1ኢየሱስም ከፋሲካ በዓል በፊት፥ ከዚህ ዓለም ወደ አብ የሚሄድበት ሰዓት እንደ ደረሰ አውቆ፥ በዚህ ዓለም ያሉትን ወገኖቹን የወደዳቸውን እስከ መጨረሻ ወደዳቸው።
1耶穌為門徒洗腳逾越節以前,耶穌知道自己離開這世界回到父那裡去的時候到了。他既然愛世上屬於自己的人,就愛他們到底。
2እራትም ሲበሉ ዲያብሎስ በስምዖን ልጅ በአስቆሮቱ በይሁዳ ልብ አሳልፎ እንዲሰጠው አሳብ ካገባ በኋላ፥
2吃晚飯的時候(魔鬼已經把出賣耶穌的意念放在西門的兒子加略人猶大的心裡),
3ኢየሱስ አብ ሁሉን በልጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥
3耶穌知道父已經把萬有交在他手中,並且知道自己從 神而來,又要回到 神那裡去,
4ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤
4就起身離席,脫去外衣,拿一條手巾束腰。
5በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።
5然後他倒了一盆水,洗門徒的腳,並且用束腰的手巾擦乾。
6ወደ ስምዖን ጴጥሮስም መጣ፤ እርሱም። ጌታ ሆይ፥ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን? አለው።
6輪到西門.彼得,彼得就說:“主啊,你要洗我的腳嗎?”
7ኢየሱስም መልሶ። እኔ የማደርገውን አንተ አሁን አታውቅም፥ በኋላ ግን ታስተውለዋለህ አለው።
7耶穌回答:“我所作的,你現在不知道,以後就會明白。”
8ጴጥሮስም። የእኔን እግር ለዘላለም አታጥብም አለው። ኢየሱስም። ካላጠብሁህ፥ ከእኔ ጋር ዕድል የለህም ብሎ መለሰለት።
8彼得說:“不行,你千萬不可洗我的腳!”耶穌說:“如果我不洗你的腳,你就與我沒有關係了。”
9ስምዖን ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም አለው።
9西門.彼得說:“主啊,那就不單洗我的腳,連我的手和頭都洗吧!”
10ኢየሱስም። የታጠበ እግሩን ከመታጠብ በቀር ሌላ አያስፈልገውም፥ ሁለንተናው ግን ንጹሕ ነው፤ እናንተም ንጹሐን ናችሁ፥ ነገር ግን ሁላችሁ አይደላችሁም አለው።
10耶穌說:“洗過澡的人,全身都潔淨,只需要洗腳就可以了。你們是潔淨的,但不是人人都是這樣。”
11አሳልፎ የሚሰጠውን ያውቅ ነበርና፤ ስለዚህ። ሁላችሁ ንጹሐን አይደላችሁም አለው።
11原來耶穌知道誰要出賣他,所以他說“你們不是人人都是潔淨的”。
12እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥ እንዲህም አላቸው። ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?
12耶穌洗完了門徒的腳,就穿上外衣,再坐下來,對他們說:“我給你們作的,你們明白嗎?
13እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ።
13你們稱呼我‘老師,主’,你們說得對,我本來就是。
14እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል።
14我是主,是老師,尚且洗你們的腳,你們也應當彼此洗腳。
15እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና።
15我作了你們的榜樣,是要你們也照著我所作的去行。
16እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም። መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም።
16我實實在在告訴你們,僕人不能大過主人,奉差遣的也不能大過差他的人。
17ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ።
17你們既然知道這些事,如果去實行,就有福了。
18ስለ ሁላችሁ አልናገርም፤ እኔ የመረጥኋቸውን አውቃለሁ፤ ነገር ግን መጽሐፍ። እንጀራዬን የሚበላ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣብኝ ያለው ይፈጸም ዘንድ ነው።
18我這話不是指著你們全體說的;我認識我所揀選的人,但是經上的話:‘那吃我飯的,用他的腳踢我’,必須應驗。
19በሆነ ጊዜ እኔ እንደ ሆንሁ ታምኑ ዘንድ፥ ከአሁን ጀምሬ አስቀድሞ ሳይሆን እነግራችኋለሁ።
19現在,事情還沒有發生,我就告訴你們,使你們到時可以信我就是‘那一位’。
20እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ማናቸውን የምልከውን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።
20我實實在在告訴你們,那接待我所差遣的,就是接待我;接待我的,就是接待那差我來的。”
21ኢየሱስ ይህን ብሎ በመንፈሱ ታወከ መስክሮም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ከእናንተ አንዱ አሳልፎ ይሰጠኛል አለ።
21耶穌預言要被人出賣(太26:20~25;可14:17~21;路22:21~23)耶穌說了這話,心裡很難過,就明明地說:“我實實在在告訴你們,你們中間有一個人要出賣我。”
22ደቀ መዛሙርቱ ስለ ማን እንደ ተናገረ አመንትተው እርስ በርሳቸው ተያዩ።
22門徒面面相覷,不知道他是指著誰說的。
23ኢየሱስም ይወደው የነበረ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ በኢየሱስ ደረት ላይ ተጠጋ፤
23門徒中有一個人,是耶穌所愛的,他坐在耶穌旁邊。
24ስለዚህ ስምዖን ጴጥሮስ እርሱን ጠቅሶ። ስለማን እንደ ተናገረ ንገረን አለው።
24西門.彼得向他示意,叫他問耶穌是指著誰說的。
25እርሱም በኢየሱስ ደረት እንዲህ ተጠግቶ። ጌታ ሆይ፥ ማን ነው? አለው።
25於是那個門徒貼近耶穌的胸懷,問他:“主啊,是誰呢?”
26ኢየሱስም። እኔ ቍራሽ አጥቅሼ የምሰጠው እርሱ ነው ብሎ መለሰለት። ቍራሽም አጥቅሶ ለአስቆሮቱ ለስምዖን ልጅ ለይሁዳ ሰጠው።
26耶穌回答:“我蘸一小塊餅給誰,誰就是了。”於是他蘸了一小塊餅,遞給加略人西門的兒子猶大。
27ቍራሽም ከተቀበለ በኋላ ያን ጊዜ ሰይጣን ገባበት። እንግዲህ ኢየሱስ። የምታደርገውን ቶሎ ብለህ አድርግ አለው።
27猶大接過餅以後,撒但就進入他的心。耶穌對他說:“你要作的,快去作吧。”
28ነገር ግን ከተቀመጡት ስለ ምን ይህን እንዳለው ማንም አላወቀም፤
28在座的人,沒有一個知道耶穌為甚麼對猶大說這話。
29ይሁዳ ከረጢቱን የያዘ ስለ ሆነ፥ ኢየሱስ። ለበዓሉ የሚያስፈልገንን ግዛ፥ ወይም ለድሆች ምጽዋት እንዲሰጥ ያለው ለአንዳንዱ መስሎአቸው ነበርና።
29猶大是管錢的,所以有人以為耶穌叫他去買過節用的東西,或是吩咐他拿點東西去賙濟窮人。
30እርሱም ቍራሹን ከተቀበለ በኋላ ወዲያው ወጣ፤ ሌሊትም ነበረ።
30猶大吃了餅,立刻就出去;那時是黑夜了。
31ከወጣም በኋላ ኢየሱስ እንዲ አለ። አሁን የሰው ልጅ ከበረ እግዚአብሔርም ሰለ እርሱ ከበረ፤
31吩咐門徒要彼此相愛他出去以後,耶穌就說:“現在人子得了榮耀, 神也在人子身上得了榮耀,
32እግዚአብሔር ስለ እርሱ የከበረ ከሆነ፥ እግዚአብሔር ደግሞ እርሱን ራሱን ያከብረዋል ወዲያውም ያከብረዋል።
32( 神既然在人子身上得了榮耀,)(有些抄本無此句)也要在自己身上榮耀人子,並且要立刻榮耀他。
33ልጆች ሆይ፥ ገና ጥቂት ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ፤ ትፈልጉኛላችሁ፤ ለአይሁድም። እኔ ወደምሄድበት እናንተ ልትመጡ አይቻላችሁም እንዳልኋቸው፥ አሁን ለእናንተ ደግሞ እላችኋለሁ።
33孩子們啊,我跟你們在一起的時候不多了。你們要尋找我,但是我對猶太人說過,現在也照樣對你們說:‘我去的地方,是你們不能去的。’
34እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ፥ እንደ ወደድኋችሁ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ።
34我給你們一條新命令,就是要你們彼此相愛;我怎樣愛你們,你們也要怎樣彼此相愛。
35እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ።
35如果你們彼此相愛,眾人就會認出你們是我的門徒了。”
36ስምዖን ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ ወዴት ትሄዳለህ? አለው። ኢየሱስም። ወደምሄድበት አሁን ልትከተለኝ አትችልም፥ ነገር ግን በኋላ ትከተለኛለህ ብሎ መለሰለት።
36預言彼得不認主(太26:33~35;可14:29~31;路22:33~34)西門.彼得對耶穌說:“主啊,你往哪裡去?”耶穌回答:“我去的地方,你現在不能跟著我去,但後來卻要跟著我去。”
37ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ አሁን ልከተልህ አለመቻሌ ስለ ምንድር ነው? ነፍሴን ስንኳ ስለ አንተ እሰጣለሁ አለው።
37彼得說:“主啊,為甚麼我現在不能跟著你去?為了你,我捨命也願意!”
38ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰለት። ነፍስህን ስለ እኔ ትሰጣለህን? እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዶሮ አይጮኽም።
38耶穌說:“你願意為我捨命嗎?我實實在在告訴你,雞叫之前,你必定三次不認我。”