1እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ።
1所以,你們既然與基督一同復活,就應當尋求天上的事,那裡有基督坐在 神的右邊。
2በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም።
2你們要思念的,是天上的事,不是地上的事。
3ሞታችኋልና፥ ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና።
3因為你們已經死了,你們的生命與基督一同隱藏在 神裡面。
4ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ፥ በዚያን ጊዜ እናንተ ደግሞ ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ።
4基督就是你們的生命,他顯現的時候,你們也要和他一同在榮耀裡顯現。
5እንግዲህ በምድር ያሉቱን ብልቶቻችሁን ግደሉ፥ እነዚህም ዝሙትና ርኵሰት ፍትወትም ክፉ ምኞትም ጣኦትንም ማምለክ የሆነ መጎምጀት ነው።
5所以要治死你們在地上的肢體,就如淫亂、污穢、邪情、惡慾和貪心,貪心就是拜偶像。
6በእነዚህም ጠንቅ የእግዚአብሔር ቍጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ ይመጣል።
6因著這些事, 神的忿怒必要臨到悖逆的人(有些抄本無“悖逆的人”)。
7እናንተም ደግሞ ትኖሩባቸው በነበራችሁ ጊዜ፥ በፊት በእነዚህ ተመላለሳችሁ።
7你們從前在其中生活的時候,也曾經這樣行過。
8አሁን ግን እናንተ ደግሞ ቍጣንና ንዴትን ክፋትንም፥ ከአፋችሁም ስድብን የሚያሳፍርንም ንግግር እነዚህን ሁሉ አስወግዱ።
8但現在你們要除去忿怒、惱怒、惡毒、毀謗,以及粗言穢語這一切事。
9እርስ በርሳችሁ ውሸት አትነጋገሩ፥ አሮጌውን ሰው ከሥራው ጋር ገፋችሁታልና፥
9不要彼此說謊,因為你們已經脫去了舊人和舊人的行為,
10የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል።
10穿上了新人。這新人照著他的創造者的形象漸漸更新,能夠充分認識主。
11በዚያም የግሪክ ሰው አይሁዳዊም የተገረዘም ያልተገረዘም አረማዊም እስኩቴስም ባሪያም ጨዋ ሰውም መሆን አልተቻለም፥ ነገር ግን ክርስቶስ ሁሉ ነው፥ በሁሉም ነው።
11在這一方面,並不分希臘人和猶太人,受割禮的和未受割禮的,未開化的人和西古提人,奴隸和自由人,唯有基督是一切,也在一切之內。
12እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ።
12所以,你們既然是 神所揀選的,是聖潔、蒙愛的人,就要存憐憫的心腸、恩慈、謙卑、溫柔和忍耐。
13እርስ በርሳችሁ ትዕግሥትን አድርጉ፥ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው፥ ይቅር ተባባሉ። ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ።
13如果有人對別人有嫌隙,總要彼此寬容,互相饒恕;主怎樣饒恕了你們,你們也要照樣饒恕人。
14በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት።
14在這一切之上,還要有愛心,愛心是聯繫全德的。
15በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ። የምታመሰግኑም ሁኑ።
15又要讓基督的平安在你們心裡作主;你們蒙召歸為一體,也是為了這個緣故。你們要有感謝的心。
16የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ። በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ። በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ።
16你們要讓基督的道豐豐富富地住在你們心裡,以各樣的智慧,彼此教導,互相勸戒,用詩章、聖詩、靈歌,懷著感恩的心歌頌 神。
17እግዚአብሔር አብን በእርሱ እያመሰገናችሁ፥ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት።
17凡你們所作的,無論是言語或行為,都要奉主耶穌的名,藉著他感謝父 神。
18ሚስቶች ሆይ፥ በጌታ እንደሚገባ ለባሎቻችሁ ተገዙ።
18過新人的生活你們作妻子的,要順服丈夫,這在主裡是合宜的。
19ባሎች ሆይ፥ ሚስቶቻችሁን ውደዱ መራራም አትሁኑባቸው።
19你們作丈夫的,要愛妻子,不可苦待她們。
20ልጆች ሆይ፥ ይህ ለጌታ ደስ የሚያሰኝ ነውና በሁሉ ለወላጆቻችሁ ታዘዙ።
20你們作兒女的,要凡事聽從父母,因為這在主裡是可喜悅的。
21አባቶች ሆይ፥ ልባቸው እንዳይዝል ልጆቻችሁን አታበሳጩአቸው።
21你們作父親的,不要激怒兒女,免得他們灰心喪志。
22ባሪያዎች ሆይ፥ በቅን ልብ ጌታን እየፈራችሁ እንጂ፥ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ ሳትሆኑ፥ በሥጋ ጌቶቻችሁ ለሆኑ በሁሉ ታዘዙ።
22你們作僕人的,要凡事聽從世上的主人,作事不要只作給人看,像那些討人歡心的一樣,卻要以真誠的心敬畏主。
23ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉ፥ የምታደርጉትን ሁሉ በትጋት አድርጉት፥
23無論你們作甚麼,都要從心裡去作,像是為主作的,不是為人作的,
24ከጌታ የርስትን ብድራት እንድትቀበሉ ታውቃላችሁና። የምታገለግሉት ጌታ ክርስቶስ ነውና።
24因為你們知道,你們一定會從主那裡得到基業為賞賜。你們應當服事主基督,
25የሚበድልም የበደለውን በብድራት ይቀበላል፥ ለሰው ፊትም አድልዎ የለም።
25但那些不義的人,必按他所行的不義受報應。主並不偏待人。