1እርሱም በአንድ ስፍራ ይጸልይ ነበር፥ በጨረሰም ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ። ጌታ ሆይ፥ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርቱን እንዳስተማረ እንጸልይ ዘንድ አስተምረን አለው።
1祈求就必得著(太6:9~13,7:7~11)有一天,耶穌在一個地方祈禱,祈禱完了,有一個門徒對他說:“主啊,求你教導我們禱告,像約翰教導他的門徒一樣。”
2አላቸውም። ስትጸልዩ እንዲህ በሉ። በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፤ ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤
2耶穌說:“你們禱告的時候,要說:‘父啊,願你的名被尊為聖,願你的國降臨(有些抄本在此有“願你的旨意行在地上,如同行在天上”一句);
3የዕለት እንጀራችንን ዕለት ዕለት ስጠን፤
3我們需用的食物,求你每天賜給我們;
4ኃጢአታችንንም ይቅር በለን፥ እኛ ደግሞ የበደሉንን ሁሉ ይቅር ብለናልና፤ ከክፉ አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታግባን።
4赦免我們的罪,因為我們也饒恕所有虧負我們的人;不要讓我們陷入試探(有些抄本在此有“救我們脫離那惡者”一句)。’”
5እንዲህም አላቸው። ከእናንተ ማናቸውም ወዳጅ ያለው፥ በእኩል ሌሊትስ ወደ እርሱ ሄዶ። ወዳጄ ሆይ፥ ሦስት እንጀራ አበድረኝ፥
5耶穌又對他們說:“你們當中,誰有朋友半夜去找他,說:‘請你借給我三個餅,
6አንድ ወዳጄ ከመንገድ ወደ እኔ መጥቶ የማቀርብለት የለኝምና ይላልን?
6因為我有一個朋友旅行來到我這裡,我沒有甚麼可以招待他。’
7ያም ከውስጥ መልሶ። አታድክመኝ፤ አሁን ደጁ ተቈልፎአል ልጆቼም ከእኔ ጋር በአልጋ ላይ አሉ፤ ተነሥቼ ልሰጥህ አልችልም ይላልን?
7而他卻在裡面回答:‘不要麻煩我,門已經關好了,孩子也跟我在床上了,我不能起來拿給你。’
8እላችኋለሁ፥ ወዳጅ ስለ ሆነ ተነሥቶ ባይሰጠው እንኳ፥ ስለ ንዝነዛው ተነስቶ የሚፈልገውን ሁሉ ይሰጠዋል።
8我告訴你們,即使不因為他是朋友而起來給他,也會因為他厚顏地直求,而起來照他所需要的給他。
9እኔም እላችኋለሁ። ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፍትላችሁማል።
9我又告訴你們,你們祈求,就給你們;尋找,就尋見;叩門,就給你們開門。
10የሚለምን ሁሉ ይቀበላልና፥ የሚፈልግም ያገኛል፥ መዝጊያውንም ለሚያንኳኳው ይከፈትለታል።
10因為所有祈求的就得著,尋找的就尋見,叩門的就給他開門。
11አባት ከሆናችሁ ከእናንተ ከማንኛችሁም ልጁ እንጀራ ቢለምነው፥ እርሱም ድንጋይ ይሰጠዋልን? ዓሣ ደግሞ ቢለምነው በዓሣ ፋንታ እባብ ይሰጠዋልን?
11你們中間作父親的,哪有兒子求魚,反拿蛇給他呢?
12ወይስ እንቍላል ቢለምነው ጊንጥ ይሰጠዋልን?
12或求雞蛋,反給他蠍子呢?
13እንኪያስ እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠት ካወቃችሁ፥ በሰማይ ያለው አባት ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መንፈስ ቅዱስን ይሰጣቸው?
13你們雖然不好,尚且知道把好東西給自己的兒女,何況天父,豈不更把聖靈賜給求他的人嗎?”
14ዲዳውንም ጋኔን ያወጣ ነበር፤ ጋኔኑም ከወጣ በኋላ ዲዳው ተናገረ ሕዝቡም ተደነቁ፤
14耶穌靠 神的能力趕鬼(太12:22~30;可3:22~27)耶穌趕出一個啞巴鬼,鬼既出去,啞巴就說起話來,眾人都希奇。
15ነገር ግን ከእነርሱ አንዳንዱ። በብዔል ዜቡል በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል አሉ።
15有人說:“他靠鬼王別西卜趕鬼。”
16ሌሎችም ሲፈትኑት ከሰማይ ምልክት ከእርሱ ይፈልጉ ነበር።
16又有人試探他,向他求一個從天上來的神蹟。
17እርሱ ግን አሳባቸውን አውቆ እንዲህ አላቸው። እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁሉ ትጠፋለች፤ ቤትም በቤት ላይ ይወድቃል።
17耶穌知道他們的心意,就對他們說:“如果一個國家自相紛爭,就必定荒涼;如果一個家庭自相為敵,就必然敗落。
18እኔ አጋንንትን በብዔል ዜቡል እንዳወጣ ትላላችሁና ሰይጣን ደግሞ እርስ በርሱ ከተለያየ መንግሥቱ እንዴት ትቆማለች?
18如果撒但自相紛爭,他的國怎能站立得住呢?你們說我靠別西卜趕鬼,
19እኔስ በብዔል ዜቡል አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ ልጆቻችሁ በማን ያወጡአቸዋል? ስለዚህ እነርሱ ፈራጆች ይሆኑባችኋል።
19我若靠別西卜趕鬼,你們的子孫趕鬼又靠誰呢?因此,他們必要作你們的審判官。
20እኔ ግን በእግዚአብሔር ጣት አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ እንግዲህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ደርሳለች።
20我若靠 神的能力趕鬼,這就是 神的國臨到你們了。
21ኃይለኛ ሰው ጋሻና ጦር ይዞ የራሱን ግቢ ቢጠብቅ፥ ያለው ገንዘቡ በሰላም ይሆናል፤
21一個壯漢拿著武器,看守自己的家園,他的家財就平安無事。
22ከእርሱ ይልቅ የሚበረታ መጥቶ ሲያሸንፈው ግን፥ ታምኖበት የነበረውን ጋሻና ጦር ይወስድበታል ምርኮውንም ያካፍላል።
22但是一個比他更強的人來了,勝過了他,奪去他所倚靠的武器,就把他的家財當作掠物分了。
23ከእኔ ጋር ያልሆነ ይቃወመኛል፥ ከእኔ ጋርም የማያከማች ይበትናል።
23不站在我這一邊的就是反對我的;不跟從一起收聚的就是分散的。
24ርኵስ መንፈስ ከሰው በወጣ ጊዜ ዕረፍትን እየፈለገ ውኃ በሌለበት ቦታ ያልፋል፤ ባያገኝም። ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል፤
24污靈去而復返的教訓(太12:43~45)“一個污靈離開了一個人,走遍乾旱之地,尋找棲身的地方,卻沒有找到,就說:‘我要回到我從前離開了的那房子。’
25ሲመጣም ተጠርጎ አጊጦም ያገኘዋል።
25到了之後,看見裡面已經打掃乾淨,粉飾好了,
26ከዚያ ወዲያ ይሄድና ከእርሱ የከፉትን ሌሎችን ሰባት አጋንንት ከእርሱ ጋር ይይዛል፥ ገብተውም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያም ሰው ከፊተኛው ይልቅ የኋለኛው ይብስበታል።
26他就去帶了另外七個比自己更惡的污靈來,進去住在那裡;那人後來的情況,比以前更壞了。”
27ይህንም ሲናገር፥ ከሕዝቡ አንዲት ሴት ድምፅዋን ከፍ አድርጋ። የተሸከመችህ ማኅፀንና የጠባሃቸው ጡቶች ብፁዓን ናቸው አለችው።
27約拿的神蹟(太12:39~42)耶穌正說這些話的時候,群眾中有一個女人高聲對他說:“懷你胎的和哺養你的有福了!”
28እርሱ ግን። አዎን፥ ብፁዓንስ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚጠብቁት ናቸው አለ።
28他說:“是的,卻還不如聽 神的道而遵守的人有福。”
29ብዙ ሕዝብም በተሰበሰቡ ጊዜ እንዲህ ይል ጀመር። ይህ ትውልድ ክፉ ነው፤ ምልክት ይፈልጋል፥ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም።
29眾人聚集的時候,耶穌就說:“這世代是個邪惡的世代。這世代尋求神蹟,可是除了約拿的神蹟以外,再沒有神蹟給他們了。
30ዮናስ ለነነዌ ሰዎች ምልክት እንደ ሆናቸው፥ እንዲሁ ደግሞ የሰው ልጅ ለዚህ ትውልድ ምልክት ይሆናል።
30約拿怎樣成了尼尼微人的神蹟,人子也照樣成為這個世代的神蹟。
31ንግሥተ አዜብ በፍርድ ከዚህ ትውልድ ሰዎች ጋር ተነሥታ ትፈርድባቸዋለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና፥ እነሆም፥ ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ።
31審判的時候,南方的女王要和這世代的人一同起來,她要定他們的罪,因為她從地極來到,要聽所羅門智慧的話。你看,這裡有一位是比所羅門更大的。
32የነነዌ ሰዎች በፍርድ ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፥ እነሆም፥ ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።
32審判的時候,尼尼微人要和這世代的人一同起來,他們要定這個世代的罪,因為尼尼微人聽了約拿所傳的就悔改了。你看,這裡有一位是比約拿更大的。
33መብራትንም አብርቶ በስውር ወይም በእንቅብ በታች የሚያኖረው የለም፥ የሚገቡ ሰዎች ብርሃኑን እንዲያዩ በመቅረዝ ላይ ያኖረዋል እንጂ።
33裡面的光(太5:15,6:22~23)“沒有人點了燈,把它放在地窖裡,或量器底下,卻放在燈臺上,叫進來的人看得見光。
34የሰውነትህ መብራት ዓይንህ ናት። ዓይንህ ጤናማ በሆነች ጊዜ ሰውነትህ ሁሉ ደግሞ ብሩህ ይሆናል። ዓይንህ ታማሚ በሆነች ጊዜ ግን ሰውነትህ ደግሞ የጨለመ ይሆናል።
34你的眼睛就是你身體的燈,你的眼睛健全,全身就明亮;如果不健全,全身就黑暗。
35እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ እንዳይሆን ተመልከት።
35所以要謹慎,免得你裡面的光黑暗了。
36እንግዲህ ሰውነትህ ሁሉ የጨለማ ቍራጭ የሌለበት ብሩህ ቢሆን፥ መብራት በደመቀ ብርሃን እንደሚያበራልህ በጭራሽ ብሩህ ይሆናል።
36你若全身明亮,沒有一點黑暗,你就完全明亮,好像明亮的燈光照你一樣。”
37ይህንንም ሲናገር አንድ ፈሪሳዊ ከእርሱ ጋር ምሳ ይበላ ዘንድ ለመነው ገብቶም ተቀመጠ።
37法利賽人和律法師有禍了(太23:1~36;可12:38~40)耶穌說話的時候,有一個法利賽人請耶穌和他一起吃飯;他就進去坐席。
38ከምሳም በፊት አስቀድሞ እንዳልታጠበ ባየው ጊዜ ፈሪሳዊው ተደነቀ።
38這個法利賽人見耶穌吃飯之前不洗手,覺得奇怪。
39ጌታም እንዲህ አለው። አሁን እናንተ ፈሪሳውያን የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ታጠራላችሁ፥ ውስጣችሁ ግን ቅሚያና ክፋት ሞልቶበታል
39主對他說:“你們法利賽人把杯盤的外面洗淨,但你們裡面卻充滿了搶奪和邪惡。
40እናንት ደንቆሮዎች፥ የውጭውን የፈጠረ የውስጡን ደግሞ አልፈጠረምን?
40無知的人哪,那造外面的,不也造裡面嗎?
41ነገር ግን በውስጥ ያለውን ምጽዋት አድርጋችሁ ስጡ፥ እነሆም፥ ሁሉ ንጹሕ ይሆንላችኋል።
41只要把裡面的施捨出去,你們的一切就都潔淨了。
42ነገር ግን እናንተ ፈሪሳውያን፥ ከአዝሙድና ከጤና አዳም ከአትክልትም ሁሉ አሥራት ስለምታወጡ፥ ፍርድንና እግዚአብሔርን መውደድ ስለምትተላለፉ፥ ወዮላችሁ፤ ነገር ግን ሌላውን ሳትተዉ ይህን ልታደርጉት ይገባችሁ ነበር።
42然而你們法利賽人有禍了!因為你們把薄荷、茴香和各樣菜蔬獻上十分之一,卻把公義和愛 神的事疏忽了;這些是你們應當作的,但其他的也不可疏忽。
43እናንተ ፈሪሳውያን፥ በምኵራብ የከበሬታ ወንበር በገበያም ሰላምታ ስለምትወዱ፥ ወዮላችሁ።
43你們法利賽人有禍了!因為你們喜愛會堂裡的高位和人在巿中心的問安。
44እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ ሰዎች ሳያውቁ በላዩ የሚሄዱበት የተሰወረ መቃብር ስለምትመስሉ፥ ወዮላችሁ።
44你們有禍了!因為你們好像不顯露的墳墓,走在上面的人並不知道。”
45ከሕግ አዋቂዎችም አንዱ መልሶ። መምህር ሆይ፥ ይህን ማለትህ እኛን ደግሞ መስደብህ ነው አለው።
45律法師中有一個回答他:“老師,你這樣說,把我們也侮辱了!”
46እርሱም እንዲህ አለ። እናንተ ደግሞ ሕግ አዋቂዎች፥ አስቸጋሪ ሸክም ለሰዎች ስለምታሸክሙ፥ ራሳችሁም በአንዲት ጣታችሁ ስንኳ ሸክሙን ስለማትነኩት፥ ወዮላችሁ።
46耶穌說:“你們律法師也有禍了,因為你們把難擔的擔子叫人擔,自己連一個指頭也不動。
47አባቶቻችሁ የገደሉአቸውን የነቢያትን መቃብር ስለምትሠሩ፥ ወዮላችሁ።
47你們有禍了!因為你們修造先知的墳墓,而那些先知正是你們祖先所殺的,
48እንግዲህ ለአባቶቻችሁ ሥራ ትመሰክራላችሁ ትስማማላችሁም፤ እነርሱ ገድለዋቸዋልና፥ እናንተም መቃብራቸውን ትሠራላችሁ።
48這樣,你們就成了證人,對你們祖先的作為表示同意;他們殺害先知,你們修造先知的墳墓。
49ስለዚህ ደግሞ የእግዚአብሔር ጥበብ እንዲህ አለች። ወደ እነርሱ ነቢያትንና ሐዋርያትን እልካለሁ፥ ከእነርሱም ይገድላሉ ያሳድዱማል፥
49所以, 神的智慧說:‘我要差遣先知和使徒到他們那裡去,有的他們要殺害,有的他們要迫害,
50ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የፈሰሰው የነቢያት ሁሉ ደም፥
50為要使創世以來眾先知所流的血,從亞伯的血起,直到在祭壇和聖所之間受害的撒迦利亞的血為止,都向這一代追討。’是的,我告訴你們,都要向這一代追討。
51ከአቤል ደም ጀምሮ በመሠዊያውና በቤተ መቅደስ መካከል እስከ ጠፋው እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ፥ ከዚህ ትውልድ እንዲፈለግ አዎን እላችኋለሁ፥ ከዚህ ትውልድ ይፈለጋል።
51
52እናንተ ሕግ አዋቂዎች፥ የእውቀትን መክፈቻ ስለ ወሰዳችሁ፥ ወዮላችሁ ራሳችሁ አልገባችሁም የሚገቡትንም ከለከላችሁ።
52你們律法師有禍了!因為你們拿去知識的鑰匙,自己不進去,又阻止要進去的人。”
53ይህንም ሲናገራቸው፥ ጻፎችና ፈሪሳውያን በአፉ የተናገረውን ሊነጥቁ ሲያደቡ፥ እጅግ ይቃወሙና ስለ ብዙ ነገር እንዲናገር ያነሣሡ ጀመር።
53耶穌從那裡出來,經學家和法利賽人非常敵視他,質問他很多問題,