Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

Romans

9

1Truth I say in Christ, I lie not, my conscience bearing testimony with me in the Holy Spirit,
1ብዙ ኀዘን የማያቋርጥም ጭንቀት በልቤ አለብኝ ስል በክርስቶስ ሆኜ እውነትን እናገራለሁ፤ አልዋሽምም፤ ሕሊናዬም በመንፈስ ቅዱስ ይመሰክርልኛል።
2that I have great grief and unceasing pain in my heart —
3በሥጋ ዘመዶቼ ስለ ሆኑ ስለ ወንድሞቼ ከክርስቶስ ተለይቼ እኔ ራሴ የተረገምሁ እንድሆን እጸልይ ነበርና።
3for I was wishing, I myself, to be anathema from the Christ — for my brethren, my kindred, according to the flesh,
4እነርሱ እስራኤላውያን ናቸውና፥ ልጅነትና ክብር ኪዳንም የሕግም መሰጠት የመቅደስም ሥርዓት የተስፋውም ቃላት ለእነርሱ ናቸውና፤
4who are Israelites, whose [is] the adoption, and the glory, and the covenants, and the lawgiving, and the service, and the promises,
5አባቶችም ለእነርሱ ናቸውና፤ ከእነርሱም ክርስቶስ በሥጋ መጣ፥ እርሱም ከሁሉ በላይ ሆኖ ለዘላለም የተባረከ አምላክ ነው፤ አሜን።
5whose [are] the fathers, and of whom [is] the Christ, according to the flesh, who is over all, God blessed to the ages. Amen.
6ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል የተሻረ አይደለም። እነዚህ ከእስራኤል የሚወለዱ ሁሉ እስራኤል አይደሉምና፤ የአብርሃምም ዘር ስለሆኑ ሁላቸው ልጆች አይደሉም፥
6And it is not possible that the word of God hath failed; for not all who [are] of Israel are these Israel;
7ነገር ግን። በይስሐቅ ዘር ይጠራልሃል ተባለ።
7nor because they are seed of Abraham [are] all children, but — `in Isaac shall a seed be called to thee;`
8ይህም፥ የተስፋ ቃል ልጆች ዘር ሆነው ይቆጠራሉ እንጂ እነዚህ የሥጋ ልጆች የሆኑ የእግዚአብሔር ልጆች አይደሉም ማለት ነው።
8that is, the children of the flesh — these [are] not children of God; but the children of the promise are reckoned for seed;
9ይህ። በዚህ ጊዜ እመጣለሁ ለሳራም ልጅ ይሆንላታል የሚል የተስፋ ቃል ነውና።
9for the word of promise [is] this; `According to this time I will come, and there shall be to Sarah a son.`
10ይህ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ርብቃ ደግሞ ከአንዱ ከአባታችን ከይስሐቅ በፀነሰች ጊዜ፥
10And not only [so], but also Rebecca, having conceived by one — Isaac our father —
11ልጆቹ ገና ሳይወለዱ፥ በጎ ወይም ክፉ ምንም ሳያደርጉ፥ ከጠሪው እንጂ ከሥራ ሳይሆን በምርጫ የሚሆን የእግዚአብሔር አሳብ ይጸና ዘንድ፥
11(for they being not yet born, neither having done anything good or evil, that the purpose of God, according to choice, might remain; not of works, but of Him who is calling,) it was said to her —
12ለእርስዋ። ታላቁ ለታናሹ ይገዛል ተባለላት።
12`The greater shall serve the less;`
13ያዕቆብን ወደድሁ ኤሳውን ግን ጠላሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።
13according as it hath been written, `Jacob I did love, and Esau I did hate.`
14እንግዲህ ምን እንላለን? በእግዚአብሔር ዘንድ ዓመፃ አለ ወይ? አይደለም።
14What, then, shall we say? unrighteousness [is] with God? let it not be!
15ለሙሴ። የምምረውን ሁሉ እምረዋለሁ ለምራራለትም ሁሉ እራራለታለሁ ይላልና።
15for to Moses He saith, `I will do kindness to whom I do kindness, and I will have compassion on whom I have compassion;`
16እንግዲህ ምሕረት ለወደደ ወይም ለሮጠ አይደለም፥ ከሚምር ከእግዚአብሔር ነው እንጂ።
16so, then — not of him who is willing, nor of him who is running, but of God who is doing kindness:
17መጽሐፍ ፈርዖንን። ኃይሌን በአንተ አሳይ ዘንድ ስሜም በምድር ሁሉ ይነገር ዘንድ ለዚህ አስነሣሁህ ይላልና።
17for the Writing saith to Pharaoh — `For this very thing I did raise thee up, that I might shew in thee My power, and that My name might be declared in all the land;`
18እንግዲህ የሚወደውን ይምረዋል፥ የሚወደውንም እልከኛ ያደርገዋል።
18so, then, to whom He willeth, He doth kindness, and to whom He willeth, He doth harden.
19እንግዲህ ስለ ምን እስከ አሁን ድረስ ይነቅፋል? ፈቃዱንስ የሚቃወም ማን ነው? ትለኝ ይሆናል።
19Thou wilt say, then, to me, `Why yet doth He find fault? for His counsel who hath resisted?`
20ነገር ግን፥ አንተ ሰው ሆይ፥ ለእግዚአብሔር የምትመልስ ማን ነህ? ሥራ ሠሪውን። ስለ ምን እንዲህ አድርገህ ሠራኸኝ ይለዋልን?
20nay, but, O man, who art thou that art answering again to God? shall the thing formed say to Him who did form [it], Why me didst thou make thus?
21ወይም ሸክላ ሠሪ ከአንዱ ጭቃ ክፍል አንዱን ዕቃ ለክብር አንዱንም ለውርደት ሊሠራ በጭቃ ላይ ሥልጣን የለውምን?
21hath not the potter authority over the clay, out of the same lump to make the one vessel to honour, and the one to dishonour?
22ነገር ግን እግዚአብሔር ቍጣውን ሊያሳይ ኃይሉንም ሊገልጥ ወዶ፥ አስቀድሞ ለክብር ባዘጋጃቸው በምሕረት ዕቃዎች ላይ የክብሩን ባለ ጠግነት ይገልጥ ዘንድ፥ ለጥፋት የተዘጋጁትን የቁጣ ዕቃዎች በብዙ ትዕግሥት ከቻለ፥ እንዴት ነው?
22And if God, willing to shew the wrath and to make known His power, did endure, in much long suffering, vessels of wrath fitted for destruction,
24የምሕረቱ ዕቃዎችም ከአይሁድ ብቻ አይደሉም፥ ነገር ግን ከአሕዛብ ደግሞ የጠራን እኛ ነን።
23and that He might make known the riches of His glory on vessels of kindness, that He before prepared for glory, whom also He did call — us —
25እንዲሁ ደግሞ በሆሴዕ። ሕዝቤ ያልሆነውን ሕዝቤ ብዬ፥ ያልተወደደችውንም የተወደደችው ብዬ እጠራለሁ፤
24not only out of Jews, but also out of nations,
26እናንተ ሕዝቤ አይደላችሁም በተባለላቸውም ስፍራ በዚያ የሕያው እግዚአብሔር ልጆች ተብለው ይጠራሉ ይላል።
25as also in Hosea He saith, `I will call what [is] not My people — My people; and her not beloved — Beloved,
27ኢሳይያስም። የእስራኤል ልጆች ቁጥር ምንም እንደ ባሕር አሸዋ ቢሆን ቅሬታው ይድናል፤ ጌታ ነገሩን ፈጽሞና ቆርጦ በምድር ላይ ያደርገዋልና ብሎ ስለ እስራኤል ይጮኻል።
26and it shall be — in the place where it was said to them, Ye [are] not My people; there they shall be called sons of the living God.`
29ኢሳይያስም እንደዚሁ። ጌታ ፀባዖት ዘር ባላስቀረልን እንደ ሰዶም በሆንን ገሞራንም በመሰልን ነበር ብሎ አስቀድሞ ተናገረ።
27And Isaiah doth cry concerning Israel, `If the number of the sons of Israel may be as the sand of the sea, the remnant shall be saved;
30እንግዲህ ምን እንላለን? ጽድቅን ያልተከተሉት አሕዛብ ጽድቅን አገኙ፥ እርሱ ግን ከእምነት የሆነ ጽድቅ ነው፤
28for a matter He is finishing, and is cutting short in righteousness, because a matter cut short will the Lord do upon the land.
31እስራኤል ግን የጽድቅን ሕግ እየተከተሉ ወደ ሕግ አልደረሱም።
29and according as Isaiah saith before, `Except the Lord of Sabaoth did leave to us a seed, as Sodom we had become, and as Gomorrah we had been made like.`
32ይህስ ስለ ምንድር ነው? በሥራ እንጂ በእምነት ጽድቅን ስላልተከተሉ ነው፤ እነሆ፥ በጽዮን የእንቅፋት ድንጋይና የማሰናከያ ዓለት አኖራለሁ በእርሱም የሚያምን አያፍርም ተብሎ እንደ ተጻፈ በእንቅፋት ድንጋይ ተሰናከሉ።
30What, then, shall we say? that nations who are not pursuing righteousness did attain to righteousness, and righteousness that [is] of faith,
31and Israel, pursuing a law of righteousness, at a law of righteousness did not arrive;
32wherefore? because — not by faith, but as by works of law; for they did stumble at the stone of stumbling,
33according as it hath been written, `Lo, I place in Sion a stone of stumbling and a rock of offence; and every one who is believing thereon shall not be ashamed.`