትን አላገኙትም፤ የተመረጡት ግን አገኙት፤
8according as it hath been written, `God gave to them a spirit of deep sleep, eyes not to see, and ears not to hear,` — unto this very day,
8ሌሎቹም ደነዘዙ፤ እንዲሁም። ዓይኖቻቸው እንዳያዩ ጆሮቻቸውም እንዳይሰሙ እግዚአብሔር የእንቅልፍ መንፈስን እስከ ዛሬ ድረስ ሰጣቸው ተብሎ ተጽፎአል። ዳዊትም።
9and David saith, `Let their table become for a snare, and for a trap, and for a stumbling-block, and for a recompense to them;
9ማዕዳቸው ወጥመድና አሽክላ ማሰናከያም ፍዳም ይሁንባቸው፤
10let their eyes be darkened — not to behold, and their back do Thou always bow down.`
10ዓይኖቻቸው እንዳያዩ ይጨልሙ፥ ጀርባቸውንም ዘወትር አጉብጥ ብሎአል።
11I say, then, Did they stumble that they might fall? let it not be! but by their fall the salvation [is] to the nations, to arouse them to jealousy;
11እንግዲህ። የተሰናከሉ እስኪወድቁ ድረስ ነውን? እላለሁ። አይደለም፤ ነገር ግን እነርሱን ያስቀናቸው ዘንድ በእነርሱ በደል መዳን ለአሕዛብ ሆነ።
12and if the fall of them [is] the riches of a world, and the diminution of them the riches of nations, how much more the fulness of them?
12ዳሩ ግን በደላቸው ለዓለም ባለ ጠግነት መሸነፋቸውም ለአሕዛብ ባለ ጠግነት ከሆነ፥ ይልቁንስ መሙላታቸው እንዴት ይሆን?
13For to you I speak — to the nations — inasmuch as I am indeed an apostle of nations, my ministration I do glorify;
13ለእናንተም ለአሕዛብ እናገራለሁ። እኔ የአሕዛብ ሐዋርያ በሆንሁ መጠን ሥጋዬ የሆኑትን አስቀንቼ ምናልባት ከእነርሱ አንዳንዱን አድን እንደሆነ አገልግሎቴን አከብራለሁ።
14if by any means I shall arouse to jealousy mine own flesh, and shall save some of them,
15የእነርሱ መጣል ለዓለም መታረቅ ከሆነ ከሙታን ከሚመጣ ሕይወት በቀር መመለሳቸው ምን ይሆን?
15for if the casting away of them [is] a reconciliation of the world, what the reception — if not life out of the dead?
16በኵራቱም ቅዱስ ከሆነ ብሆው ደግሞ ቅዱስ ነው፤ ሥሩም ቅዱስ ከሆነ ቅርንጫፎቹ ደግሞ ቅዱሳን ናቸው።
16and if the first-fruit [is] holy, the lump also; and if the root [is] holy, the branches also.
17ነገር ግን ከቅርንጫፎች አንዳንዱ ቢሰበሩ አንተም የበረሀ ወይራ የሆንህ በመካከላቸው ገብተህ ከእነርሱ ጋር የወይራ ዘይት ከሚወጣው ሥር ተካፋይ ከሆንህ፥ በቅርንጫፎች ላይ አትመካ፤
17And if certain of the branches were broken off, and thou, being a wild olive tree, wast graffed in among them, and a fellow-partaker of the root and of the fatness of the olive tree didst become —
18ብትመካባቸው ግን ሥሩ አንተን ይሸከምሃል እንጂ ሥሩን የምትሸከም አንተ አይደለህም።
18do not boast against the branches; and if thou dost boast, thou dost not bear the root, but the root thee!
19እንግዲህ። እኔ እንድገባ ቅርንጫፎች ተሰበሩ ትል ይሆናል።
19Thou wilt say, then, `The branches were broken off, that I might be graffed in;` right!
20መልካም፤ እነርሱ ከአለማመን የተነሣ ተሰበሩ አንተም ከእምነት የተነሣ ቆመሃል። ፍራ እንጂ የትዕቢትን ነገር አታስብ።
20by unbelief they were broken off, and thou hast stood by faith; be not high-minded, but be fearing;
21እግዚአብሔር እንደ ተፈጠሩት ለነበሩት ቅርንጫፎች የራራላቸው ካልሆነ ለአንተ ደግሞ አይራራልህምና።
21for if God the natural branches did not spare — lest perhaps He also shall not spare thee.
22እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ጭከና ተመልከት፤ ጭከናው በወደቁት ላይ ነው፥ በቸርነቱ ግን ጸንተህ ብትኖር የእግዚአብሔር ቸርነት በአንተ ላይ ነው፤ ያለዚያ አንተ ደግሞ ትቆረጣለህ።
22Lo, then, goodness and severity of God — upon those indeed who fell, severity; and upon thee, goodness, if thou mayest remain in the goodness, otherwise, thou also shalt be cut off.
23እነዚያም ደግሞ በአለማመናቸው ጸንተው ባይኖሩ በዛፉ ውስጥ ይገባሉ፤ እግዚአብሔር መልሶ ሊያገባቸው ይችላልና።
23And those also, if they may not remain in unbelief, shall be graffed in, for God is able again to graff them in;
24አንተ በፍጥረቱ የበረሀ ከነበረ ወይራ ተቆርጠህ እንደ ፍጥረትህ ሳትሆን በመልካም ወይራ ከገባህ፥ ይልቁንስ እነዚያ በፍጥረታቸው ያሉት ቅርንጫፎች በራሳቸው ወይራ እንዴት አይገቡም?
24for if thou, out of the olive tree, wild by nature, wast cut out, and, contrary to nature, wast graffed into a good olive tree, how much rather shall they, who [are] according to nature, be graffed into their own olive tree?
25ወንድሞች ሆይ፥ ልባሞች የሆናችሁ እንዳይመስላችሁ ይህን ምሥጢር ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ፤ የአሕዛብ ሙላት እስኪገባ ድረስ ድንዛዜ በእስራኤል በአንዳንድ በኩል ሆነባቸው፤
25For I do not wish you to be ignorant, brethren, of this secret — that ye may not be wise in your own conceits — that hardness in part to Israel hath happened till the fulness of the nations may come in;
26እንደዚሁም እስራኤል ሁሉ ይድናል፤ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ። መድኃኒት ከጽዮን ይወጣል ከያዕቆብም ኃጢአተኛነትን ያስወግዳል።
26and so all Israel shall be saved, according as it hath been written, `There shall come forth out of Sion he who is delivering, and he shall turn away impiety from Jacob,
27ኃጢአታቸውንም ስወስድላቸው ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው።
27and this to them [is] the covenant from Me, when I may take away their sins.`
28በወንጌልስ በኩል ስለ እናንተ ጠላቶች ናቸው፥ በምርጫ በኩል ግን ስለ አባቶች ተወዳጆች ናቸው፤
28As regards, indeed, the good tidings, [they are] enemies on your account; and as regards the choice — beloved on account of the fathers;
29እግዚአብሔር በጸጋው ስጦታና በመጥራቱ አይጸጸትምና።
29for unrepented of [are] the gifts and the calling of God;
30እናንተም ቀድሞ ለእግዚአብሔር እንዳልታዘዛችሁ፥ አሁን ግን ከአለመታዘዛቸው የተነሣ ምሕረት እንዳገኛችሁ፥
30for as ye also once did not believe in God, and now did find kindness by the unbelief of these:
31እንዲሁ በተማራችሁበት ምሕረት እነርሱ ደግሞ ምሕረትን ያገኙ ዘንድ እነዚህ ደግሞ አሁን አልታዘዙም።
31so also these now did not believe, that in your kindness they also may find kindness;
32እግዚአብሔር ሁሉን ይምር ዘንድ ሁሉን በአለመታዘዝ ዘግቶታልና።
32for God did shut up together the whole to unbelief, that to the whole He might do kindness.
33የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።
33O depth of riches, and wisdom and knowledge of God! how unsearchable His judgments, and untraceable His ways!
34የጌታን ልብ ያወቀው ማን ነው?
34for who did know the mind of the Lord? or who did become His counsellor?
35ወይስ አማካሪው ማን ነበር? ወይስ ብድራቱን ይመልስ ዘንድ ለእርሱ አስቀድሞ የሰጠው ማን ነው?
35or who did first give to Him, and it shall be given back to him again?
36ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።
36because of Him, and through Him, and to Him [are] the all things; to Him [is] the glory — to the ages. Amen.