1ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በጥብርያዶስ ባሕር አጠገብ ለደቀ መዛሙርቱ እንደ ገና ተገለጠላቸው፤
1耶穌在海邊向七個門徒顯現這些事以後,耶穌在提比里亞海邊再次向門徒顯現。他顯現的經過是這樣的:
2እንዲህም ተገለጠ። ስምዖን ጴጥሮስና ዲዲሞስ የሚባለው ቶማስ ከገሊላ ቃና የሆነ ናትናኤልም የዘብዴዎስም ልጆች ከደቀ መዛሙርቱም ሌሎች ሁለት በአንድነት ነበሩ።
2當時西門.彼得、稱為“雙生子”的多馬、加利利的迦拿人拿但業、西庇太的兩個兒子,和另外兩個門徒都聚在一起。
3ስምዖን ጴጥሮስ። ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ አላቸው። እነርሱም። እኛም ከአንተ ጋር እንመጣለን አሉት። ወጥተውም ወደ ታንኳይቱ ገቡ በዚያችም ሌሊት ምንም እላጠመዱም።
3西門.彼得對他們說:“我要打魚去。”他們說:“我們也跟你一起去。”於是他們出去,上了船,可是那一夜他們並沒有打到甚麼。
4በነጋም ጊዜ ኢየሱስ በባሕር ዳር ቆመ፤ ደቀ መዛሙርቱ ግን ኢየሱስ መሆኑን አላወቁም።
4清早的時候,耶穌站在岸邊;門徒卻不知道他就是耶穌。
5ኢየሱስም። ልጆች ሆይ፥ አንዳች የሚበላ አላችሁን? አላቸው። የለንም ብለው መለሱለት።
5耶穌對他們說:“孩子們,打到魚沒有?”他們回答:“沒有。”
6እርሱም። መረቡን በታንኳይቱ በስተ ቀኝ ጣሉት ታገኙማላችሁ አላቸው። ስለዚህ ጣሉት፤ በዚህም ጊዜ ከዓሣው ብዛት የተነሣ ሊጐትቱት አቃታቸው።
6耶穌說:“把網撒在船的右邊,就可以得著。”他們就把網撒下去,可是拉不上來,因為魚太多。
7ኢየሱስ ይወደው የነበረውም ደቀ መዝሙር ጴጥሮስን። ጌታ እኮ ነው አለው። ስለዚህ ስምዖን ጴጥሮስ ጌታ መሆኑን በሰማ ጊዜ ዕራቁቱን ነበረና ልብሱን ታጥቆ ወደ ባሕር ራሱን ጣለ።
7耶穌所愛的那門徒對彼得說:“是主!”西門.彼得一聽見是主,就立刻束上外衣(因為他當時赤著身子),縱身跳進海裡。
8ሌሎቹ ደቀ መዛሙርት ግን ከምድር ሁለት መቶ ክንድ ያህል እንጂ እጅግ አልራቁም ነበርና ዓሣ የሞላውን መረብ እየሳቡ በጀልባ መጡ።
8其他的門徒,因為離岸不遠(約有一百公尺),就坐在小船上,把那網魚拖過來。
9ወደ ምድርም በወጡ ጊዜ ፍምና ዓሣ በላዩ ተቀምጦ እንጀራም አዩ።
9他們上了岸,就看見那裡有一堆炭火,上面有魚有餅。
10ኢየሱስም። አሁን ካጠመዳችሁት ዓሣ አምጡ አላቸው።
10耶穌對他們說:“把你們剛才打的魚拿幾條來。”
11ስምዖን ጴጥሮስም ወደ ጀልባይቱ ገብቶ መቶ አምሳ ሦስት ታላላቅ ዓሦች ሞልቶ የነበረውን መረብ ወደ ምድር ጐተተ፤ ይህንም ያህል ብዙ ሲሆን መረቡ አልተቀደደም።
11西門.彼得就上船,把網拉到岸上;那網滿了大魚,共有一百五十三條。魚雖然這麼多,網卻沒有破。
12ኢየሱስም። ኑ፥ ምሳ ብሉ አላቸው። ከደቀ መዛሙርቱ አንድ ስንኳ። አንተ ማን ነህ? ብሎ ሊመረምረው የደፈረ አልነበረም፤ ጌታ መሆኑን አውቀው ነበርና።
12耶穌對他們說:“你們來,吃早飯吧。”門徒中沒有一個人敢問他:“你是誰?”因為知道他是主。
13ኢየሱስም መጣና እንጀራ አንሥቶ ሰጣቸው፥ እንዲሁም ዓሣውን።
13耶穌走過來,拿餅遞給他們,又照樣拿魚遞給他們。
14ኢየሱስ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ሲገለጥላቸው ይህ ሦስተኛው ጊዜ ነበረ።
14這是耶穌從死人中復活之後,第三次向門徒顯現。
15ምሳ ከበሉ በኋላም ኢየሱስ ስምዖን ጴጥሮስን። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ግልገሎቼን አሰማራ አለው።
15耶穌三次問彼得是否愛他他們吃了早飯,耶穌問西門.彼得:“約翰的兒子西門,你愛我比這些更深嗎?”他回答:“主啊,是的,你知道我愛你。”耶穌說:“你餵養我的小羊。”
16ደግሞ ሁለተኛ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው።
16耶穌第二次又問他:“約翰的兒子西門,你愛我嗎?”他回答:“主啊,是的,你知道我愛你。”耶穌說:“你牧養我的羊。”
17ጠቦቶቼን ጠብቅ አለው። ሦስተኛ ጊዜ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። ሦስተኛ። ትወደኛለህን? ስላለው ጴጥሮስ አዘነና። ጌታ ሆይ፥ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ኢየሱስም። በጎቼን አሰማራ።
17耶穌第三次問他:“約翰的兒子西門,你愛我嗎?”彼得因為耶穌第三次問他:“你愛我嗎?”就憂愁起來,對耶穌說:“主啊,你是無所不知的,你知道我愛你。”耶穌說:“你餵養我的羊。
18እውነት እውነት እልሃለሁ፥ አንተ ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን በገዛ ራስህ ታጥቀህ ወደምትወደው ትሄድ ነበር፤ ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ፥ ሌላውም ያስታጥቅሃል ወደማትወደውም ይወስድሃል አለው።
18我實實在在告訴你,你年輕的時候,自己束上腰帶,隨意往來;但到了年老的時候,你要伸出手來,別人要把你綁著,帶你到你不願意去的地方。”
19በምን ዓይነት ሞት እግዚአብሔርን ያከብር ዘንድ እንዳለው ሲያመለክት ይህን አለ። ይህንም ብሎ። ተከተለኝ አለው።
19耶穌說這話,是指明彼得將怎樣死,來榮耀 神。說了這話,就對彼得說:“你跟從我吧!”
20ጴጥሮስም ዘወር ብሎ ኢየሱስ ይወደው የነበረውን ደቀ መዝሙር ሲከተለው አየ፤ እርሱም ደግሞ በእራት ጊዜ በደረቱ ተጠግቶ። ጌታ ሆይ፥ አሳልፎ የሚሰጥህ ማን ነው? ያለው ነበረ።
20耶穌所愛的那門徒彼得轉過身來,看見耶穌所愛的那門徒跟著,就是在晚飯的時候,靠著耶穌的胸膛,問“主啊,出賣你的是誰?”的那個人。
21ጴጥሮስም ይህን አይቶ ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ ይህስ እንዴት ይሆናል? አለው።
21彼得看見他,就問耶穌:“主啊,這個人將來怎麼樣?”
22ኢየሱስም። እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ፥ ምን አግዶህ? አንተ ተከተለኝ አለው።
22耶穌回答他:“如果我要他活到我來的時候,跟你有甚麼關係呢?你只管跟從我吧!”
23ስለዚህ። ያ ደቀ መዝሙር አይሞትም የሚለው ይህ ነገር ወደ ወንድሞች ወጣ፤ ነገር ግን ኢየሱስ። እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ? አለው እንጂ አይሞትም አላለውም።
23於是這話流傳在弟兄中間,說那門徒不會死。其實耶穌並沒有說他不會死,只是說:“如果我要他活到我來的時候,跟你有甚麼關係呢?”
24ስለ እነዚህም የመሰከረ ይህንንም ጽፎ ያለ ይህ ደቀ መዝሙር ነው፥ ምስክሩም እውነት እንደ ሆነ እናውቃለን።
24為這些事作證,並且記述這些事的,就是這門徒;我們知道他的見證是真實的。
25ኢየሱስም ያደረገው ብዙ ሌላ ነገር ደግሞ አለ፤ ሁሉ በእያንዳንዱ ቢጻፍ ለተጻፉት መጻሕፍት ዓለም ራሱ ባልበቃቸውም ይመስለኛል።
25耶穌所行的,還有許多其他的事;如果都一一寫下來,所要寫成的書,我想就是這個世界也容不下了。