Amharic: New Testament

聖經新譯本

John

20

1ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች።
1耶穌復活(太28:1~8;可16:1~8;路24:1~10)禮拜日清早,天還沒有亮的時候,抹大拉的馬利亞來到墓旁,看見石頭已經從墳墓移開了。
2እየሮጠችም ወደ ስምዖን ጴጥሮስና ኢየሱስ ይወደው ወደ ነበረው ወደ ሌላው ደቀ መዝሙር መጥታ። ጌታን ከመቃብር ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አናውቅም አለቻቸው።
2她就跑去見西門.彼得,和耶穌所愛的那個門徒,對他們說:“有人把主從墳墓裡搬走了,我們不知道他們把他放在哪裡。”
3ስለዚህ ጴጥሮስና ሌላው ደቀ መዝሙር ወጥተው ወደ መቃብሩ ሄዱ።
3彼得和那門徒就動身,到墳墓那裡去。
4ሁለቱም አብረው ሮጡ፤ ሌላው ደቀ መዝሙርም ከጴጥሮስ ይልቅ ፈጥኖ ወደ ፊት ሮጠና አስቀድሞ ከመቃብሩ ደረሰ፤
4兩個人一齊跑,那門徒比彼得跑得快,先到了墳墓,
5ዝቅም ብሎ ቢመለከት የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥ ነገር ግን አልገባም።
5屈身向裡面觀看,看見細麻布還在那裡,但他卻沒有進去。
6ስምዖን ጴጥሮስም ተከትሎት መጣ ወደ መቃብሩም ገባ፤ የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥
6西門.彼得隨後也到了;他進入墳墓,看見細麻布還放在那裡,
7ደግሞም በራሱ የነበረውን ጨርቅ ለብቻው በአንድ ስፍራ ተጠምጥሞ እንደ ነበረ እንጂ ከተልባ እግሩ ልብስ ጋር ተቀምጦ እንዳልነበረ አየ።
7也看見耶穌的裹頭巾,沒有和細麻布放在一起,而是捲著放在一邊。
8በዚያን ጊዜ አስቀድሞ ወደ መቃብር የመጣውም ሌላው ደቀ መዝሙር ደግሞ ገባ፥ አየም፥ አመነም፤
8那時,先到墳墓的那門徒也進去,他看見,就信了。
9ከሙታን ይነሣ ዘንድ እንዲገባው የሚለውን የመጽሐፉን ቃል ገና አላወቁም ነበርና።
9他們還不明白經上所說“他必須從死人中復活”這句話的意思。
10ደቀ መዛሙርቱም ወደ ቤታቸው ደግሞ ሄዱ።
10於是兩個門徒就回家去了。
11ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተ ውጭ ቆማ ነበር። ስታለቅስም ወደ መቃብር ዝቅ ብላ ተመለከተች፤
11向抹大拉的馬利亞顯現(太28:9~10;可16:9~11)馬利亞站在墳墓外面哭泣。她哭的時候,屈身往裡面觀看,
12ሁለት መላእክትም ነጭ ልብስ ለብሰው የኢየሱስ ሥጋ ተኝቶበት በነበረው አንዱ በራስጌ ሌላውም በእግርጌ ተቀምጠው አየች።
12看見兩個身穿白衣的天使,坐在安放耶穌身體的地方,一個在頭那邊,一個在腳那邊。
13እነርሱም። አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? አሉአት። እርስዋም። ጌታዬን ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አላውቅም አለቻቸው።
13天使問她:“婦人,你為甚麼哭?”她說:“有人把我的主搬走了,我不知道他們把他放在哪裡。”
14ይህንም ብላ ወደ ኋላ ዘወር ስትል ኢየሱስን ቆሞ አየችው፤ ኢየሱስም እንደ ሆነ አላወቀችም።
14馬利亞說了這話,就轉過身來,看見耶穌站在那裡,卻不知道他就是耶穌。
15ኢየሱስም። አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? ማንንስ ትፈልጊያለሽ? አላት። እርስዋም የአትክልት ጠባቂ መስሎአት። ጌታ ሆይ፥ አንተ ወስደኸው እንደ ሆንህ ወዴት እንዳኖርኸው ንገረኝ እኔም እወስደዋለሁ አለችው።
15耶穌對她說:“婦人,你為甚麼哭?你找誰呢?”馬利亞以為耶穌是園丁,就對他說:“先生,如果是你把他挪去了,請告訴我你把他放在甚麼地方,我好去搬回來。”
16ኢየሱስም። ማርያም አላት። እርስዋ ዘወር ብላ በዕብራይስጥ። ረቡኒ አለችው፤ ትርጓሜውም። መምህር ሆይ ማለት ነው።
16耶穌對她說:“馬利亞!”她轉過身來,用希伯來話對他說:“拉波尼!”(就是“老師”的意思。)
17ኢየሱስም። ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ። እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው አላት።
17耶穌說:“你不要拉住我,因為我還沒有上去見父。你要到我的弟兄們那裡去,告訴他們我要上去見我的父,也是你們的父;見我的 神,也是你們的 神。”
18መግደላዊት ማርያም መጥታ ጌታን እንዳየች ይህንም እንዳላት ለደቀ መዛሙርቱ ነገረች።
18抹大拉的馬利亞就去,向門徒報信說:“我已經看見主了!”她又把主對她所說的話告訴他們。
19ያም ቀን እርሱም ከሳምንቱ ፊተኛው በመሸ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ተሰብስበው በነበሩበት፥ አይሁድን ስለ ፈሩ ደጆቹ ተዘግተው ሳሉ፥ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው።
19向門徒顯現(太28:16~20;可16:14~18;路24:36~49)禮拜日黃昏的時候,門徒聚在一起,因為怕猶太人,就把門戶都關上。耶穌來了,站在他們中間,說:“願你們平安。”
20ይህንም ብሎ እጆቹንም ጎኑንም አሳያቸው። ደቀ መዛሙርቱም ጌታን ባዩ ጊዜ ደስ አላቸው።
20說了這話,就把手和肋旁給他們看。門徒看見主,就歡喜了。
21ኢየሱስም ዳግመኛ። ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ አብ እንደ ላከኝ እኔ ደግሞ እልካችኋለሁ አላቸው።
21耶穌又對他們說:“願你們平安。父怎樣差遣了我,我也怎樣差遣你們。”
22ይህንም ብሎ እፍ አለባቸውና። መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።
22說了這話,就向他們吹一口氣,說:“你們領受聖靈吧!
23ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤ የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል አላቸው።
23你們赦免誰的罪,誰的罪就得赦免;你們不赦免誰的罪,誰的罪就不得赦免。”
24ነገር ግን ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ዲዲሞስ የሚሉት ቶማስ ኢየሱስ በመጣ ጊዜ ከእነርሱ ጋር አልነበረም።
24耶穌向疑惑的多馬顯現十二個門徒中,有一個稱為“雙生子”的多馬。耶穌來的時候,他沒有和門徒在一起。
25ሌሎቹም ደቀ መዛሙርቱ። ጌታን አይተነዋል አሉት። እርሱ ግን። የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ካላየሁ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ እጄንም በጎኑ ካላገባሁ አላምንም አላቸው።
25其他的門徒對他說:“我們已經見過主了。”多馬對他們說:“除非我親眼看見他手上的釘痕,用我的指頭探入那釘痕,又用我的手探入他的肋旁,我決不相信。”
26ከስምንት ቀን በኋላም ደቀ መዛሙርቱ ደግመው በውስጥ ነበሩ፥ ቶማስም ከእነርሱ ጋር ነበረ። ደጆች ተዘግተው ሳሉ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው።
26過了八天,門徒又在屋子裡,多馬也和他們在一起。門戶都關上了。耶穌來了,站在他們中間,說:“願你們平安。”
27ከዚያም በኋላ ቶማስን። ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን አለው።
27然後對多馬說:“把你的指頭放在這裡,看看我的手吧!伸出你的手來,探探我的肋旁!不要疑惑,只要信!”
28ቶማስም። ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት።
28多馬對他說:“我的主!我的 神!”
29ኢየሱስም። ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው።
29耶穌說:“你因為看見我才信嗎?那些沒有看見就信的人,是有福的。”
30ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤
30本書是要人信耶穌得生命耶穌在門徒面前還行了許多別的神蹟,沒有記在這書上。
31ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።
31但把這些事記下來,是要你們信耶穌是基督,是 神的兒子,並且使你們信了,可以因他的名得生命。