Amharic: New Testament

聖經新譯本

John

19

1በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው።
1那時,彼拉多吩咐人把耶穌拉去鞭打。
2ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ አኖሩ ቀይ ልብስም አለበሱት፤
2士兵用荊棘編成冠冕,戴在他的頭上,又給他披上紫色的外袍,
3እየቀረቡም። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ይሉት ነበር፤
3然後來到他面前,說:“猶太人的王萬歲!”並且用手掌打他。
4በጥፊም ይመቱት ነበር። ጲላጦስም ደግሞ ወደ ውጭ ወጥቶ። እነሆ፥ አንዲት በደል ስንኳ እንዳላገኘሁበት ታውቁ ዘንድ እርሱን ወደ ውጭ አወጣላችኋለሁ አላቸው።
4彼拉多再次出到外面,對猶太人說:“看!我把他帶出來給你們,讓你們知道我查不出他有甚麼罪。”
5ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ።
5於是耶穌出來,戴著荊棘的冠冕,披著紫色的外袍。彼拉多對他們說:“看,這個人!”
6ጲላጦስም። እነሆ ሰውዬው አላቸው። የካህናት አለቆችና ሎሌዎች ባዩትም ጊዜ። ስቀለው ስቀለው እያሉ ጮኹ። ጲላጦስም። እኔስ አንዲት በደል ስንኳ አላገኘሁበትምና እናንተ ወስዳችሁ ስቀሉት አላቸው።
6祭司長和差役看見耶穌,就喊叫說:“把他釘十字架!把他釘十字架!”彼拉多對他們說:“你們自己把他帶去釘十字架吧!我查不出他有甚麼罪。”
7አይሁድም መልሰው። እኛ ሕግ አለን፥ እንደ ሕጋችንም ሊሞት ይገባዋል፥ ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ አድርጎአልና አሉት።
7猶太人回答:“我們有律法,根據那律法,他是該死的,因為他自命為 神的兒子。”
8ስለዚህ ጲላጦስ ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እግጅ ፈራ፤
8彼拉多聽見這話,就更加害怕,
9ተመልሶም ወደ ገዡ ግቢ ገባና ኢየሱስን። አንተ ከወዴት ነህ? አለው። ኢየሱስ ግን አንድ እንኳ አልመለሰለትም።
9又進了官邸,問耶穌:“你究竟是從哪裡來的?”耶穌卻不回答他。
10ስለዚህ ጲላጦስ። አትነግረኝምን? ልሰቅልህ ሥልጣን እንዳለኝ ወይም ልፈታህ ሥልጣን እንዳለኝ አታውቅምን? አለው።
10彼拉多對他說:“你不對我說話嗎?你不知道我有權釋放你,也有權把你釘十字架嗎?”
11ኢየሱስም መልሶ። ከላይ ካልተሰጠህ በቀር በእኔ ላይ ምንም ሥልጣን ባልነበረህም፤ ስለዚህ ለአንተ አሳልፎ የሰጠኝ ኃጢአቱ የባሰ ነው አለው።
11耶穌說:“如果不是從天上給你權柄,你就無權辦我;因此,把我交給你的那人,罪更重了。”
12ከዚህ በኋላ ጲላጦስ ሊፈታው ፈለገ፤ ነገር ግን አይሁድ። ይህንስ ብትፈታው የቄሣር ወዳጅ አይደለህም፤ ራሱን ንጉሥ የሚያደርግ ሁሉ የቄሣር ተቃዋሚ ነው እያሉ ጮኹ።
12從那時起,彼拉多想釋放耶穌;可是猶太人卻喊叫說:“如果你釋放這個人,就不是凱撒的忠臣了。凡是自命為王的,就是與凱撒為敵。”
13ጲላጦስም ይህን ነገር ሰምቶ ኢየሱስን ወደ ውጭ አወጣው፥ በዕብራይስጥም ገበታ በተባለው ጸፍጸፍ በሚሉት ስፍራ በፍርድ ወንበር ተቀመጠ።
13彼拉多聽了這些話,就把耶穌帶到外面,到了一個名叫“鋪石地”(希伯來話叫加巴大)的地方,就在那裡開庭審問。
14ለፋሲካም የማዘጋጀት ቀን ነበረ፤ ስድስት ሰዓትም የሚያህል ነበረ፤ አይሁድንም። እነሆ ንጉሣችሁ አላቸው።
14那天是逾越節的預備日,約在正午的時候。彼拉多對猶太人說:“看,你們的王!”
15እነርሱ ግን። አስወግደው፥ አስወግደው፥ ስቀለው እያሉ ጮኹ። ጲላጦስም። ንጉሣችሁን ልስቀለውን? አላቸው። የካህናት አለቆችም። ከቄሣር በቀር ሌላ ንጉሥ የለንም ብለው መለሱለት።
15他們就喊叫起來:“除掉他!除掉他!把他釘十字架!”彼拉多問他們:“我可以把你們的王釘十字架嗎?”祭司長回答:“除了凱撒,我們沒有王!”
16ስለዚህ በዚያን ጊዜ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጣቸው።
16於是彼拉多把耶穌交給他們去釘十字架。
17ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ።
17耶穌被釘十字架(太27:33~44;可15:22~32;路23:33~43)他們把耶穌帶去了。耶穌自己背著十字架出來,到了一個名叫“髑髏”的地方,希伯來話叫各各他。
18በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ።
18他們就在那裡把耶穌釘在十字架上;和他一同釘十字架的,還有兩個人,一邊一個,耶穌在中間。
19ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤ ጽሕፈቱም። የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ የሚል ነበረ።
19彼拉多寫了一個牌子,放在十字架上頭,寫的是:“猶太人的王拿撒勒人耶穌。”
20ኢየሱስም የተሰቀለበት ስፍራ ለከተማ ቅርብ ነበረና ከአይሁድ ብዙዎች ይህን ጽሕፈት አነበቡት፤ በዕብራይስጥና በሮማይስጥ በግሪክም ተጽፎ ነበር።
20有許多猶太人念了這牌子上所寫的,因為耶穌釘十字架的地方離城不遠,而且那牌子是用希伯來文、拉丁文和希臘文寫的。
21ስለዚህ የአይሁድ ካህናት አለቆች ጲላጦስን። እርሱ። የአይሁድ ንጉስ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ አሉት።
21猶太人的祭司長對彼拉多說:“不要寫‘猶太人的王’,要寫‘這個人自稱:我是猶太人的王’。”
22ጲላጦስም። የጻፍሁትን ጽፌአለሁ ብሎ መለሰ።
22彼拉多說:“我所寫的,我已經寫了!”
23ጭፍሮችም ኢየሱስን በሰቀሉት ጊዜ ልብሶቹን ወስደው ለእያንዳንዱ ጭፍራ አንድ ክፍል ሆኖ በአራት ከፋፈሉት፤ እጀጠባቡን ደግሞ ወሰዱ። እጀ ጠባቡም ከላይ ጀምሮ ወጥ ሆኖ የተሠራ ነበረ እንጂ የተሰፋ አልነበረም።
23士兵把耶穌釘了十字架之後,就把他的衣服拿來,分成四分,每個兵一分。他們又拿他的內衣;這內衣是沒有縫的,是從上到下整件織成的。
24ስለዚህ እርስ በርሳቸው። ለማን እንዲሆን በእርሱ ዕጣ እንጣጣልበት እንጂ አንቅደደው ተባባሉ። ይህም። ልብሴን እርስ በርሳቸው ተከፋፈሉ በእጀ ጠባቤም ዕጣ ተጣጣሉበት የሚለው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው።
24因此,他們彼此說:“我們不要把它撕開,我們來抽籤吧,看看是誰的。”這就應驗了經上所說的:“他們分了我的外衣,又為我的內衣抽籤。”士兵果然這樣作了。
25ጭፍሮችም እንዲህ አደረጉ። ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ፥ የእናቱም እኅት፥ የቀለዮጳም ሚስት ማርያም፥ መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር።
25站在耶穌十字架旁邊的,有他母親和他母親的姊妹,還有高羅巴的妻子馬利亞,和抹大拉的馬利亞。
26ኢየሱስም እናቱን ይወደው የነበረውንም ደቀ መዝሙር በአጠገቡ ቆሞ ባየ ጊዜ እናቱን። አንቺ ሴት፥ እነሆ ልጅሽ አላት።
26耶穌看見母親,又看見他所愛的那門徒站在旁邊,就對母親說:“母親(“母親”原文作“婦人”),看!你的兒子。”
27ከዚህ በኋላ ደቀ መዝሙሩን። እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት።
27然後他對那門徒說:“看!你的母親。”從那時起,那門徒就把她接到自己的家裡去了。
28ከዚህ በኋላ ኢየሱስ አሁን ሁሉ እንደተፈጸመ አውቆ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ። ተጠማሁ አለ።
28耶穌死時的情形(太27:48、50;可15:36~37;路23:36)這事以後,耶穌知道一切都已經成就了,為了要使經上的話應驗,就說:“我渴了。”
29በዚያም ሆምጣጤ የሞላበት ዕቃ ተቀምጦ ነበር፤ እነርሱም ሆምጣጤውን በሰፍነግ ሞልተው በሁሶፕም አድርገው ወደ አፉ አቀረቡለት።
29在那裡有一個罈子,盛滿了酸酒,他們就拿海綿浸了酸酒,綁在牛膝草上,送到他的口裡。
30ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ። ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።
30耶穌嘗了那酸酒,說:“成了!”就低下頭,斷了氣。
31አይሁድም የማዘጋጀት ቀን ስለ ሆነ ያ ሰንበት ትልቅ ነበረና ሥጋቸው በሰንበት በመስቀል ላይ እንዳይኖር፥ ጭናቸውን ሰብረው እንዲያወርዱአቸው ጲላጦስን ለመኑት።
31因為那天是預備日,為了要避免屍體在安息日留在十字架上(因為那安息日是個重要的日子),猶太人就請求彼拉多打斷那些被釘十字架的人的腿,把他們拿下來。
32ጭፍሮችም መጥተው የፊተኛውን ጭን ከእርሱም ጋር የተሰቀለውን የሌላውን ጭን ሰበሩ፤
32於是士兵來了,把和耶穌一同釘十字架的那兩個人的腿都先後打斷了。
33ወደ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን እርሱ ፈጽሞ እንደ ሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም፤
33他們來到耶穌那裡,看見他已經死了,就沒有打斷他的腿。
34ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጎኑን በጦር ወጋው፤ ወዲያውም ደምና ውኃ ወጣ።
34但是有一個士兵用槍刺他的肋旁,立刻有血和水流出來。
35ያየውም መስክሮአል፤ ምስክሩም እውነት ነው፤ እናንተም ደግሞ ታምኑ ዘንድ እርሱ እውነት እንዲናገር ያውቃል።
35那看見這事的人已經作證了,他的見證是真實的,他也知道自己所說的是實在的,使你們也相信。
36ይህ የሆነ። ከእርሱ አጥንት አይሰበርም የሚል የመጽሐፉ ቃል እንዲፈጸም ነው።
36這些事的發生,是要應驗經上所說的:“他的骨頭,一根也不可折斷。”
37ደግሞም ሌላው መጽሐፍ። የወጉትን ያዩታል ይላል።
37另有一處經文說:“他們要仰望自己所刺的人。”
38ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ።
38耶穌葬在新墳墓裡(太27:57~61;可15:42~47;路23:50~56)這些事以後,有一個亞利馬太人約瑟來求彼拉多,要領耶穌的身體;他因為怕猶太人,就暗暗地作耶穌的門徒。彼拉多批准了,他便把耶穌的身體領去。
39ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ።
39從前夜間來見耶穌的尼哥德慕也來了,帶著沒藥和沉香混合的香料,約有三十二公斤。
40የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።
40他們領取了耶穌的身體,照著猶太人的葬禮的規例,用細麻布和香料把他裹好。
41በተሰቀለበትም ስፍራ አትክልት ነበረ፥ በአትክልቱም ማንም ገና ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበረ።
41在耶穌釘十字架的地方,有一個園子,園裡有一個新的墓穴,是從來沒有葬過人的。
42ስለዚህ መቃብሩ ቅርብ ነበረና ስለ አይሁድ ማዘጋጀት ቀን ኢየሱስን በዚያ አኖሩት።
42因為那天是猶太人的預備日,又因為那墓穴就在附近,他們就把耶穌葬在那裡。