Amharic: New Testament

聖經新譯本

John

1

1በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።
1道成肉身太初有道,道與 神同在,道就是 神。
2ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ።
2這道太初與 神同在。
3ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም።
3萬有是藉著他造的;凡被造的,沒有一樣不是藉著他造的。
4በእርሱ ሕይወት ነበረች፥ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረች።
4在他裡面有生命,(有些抄本第3、4節或譯:“萬有是藉著他造的,沒有一樣不是藉著他造的;凡被造的,都在他裡面有生命……”)這生命就是人的光。
5ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም።
5光照在黑暗中,黑暗不能勝過光。
6ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤
6有一個人,名叫約翰,是 神所差來的。
7ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምኑ ይህ ስለ ብርሃን ይመሰክር ዘንድ ለምስክር መጣ።
7他來是要作見證,就是為光作見證,使眾人藉著他可以相信。
8ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ እንጂ፥ እርሱ ብርሃን አልነበረም።
8他不是那光,而是要為那光作見證。
9ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ይመጣ ነበር።
9那光來到世界,是普照世人的真光。
10በዓለም ነበረ፥ ዓለሙም በእርሱ ሆነ፥ ዓለሙም አላወቀውም።
10他在世界,世界也是藉著他造的,世界卻不認識他。
11የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም።
11他到自己的地方來,自己的人卻不接受他。
12ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤
12凡接受他的,就是信他名的人,他就賜給他們權利,成為 神的兒女。
13እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።
13他們不是從血統生的,不是從肉身的意思生的,也不是從人意生的,而是從 神生的。
14ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።
14道成了肉身,住在我們中間,滿有恩典和真理。我們見過他的榮光,正是從父而來的獨生子的榮光。
15ዮሐንስ ስለ እርሱ መሰከረ እንዲህም ብሎ ጮኸ። ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ከእኔ በፊት ነበረና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል፤ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነበረ።
15約翰為他作見證,大聲說:“這一位就是我所說的:‘那在我以後來的,位分比我高,因為他本來是在我以前的。’”
16እኛ ሁላችን ከሙላቱ ተቀብለን በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጥቶናልና ሕግ በሙሴ ተሰጥቶ ነበርና፤
16從他的豐盛裡我們都領受了,而且恩上加恩。
17ጸጋና እውነት ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ሆነ።
17律法是藉著摩西頒布的,恩典和真理卻是藉著耶穌基督而來的。
18መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው።
18從來沒有人見過 神,只有在父懷裡的獨生子把他彰顯出來。
19አይሁድም። አንተ ማን ነህ? ብለው ይጠይቁት ዘንድ ከኢየሩሳሌም ካህናትንና ሌዋውያንን በላኩበት ጊዜ፥ የዮሐንስ ምስክርነት ይህ ነው።
19施洗約翰的見證(太3:1~12;可1:1~8;路3:1~18)以下是約翰的見證:猶太人從耶路撒冷派祭司和利未人到約翰那裡,問他:“你是誰?”
20መሰከረም አልካደምም፤ እኔ ክርስቶስ አይደለሁም ብሎ መሰከረ።
20約翰並不否認,坦白地承認說:“我不是基督。”
21እንኪያስ ማን ነህ? ኤልያስ ነህን? ብለው ጠየቁት። አይደለሁም አለ። ነቢዩ ነህን? አይደለሁም ብሎ መለሰ።
21他們又問:“那麼你是誰?是以利亞嗎?”他說:“我不是。”“是那位先知嗎?”他回答:“不是。”
22እንኪያስ። ማን ነህ? ለላኩን መልስ እንድንሰጥ፤ ስለራስህ ምን ትላለህ? አሉት።
22於是他們再問:“你是誰?好讓我們回覆派我們來的人。你說你自己是誰?”
23እርሱም። ነቢዩ ኢሳይያስ እንዳለ። የጌታን መንገድ አቅኑ ብሎ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ እኔ ነኝ አለ።
23他說:“我就是在曠野呼喊者的聲音:‘修直主的路!’正如以賽亞先知所說的。”
24የተላኩትም ከፈሪሳውያን ነበሩና። እንኪያስ አንተ ክርስቶስ ወይም ኤልያስ ወይም ነቢዩ ካይደለህ፥ ስለ ምን ታጠምቃለህ? ብለው ጠየቁት።
24這些人是法利賽人派來的。
26ዮሐንስ መልሶ። እኔ በውኃ አጠምቃለሁ፤ ዳሩ ግን እናንተ የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሞአል፤
25他們問約翰:“你既然不是基督,不是以利亞,也不是那位先知,那麼你為甚麼施洗呢?”
27እኔ የጫማውን ጠፍር ልፈታ የማይገባኝ፥ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ከእኔ ይልቅ የሚከብር ይህ ነው አላቸው።
26約翰回答:“我是用水施洗,但有一位站在你們中間,是你們不認識的;
28ይህ ነገር ዮሐንስ ያጠምቅበት በነበረው በዮርዳኖስ ማዶ በቢታንያ በቤተ ራባ ሆነ።
27他是在我以後來的,我就是給他解鞋帶也不配。”
29በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ። እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።
28這些事發生在約旦河東的伯大尼,約翰施洗的地方。
30አንድ ሰው ከእኔ በኋላ ይመጣል፥ ከእኔም በፊት ነበርና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል ብዬ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነው።
29 神的羊羔第二天,約翰見耶穌迎面而來,就說:“看哪, 神的羊羔,是除去世人的罪孽的!
31እኔም አላውቀውም ነበር፥ ዳሩ ግን ለእስራኤል ይገለጥ ዘንድ ስለዚህ በውኃ እያጠመቅሁ እኔ መጣሁ።
30這一位就是我所說的:‘有一個人,是在我以後來的,位分比我高,因為他本來是在我以前的。’
32ዮሐንስም እንዲህ ብሎ መሰከረ። መንፈስ ከሰማይ እንደ ርግብ ሆኖ ሲወርድ አየሁ፤ በእርሱ ላይም ኖረ።
31我本來不認識他,但為了要把他顯明給以色列人,因此我來用水施洗。”
33እኔም አላውቀውም ነበር፥ ዳሩ ግን በውኃ አጠምቅ ዘንድ የላከኝ እርሱ። መንፈስ ሲወርድበትና ሲኖርበት የምታየው፥ በመንፈስ ቅዱስ የሚያጠምቅ እርሱ ነው አለኝ።
32約翰又作見證說:“我曾看見聖靈,好像鴿子從天上降下來,停留在他的身上。
34እኔም አይቻለሁ እርሱም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ መስክሬአለሁ።
33我本來不認識他,但那差我來用水施洗的對我說:‘你看見聖靈降下來,停留在誰身上,誰就是用聖靈施洗的。’
35በነገው ደግሞ ዮሐንስ ከደቀ መዛሙርቱም ሁለት ቆመው ነበር፥
34我看見了,就作見證說:‘這就是 神的兒子。’”
36ኢየሱስም ሲሄድ ተመልክቶ። እነሆ የእግዚአብሔር በግ አለ።
35呼召第一批門徒(太4:18~22;可1:16~20;路5:2~11)過了一天,約翰和他的兩個門徒又站在那裡。
37ሁለቱም ደቀ መዛሙርት ሲናገር ሰምተው ኢየሱስን ተከተሉት።
36約翰看見耶穌走過的時候,就說:“看哪, 神的羊羔!”
38ኢየሱስም ዘወር ብሎ ሲከተሉትም አይቶ። ምን ትፈልጋላችሁ? አላቸው። እነርሱም። ረቢ፥ ወዴት ትኖራለህ? አሉት፤ ትርጓሜው መምህር ሆይ ማለት ነው።
37那兩個門徒聽見他的話,就跟從了耶穌。
40መጥታችሁ እዩ አላቸው። መጥተው የሚኖርበትን አዩ፥ በዚያም ቀን በእርሱ ዘንድ ዋሉ፤ አሥር ሰዓት ያህል ነበረ።
38耶穌轉過身來,看見他們跟著,就問:“你們要甚麼?”他們說:“拉比,你在哪裡住?”(“拉比”的意思就是“老師”。)
41ከዮሐንስ ዘንድ ሰምተው ከተከተሉት ከሁለቱ አንዱ የስምዖን ጴጥሮስ ወንድም እንድርያስ ነበረ።
39他說:“你們來看吧!”於是他們就去看他所住的地方。那一天他們就和耶穌住在一起;那時大約是下午四點鐘。
42እርሱ አስቀድሞ የራሱን ወንድም ስምዖንን አገኘውና። መሢሕን አግኝተናል አለው፤ ትርጓሜውም ክርስቶስ ማለት ነው።
40聽了約翰的話而跟從耶穌的那兩個人,一個是西門.彼得的弟弟安得烈。
43ወደ ኢየሱስም አመጣው። ኢየሱስም ተመልክቶ። አንተ የዮና ልጅ ስምዖን ነህ፤ አንተ ኬፋ ትባላለህ አለው፤ ትርጓሜው ጴጥሮስ ማለት ነው።
41他先找到自己的哥哥西門,告訴他:“我們遇見彌賽亞了!”(“彌賽亞”的意思就是“基督”。)
44በነገው ኢየሱስ ወደ ገሊላ ሊወጣ ወደደ፥ ፊልጶስንም አገኘና። ተከተለኝ አለው።
42安得烈就帶他到耶穌那裡。耶穌定睛看著他,說:“你是約翰的兒子西門,你要稱為磯法。”(“磯法”翻譯出來就是“彼得”。)
45ፊልጶስም ከእንድርያስና ከጴጥሮስ ከተማ ከቤተ ሳይዳ ነበረ።
43呼召腓力和拿但業再過一天,耶穌決定往加利利去;他遇見腓力,就對他說:“來跟從我!”
46ፊልጶስ ናትናኤልን አግኝቶ። ሙሴ በሕግ ነቢያትም ስለ እርሱ የጻፉትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል አለው።
44腓力是伯賽大人,與安得烈和彼得同鄉。
47ናትናኤልም። ከናዝሬት መልካም ነገር ሊወጣ ይችላልን? አለው። ፊልጶስ። መጥተህ እይ አለው።
45腓力找到拿但業,告訴他:“摩西在律法書上所寫的,和眾先知所記的那位,我們已經遇見了,他就是約瑟的兒子拿撒勒人耶穌。”
48ኢየሱስ ናትናኤልን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ። ተንኰል የሌለበት በእውነት የእስራኤል ሰው እነሆ አለ።
46拿但業說:“拿撒勒還能出甚麼好的嗎?”腓力說:“你來看!”
49ናትናኤልም። ከወዴት ታውቀኛለህ? አለው። ኢየሱስም መልሶ። ፊልጶስ ሳይጠራህ፥ ከበለስ በታች ሳለህ፥ አየሁህ አለው።
47耶穌看見拿但業向他走過來,就論到他說:“看哪,這的確是個以色列人,他心裡沒有詭詐。”
50ናትናኤልም መልሶ። መምህር ሆይ፥ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ፤ አንተ የእስራኤል ንጉሥ ነህ አለው።
48拿但業問他:“你怎麼認識我呢?”耶穌回答:“腓力還沒有招呼你,你在無花果樹下的時候,我就看見你了。”
51ኢየሱስም መልሶ። ከበለስ በታች አየሁህ ስላልሁህ አመንህን? ከዚህ የሚበልጥ ነገር ታያለህ አለው።
49拿但業說:“拉比,你是 神的兒子,你是以色列的王!”
52እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይ ሲከፈት የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ አለው።
50耶穌說:“因為我告訴你‘我看見你在無花果樹下’,你就信了嗎?你還要看見比這些更大的事。”
51又對他說:“我實實在在告訴你們,你們要看見天開了, 神的眾使者在人子的身上,上去下來。”