Amharic: New Testament

聖經新譯本

Luke

12

1በዚያን ጊዜ የሕዝብ አእላፍ እርስ በርሳቸው እስኪረጋገጡ ድረስ ተሰብስበው ሳሉ፥ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ይል ጀመር። አስቀድማችሁ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ፥ እርሱም ግብዝነት ነው።
1提防法利賽人的酵(太10:26~27)那時有成千上萬的人聚在一起,甚至彼此踐踏。耶穌就先對門徒說:“你們要提防法利賽人的酵,就是虛偽。
2ነገር ግን የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለም።
2沒有甚麼掩蓋的事不被揭露,也沒有甚麼隱藏的事不被人知道。
3ስለዚህ በጨለማ የምትናገሩት ሁሉ በብርሃን ይሰማል፥ በእልፍኝም ውስጥ በጆሮ የምትናገሩት በሰገነት ላይ ይሰበካል።
3所以,你們在暗處所說的,必在明處被人聽見;在內室附耳所談的,必在房頂上宣揚出來。
4ለእናንተም ለወዳጆቼ እላችኋለሁ፥ ሥጋን የሚገድሉትን በኋላም አንድ ስንኳ የሚበልጥ ሊያደርጉ የማይችሉትን አትፍሩ።
4應該怕誰(太10:28~31)“我的朋友,我告訴你們,那殺身體以後不能再作甚麼的,不要怕他們。
5እኔ ግን የምትፈሩትን አሳያችኋለሁ፤ ከገደለ በኋላ ወደ ገሃነም ለመጣል ሥልጣን ያለውን ፍሩ። አዎን እላችኋለሁ፥ እርሱን ፍሩ።
5我要指示你們當怕的是誰:當怕那殺身體以後,有權把人投入地獄裡的;我告訴你們,應當怕他。
6አምስት ድንቢጦች በአሥር ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ስንኳ በእግዚአብሔር ፊት አትረሳም።
6五隻麻雀,不是賣兩個大錢嗎?但在 神面前,一隻也不被忘記。
7ነገር ግን የእናንተ የራሳችሁ ጠጕር ሁሉ እንኳ የተቈጠረ ነው፤ እንግዲያስ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች ትበልጣላችሁ።
7甚至你們的頭髮都一一數過了。不要怕,你們比許多麻雀貴重得多呢。
8እላችሁማለሁ፥ በሰው ፊት የሚመሰክርልኝ ሁሉ፥ የሰው ልጅ ደግሞ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ይመሰክርለታል፤
8要在人面前承認主(太10:32~33)“我告訴你們,凡在人面前承認我的,人子在 神的使者面前也承認他;
9በሰውም ፊት የሚክደኝ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ይካዳል።
9在人面前不認我的,我在 神的使者面前也不認他。
10በሰው ልጅም ላይ ቃል የሚናገር ሁሉ ይሰረይለታል፤ መንፈስ ቅዱስን የሚሰድብ ግን አይሰረይለትም።
10凡說話得罪人子的,還可以赦免;但褻瀆聖靈的,必不得赦免。
11ወደ ምኵራቦችና ወደ መኳንንቶችም ወደ ገዢዎችም ሲጐትቱአችሁ፥ እንዴት ወይም ምን እንድትመልሱ ወይም እንድትናገሩ አትጨነቁ፤
11人把你們拉到會堂、官長和當權者的面前,你們不要思慮怎樣申辯或說甚麼話。
12መንፈስ ቅዱስ በዚያች ሰዓት ልትናገሩ የሚገባችሁን ያስተምራችኋልና።
12到了時候,聖靈必把當說的話教導你們。”
13ከሕዝቡም አንድ ሰው። መምህር ሆይ፥ ርስቱን ከእኔ ጋር እንዲካፈል ለወንድሜ ንገረው አለው።
13無知富翁的比喻群眾中有一個人對耶穌說:“老師,請吩咐我的兄弟和我分家業。”
14እርሱም። አንተ ሰው፥ ፈራጅና አካፋይ በላያችሁ አንድሆን ማን ሾመኝ? አለው።
14耶穌說:“你這個人,誰立我作你們的審判官和分家業的人呢?”
15የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና ተጠንቀቁ፥ ከመጐምጀትም ሁሉ ተጠበቁ አላቸው።
15於是他對眾人說:“你們要謹慎,遠離一切貪心,因為人的生命並不在於家道豐富。”
16ምሳሌም ነገራቸው እንዲህ ሲል። አንድ ባለ ጠጋ ሰው እርሻ እጅግ ፍሬያም ሆነችለት።
16就對他們講了一個比喻,說:“有一個富翁的田地豐收。
17እርሱም። ፍሬዬን የማከማችበት ስፍራ አጥቻለሁና ምን ላድርግ? ብሎ በልቡ አሰበ።
17他自己心裡說:‘怎麼辦呢?因為我沒有足夠的地方收藏出產了!’
18እንዲህ አደርጋለሁ፤ ጐተራዬን አፍርሼ ሌላ የሚበልጥ እሠራለሁ፥ በዚያም ፍሬዬንና በረከቴን ሁሉ አከማቻለሁ፤
18又說:‘我要這樣辦:我要拆掉這些倉房,建造更大的,好在那裡收藏我的一切糧食和貨物。
19ነፍሴንም። አንቺ ነፍሴ፥ ለብዙ ዘመን የሚቀር ብዙ በረከት አለሽ፤ ዕረፊ፥ ብዪ፥ ጠጪ፥ ደስ ይበልሽ እላታለሁ አለ።
19然後,我要對我的靈魂說:靈魂啊,你擁有許多好東西,足夠多年享用,只管安安逸逸地吃喝快樂吧!’
20እግዚአብሔር ግን። አንተ ሰነፍ፥ በዚች ሌሊት ነፍስህን ከአንተ ሊወስዱአት ይፈልጓታል፤ ይህስ የሰበሰብኸው ለማን ይሆናል? አለው።
20 神卻對他說:‘無知的人哪,今天晚上,你擁有的就要取去你的靈魂,你所預備的要歸給誰呢?’
21ለራሱ ገንዘብ የሚያከማች፥ በእግዚአብሔር ዘንድም ባለ ጠጋ ያልሆነ እንዲህ ነው።
21凡為自己積財,在 神面前卻不富足的,也是這樣。”
22ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ። ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ለነፍሳችሁ በምትበሉት ወይም ለሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ።
22不要憂慮,積財於天(太6:19~21、25~33)耶穌又對門徒說:“所以我告訴你們,不要為生命憂慮吃甚麼,也不要為身體憂慮穿甚麼。
23ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ ይበልጣልና።
23因為生命比飲食重要,身體比衣服重要。
24ቍራዎችን ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱምም፥ ዕቃ ቤትም ወይም ጎተራ የላቸውም፥ እግዚአብሔርም ይመግባቸዋል፤ እናንተስ ከወፎች እንዴት ትበልጣላችሁ?
24你們想想烏鴉:牠們不種也不收,無倉又無庫, 神尚且養活牠們;你們比飛鳥貴重得多了。
25ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው?
25你們中間誰能用憂慮使自己的壽命延長一刻呢?
26እንግዲህ ትንሹን ነገር ስንኳ የማትችሉ ከሆናችሁ፥ ስለ ምን በሌላ ትጨነቃላችሁ?
26既然連這極小的事都不能作,為甚麼還憂慮其他的事呢?
27አበቦችን እንዴት እንዲያድጉ ተመልከቱ፤ አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከእነዚህ እንደ አንዲቱ አለበሰም።
27你們想想百合花,怎樣不勞苦,也不紡織。但我告訴你們,就是所羅門最榮華的時候所穿的,也比不上這花中的一朵呢。
28እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን በሜዳ የሆነውን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ፥ እናንተ እምነት የጐደላችሁ፥ እናንተንማ ይልቁን እንዴት?
28小信的人哪,田野的草,今天還在,明天就投進爐裡, 神尚且這樣給它裝飾,何況你們呢?
29እናንተም የምትበሉትን የምትጠጡትንም አትፈልጉ፥ አታወላውሉም፤
29你們不要求吃甚麼,喝甚麼,也不要憂慮,
30ይህንስ ሁሉ በዓለም ያሉ አሕዛብ ይፈልጉታልና፤ የእናንተም አባት ይህ እንዲያስፈልጋችሁ ያውቃል።
30因為這一切都是世上不信的人所尋求的。你們的父原知道你們需要這一切。
31ዳሩ ግን መንግሥቱን ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።
31你們只管求他的國,這些東西都必加給你們。
32አንተ ታናሽ መንጋ፥ መንግሥትን ሊሰጣችሁ የአባታችሁ በጎ ፈቃድ ነውና አትፍሩ።
32你們這小群,不要怕,因為你們的父樂意把國賜給你們。
33ያላችሁን ሽጡ ምጽዋትም ስጡ፤ ሌባ በማይቀርብበት ብልም በማያጠፋበት በሰማያት የማያልቅ መዝገብ የሚሆኑትን የማያረጁትንም ኮረጆዎች ለራሳችሁ አድርጉ፤
33當變賣你們所有的施捨給人,為自己製造不朽壞的錢囊,積蓄用不盡的財寶在天上,就是賊不能近、蟲不能蛀的地方。
34መዝገባችሁ ባለበት ልባችሁ ደግሞ በዚያ ይሆናልና።
34因為你們的財寶在哪裡,你們的心也在哪裡。
35ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን፤
35忠心的僕人有福了(太24:45~51;可13:33~37)“你們的腰當束起來,燈也該點著,
36እናንተም ጌታቸው መጥቶ ደጁን ሲያንኳኳ ወዲያው እንዲከፍቱለት ከሰርግ እስኪመለስ ድረስ የሚጠብቁ ሰዎችን ምሰሉ
36像等候自己的主人從婚筵回來一樣,好叫你們在主人回來敲門時,立刻給他開門。
37ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።
37主人來到了,看見僕人警醒,這些僕人就有福了。我實在告訴你們,主人必親自束腰,招待他們吃飯,進前來侍候他們。
38ከሌሊቱም በሁለተኛው ወይም በሦስተኛው ክፍል መጥቶ እንዲሁ ቢያገኛቸው፥ እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው።
38主人也許半夜之前,或天亮之前回來,看見他們這樣,這些僕人就有福了。
39ይህን ግን እወቁ ባለቤት በምን ሰዓት ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ፥ በነቃ፥ ቤቱም እንዲቆፈር ባልፈቀደም ነበር።
39你們都知道,家主若曉得竊賊甚麼時候來,就不會讓他摸進屋裡。
40እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።
40你們也要準備妥當,因為在想不到的時候,人子就來了。”
41ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ ይህን ምሳሌ ለእኛ ወይስ ደግሞ ለሁሉ ትናገራለህን? አለው።
41彼得說:“主啊,你說這比喻,是為我們還是為眾人呢?”
42ጌታም አለ። እንኪያስ ምግባቸውን በጊዜው ይሰጣቸው ዘንድ ጌታው በቤተ ሰዎቹ ላይ የሚሾመው ታማኝና ልባም መጋቢ ማን ነው?
42主說:“誰是那忠心精明的管家,被主人指派管理家裡的僕人,按時分糧呢?
43ጌታው መጥቶ እንዲህ ሲያደርግ የሚያገኘው ያ ባሪያ ብፁዕ ነው።
43主人來到的時候,看見他這樣作,那僕人就有福了。
44እውነት እላችኋለሁ፥ ባለው ሁሉ ላይ ይሾመዋል።
44我實在告訴你們,主人要指派他管理主人的一切財產。
45ያ ባሪያ ግን። ጌታዬ እስኪመጣ ይዘገያል ብሎ በልቡ ቢያስብ ሎሌዎችንና ገረዶችንም ይመታ ይበላም ይጠጣም ይሰክርም ዘንድ ቢጀምር፥
45如果那僕人心裡說:‘我的主人不會那麼快回來’,就動手打其他的僕人使女,並且吃喝醉酒;
46የዚያ ባሪያ ጌታ ባልጠበቃት ቀን ባላወቃትም ሰዓት ይመጣል፥ ከሁለትም ይሰነጥቀዋል እድሉንም ከማይታመኑ ጋር ያደርጋል።
46在他想不到的日子、不知道的時間,那僕人的主人要來,嚴厲地處罰他,使他和不信的人同在一起。
47የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ያ ባሪያ እጅግ ይገረፋል፤
47那僕人知道主人的意思,卻不預備,也不照他的意思行,必多受責打;
48ያላወቀ ግን መገረፍ የሚገባውንም ያደረገ ጥቂት ይገረፋል። ብዙም ከተሰጠው ሰው ሁሉ ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል፥ ብዙ አደራም ከተሰጠው ከእርሱ አብዝተው ይሹበታል።
48但那不知道的,雖然作了該受責打的事,也必少受責打。多給誰就向誰多取,多託誰就向誰多要。
49በምድር ላይ እሳት ልጥል መጣሁ፥ አሁንም የነደደ ከሆነ ዘንድ ምን እፈልጋለሁ?
49將引起紛爭(太10:34~36)“我來要把火投在地上,如果燒了起來,那是我所願意的。
50ነገር ግን የምጠመቃት ጥምቀት አለችኝ፥ እስክትፈጸምም ድረስ እንዴት እጨነቃለሁ?
50我有應當受的洗,我是多麼迫切地期待這事完成。
51በምድር ላይ ሰላምንም ለመስጠት የመጣሁ ይመስላችኋልን? እላችኋለሁ፥ አይደለም፥ መለያየትን እንጂ።
51你們以為我來是要地上有和平嗎?不是的,我告訴你們,是要有紛爭。
52ከአሁን ጀምሮ በአንዲት ቤት አምስት ሰዎች ይኖራሉና፤ ሦስቱም በሁለቱ ላይ ሁለቱም በሦስቱ ላይ ተነሥተው ይለያያሉ።
52從今以後,一家五口將起紛爭,三個反對兩個,兩個反對三個。
53አባት በልጁ ላይ ልጅም በአባቱ ላይ፥ እናት በልጅዋ ላይ ልጅዋም በእናትዋ ላይ፥ አማት በምራትዋ ላይ ምራትም በአማትዋ ላይ ተነሥተው ይለያያሉ።
53他們將起紛爭:父親反對兒子,兒子反對父親,母親反對女兒,女兒反對母親,婆婆反對媳婦,媳婦反對婆婆。”
54ደግሞም ሕዝቡን እንዲህ አለ። ደመና ከምዕራብ ሲወጣ ባያችሁ ጊዜ፥ ወዲያው። ዝናብ ይመጣል ትላላችሁ፥ እንዲሁም ይሆናል፤
54當曉得分辨和判斷(太16:2~3)耶穌又對眾人說:“你們一看見西邊有雲彩升起來,就說:‘要下大雨’,果然這樣;
55በአዜብም ነፋስ ሲነፍስ። ትኩሳት ይሆናል ትላላችሁ፥ ይሆንማል።
55起了南風,就說:‘天要熱了’,也果然這樣。
56እናንት ግብዞች፥ የምድሩንና የሰማዩን ፊት ልትመረምሩ ታውቃላችሁ፥ ነገር ግን ይህን ዘመን የማትመረምሩ እንዴት ነው?
56偽君子啊!你們知道分辨天地的氣象,怎麼不知道分辨這個時代呢?
57ራሳችሁ ደግሞ ጽድቅን የማትፈርዱ ስለ ምን ነው?
57“你們為甚麼自己不能判斷甚麼是對的呢?
58ከባላጋራህ ጋር ወደ ሹም ብትሄድ፥ ወደ ዳኛ እንዳይጐትትህ ዳኛውም ለሎሌው አሳልፎ እንዳይሰጥህ ሎሌውም በወኅኒ እንዳይጥልህ፥ ገና በመንገድ ሳለህ ከባላጋራህ እንድትታረቅ ትጋ።
58你和你的對頭去見官長,還在路上的時候,應當盡力向他求和,免得他把你拉到法官面前,法官把你交給差役,差役把你關在監裡。
59እልሃለሁ፥ የመጨረሻዋን ግማሽ ሳንቲም እስክትከፍል ድረስ ከዚያ ከቶ አትወጣም።
59我告訴你,除非你還清最後的一個小錢,否則決不能從那裡出來。”