Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Romans

10

1Brethren, the pleasure indeed of my heart, and my supplication that [is] to God for Israel, is — for salvation;
1ወንድሞች ሆይ፥ የልቤ በጎ ፈቃድና ስለ እስራኤል ወደ እግዚአብሔር ልመናዬ እንዲድኑ ነው።
2for I bear them testimony that they have a zeal of God, but not according to knowledge,
2በእውቀት አይቅኑ እንጂ ለእግዚአብሔር እንዲቀኑ እመሰክርላቸዋለሁና።
3for not knowing the righteousness of God, and their own righteousness seeking to establish, to the righteousness of God they did not submit.
3የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
4For Christ is an end of law for righteousness to every one who is believing,
4የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።
5for Moses doth describe the righteousness that [is] of the law, that, `The man who did them shall live in them,`
5ሙሴ ከሕግ የሆነውን ጽድቅ የሚያደርገው ሰው በእርሱ በሕይወት እንዲኖር ጽፎአልና።
6and the righteousness of faith doth thus speak: `Thou mayest not say in thine heart, Who shall go up to the heaven,` that is, Christ to bring down?
6ከእምነት የሆነ ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል። በልብህ። ማን ወደ ሰማይ ይወጣል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
7or, `Who shall go down to the abyss,` that is, Christ out of the dead to bring up.
7ወይም። በልብህ። ወደ ጥልቁ ማን ይወርዳል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
8But what doth it say? `Nigh thee is the saying — in thy mouth, and in thy heart:` that is, the saying of the faith, that we preach;
8ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።
9that if thou mayest confess with thy mouth the Lord Jesus, and mayest believe in thy heart that God did raise him out of the dead, thou shalt be saved,
9ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
10for with the heart doth [one] believe to righteousness, and with the mouth is confession made to salvation;
10ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
11for the Writing saith, `Every one who is believing on him shall not be ashamed,`
11መጽሐፍ። በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
12for there is no difference between Jew and Greek, for the same Lord of all [is] rich to all those calling upon Him,
12በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
13for every one — whoever shall call upon the name of the Lord, he shall be saved.`
13የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።
14How then shall they call upon [him] in whom they did not believe? and how shall they believe [on him] of whom they did not hear? and how shall they hear apart from one preaching?
14እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?
15and how shall they preach, if they may not be sent? according as it hath been written, `How beautiful the feet of those proclaiming good tidings of peace, of those proclaiming good tidings of the good things!`
15መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ?
16But they were not all obedient to the good tidings, for Isaiah saith, `Lord, who did give credence to our report?`
16ነገር ግን ሁሉ ለምሥራቹ ቃል አልታዘዙም። ኢሳይያስ። ጌታ ሆይ፥ ምስክርነታችንን ማን አመነ? ብሎአልና።
17so then the faith [is] by a report, and the report through a saying of God,
17እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።
18but I say, Did they not hear? yes, indeed — `to all the earth their voice went forth, and to the ends of the habitable world their sayings.`
18ዳሩ ግን። ባይሰሙ ነው ወይ? እላለሁ። በእውነት። ድምፃቸው በምድር ሁሉ ላይ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ።
19But I say, Did not Israel know? first Moses saith, `I will provoke you to jealousy by [that which is] not a nation; by an unintelligent nation I will anger you,`
19ነገር ግን። እስራኤል ባያውቁ ነው ወይ? እላለሁ። ሙሴ አስቀድሞ። እኔ ሕዝብ በማይሆነው አስቀናችኋለሁ በማያስተውልም ሕዝብ አስቆጣችኋለሁ
20and Isaiah is very bold, and saith, `I was found by those not seeking Me; I became manifest to those not inquiring after Me;`
20ብሎአል። ኢሳይያስም ደፍሮ። ላልፈለጉኝ ተገኘሁ፥ ላልጠየቁኝም ተገለጥሁ አለ።
21and unto Israel He saith, `All the day I did stretch out My hands unto a people unbelieving and gainsaying.`
21ስለ እስራኤል ግን። ቀኑን ሁሉ ወደማይታዘዝና ወደሚቃወም ሕዝብ እጆቼን ዘረጋሁ ይላል።