Amharic: New Testament

聖經新譯本

Luke

13

1በዚያን ጊዜም ሰዎች መጥተው ጲላጦስ ደማቸውን ከመሥዋዕታቸው ጋር ስላደባለቀው ስለ ገሊላ ሰዎች አወሩለት።
1若不悔改都要滅亡就在那時候,有幾個在那裡的人,把加利利人的事告訴耶穌,就是彼拉多把他們的血和他們的祭物攙在一起的事。
2ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። እነዚህ የገሊላ ሰዎች ይህ ስለ ደረሰባቸው ከገሊላ ሰዎች ሁሉ ይልቅ ኃጢአተኞች የሆኑ ይመስሉአችኋልን?
2他回答:“你們以為這些加利利人比其他的加利利人更有罪,才這樣受害嗎?
3እላችኋለሁ፥ አይደለም፤ ነገር ግን ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንዲሁ ትጠፋላችሁ።
3不是的,我告訴你們,你們若不悔改,都要這樣滅亡。
4ወይስ በሰሌሆም ግንቡ የወደቀባቸውና የገደላቸው እነዚያ አሥራ ስምንት ሰዎች በኢየሩሳሌም ከሚኖሩት ሁሉ ይልቅ በደለኞች ይመስሉአችኋልን? አይደለም፥ እላችኋለሁ፤
4你們以為從前西羅亞樓倒塌的時候,壓死的那十八個人,比一切在耶路撒冷的居民更有罪嗎?
5ነገር ግን ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንደዚሁ ትጠፋላችሁ።
5不是的,我告訴你們,你們若不悔改,也都要這樣滅亡。”
6ይህንም ምሳሌ አለ። ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው፥ ፍሬም ሊፈልግባት መጥቶ ምንም አላገኘም።
6不結果的無花果樹耶穌講了這樣一個比喻:“有一個人把一棵無花果樹栽在自己的葡萄園裡。他來到樹那裡找果子,卻找不到。
7የወይን አትክልት ሠራተኛውንም። እነሆ፥ ከዚህች በለስ ፍሬ ልፈልግ ሦስት ዓመት እየመጣሁ ምንም አላገኘሁም፤ ቍረጣት፤ ስለ ምን ደግሞ መሬቱን ታጐሳቍላለች? አለው።
7他對管園的說:‘你看,這三年,我來到這棵無花果樹那裡找果子,卻找不到,把它砍了吧!何必白佔地土呢?’
8እርሱ ግን መልሶ። ጌታ ሆይ፥ ዙሪያዋን እስክኰተኵትላትና ፋንድያ እስካፈስላት ድረስ በዚች ዓመት ደግሞ ተዋት።
8管園的說:‘主人,今年且留著它,等我把周圍的泥土挖鬆,加上肥料;
9ወደ ፊትም ብታፈራ፥ ደኅና ነው፤ ያለዚያ ግን ትቈርጣታለህ አለው።
9以後結果子就罷,不然,再把它砍了。’”
10በሰንበትም በአንድ ምኵራብ ያስተምር ነበር።
10在安息日治好病人安息日的時候,耶穌在會堂裡教導人。
11እነሆም፥ ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባት ሴት ነበረች፥ እርስዋም ጐባጣ ነበረች ቀንታም ልትቆም ከቶ አልተቻላትም።
11有一個女人被邪靈附著,病了十八年,彎腰曲背,完全直不起來。
12ኢየሱስም ባያት ጊዜ ጠራትና። አንቺ ሴት፥ ከድካምሽ ተፈትተሻል አላት፥ እጁንም ጫነባት፤
12耶穌看見了,就叫她過來,對她說:“婦人,你脫離這疾病了。”
13ያን ጊዜም ቀጥ አለች፥ እግዚአብሔርንም አመሰገነች።
13耶穌用雙手按在她身上,她立刻直起腰來,頌讚 神。
14የምኵራብ አለቃ ግን ኢየሱስ በሰንበት ስለ ፈወሰ ተቈጥቶ መለሰና ሕዝቡን። ሊሠራባቸው የሚገባ ስድስት ቀኖች አሉ፤ እንግዲህ በእነርሱ መጥታችሁ ተፈወሱ እንጂ በሰንበት አይደለም አለ።
14會堂的主管,因為耶穌在安息日治病,就氣忿忿地對群眾說:“有六天是應當作工的,你們可以在這六天裡來求醫,但在安息日卻不可以。”
15ጌታም መልሶ። እናንተ ግብዞች፥ ከእናንተ እያንዳንዱ በሰንበት በሬውን ወይስ አህያውን ከግርግሙ ፈትቶ ውኃ ሊያጠጣው ይወስደው የለምን?
15主說:“偽君子啊,你們哪一個人在安息日,不從槽那裡解開牛、驢,牽去喝水呢?
16ይህችም የአብርሃም ልጅ ሆና ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ ሰይጣን ያሰራት በሰንበት ቀን ከዚህ እስራት ልትፈታ አይገባምን? አለው።
16何況這個女人是亞伯拉罕的後裔,已經被撒但捆綁了十八年,不應當在安息日解開她的捆綁嗎?”
17ይህንም ሲናገር ሳለ የተቃወሙት ሁሉ አፈሩ፤ ከእርሱም በተደረገው ድንቅ ሁሉ ሕዝቡ ሁሉ ደስ አላቸው።
17他說完了這些話,那些與他為敵的人都慚愧;群眾卻都因他所行一切榮耀的事歡喜。
18እርሱም። የእግዚአብሔር መንግሥት ምን ትመስላለች፥ በምንስ አስመስላታለሁ?
18芥菜種和麵酵的比喻(太13:31~33;可4:30~32)耶穌說:“ 神的國好像甚麼呢?我要把它比作甚麼呢?
19ሰው ወስዶ በአትክልቱ የጣላትን የሰናፍጭ ቅንጣት ትመስላለች፤ አደገችም ታላቅ ዛፍም ሆነች፥ የሰማይ ወፎችም በቅርንጫፎችዋ ሰፈሩ አለ።
19它好像一粒芥菜種,人拿去種在自己的園子裡。它長大了,成為一棵樹,甚至天空的飛鳥也在它的枝頭搭窩。”
20ደግሞም፥ የእግዚአብሔርን መንግሥት በምን አስመስላታለሁ?
20他又說:“我要把 神的國比作甚麼呢?
21ሴት ወስዳ ሁሉ እስኪቦካ ድረስ በሦስት መስፈሪያ ዱቄት የሸሸገችውን እርሾ ትመስላለች አለ።
21它好像麵酵,女人拿去放在三斗麵裡,直到全團發起來。”
22ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ ከተማዎችንና መንደሮችን እያስተማረ ያልፍ ነበር።
22當進窄門(太7:13~14、21~23)耶穌經過各城各鄉,往耶路撒冷去,沿途教導人。
23አንድ ሰውም። ጌታ ሆይ፥ የሚድኑ ጥቂቶች ናቸውን? አለው። እርሱም እንዲህ አላቸው።
23有一個人問他:“主啊,是不是只有很少的人得救呢?”他對眾人說:
24በጠበበው በር ለመግባት ተጋደሉ፤ እላችኋለሁና፥ ብዙዎች ሊገቡ ይፈልጋሉ አይችሉምም።
24“你們應當竭力進窄門!我告訴你們,將來許多人要進去,卻是不能。
25ባለቤቱ ተነሥቶ በሩን ከቈለፈ በኋላ፥ እናንተ በውጭ ቆማችሁ። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ ክፈትልን እያላችሁ በሩን ልታንኳኩ ትጀምራላችሁ እርሱም መልሶ። ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም ይላችኋል።
25等到家主起來關上門,你們站在門外叩門說:‘主啊,給我們開門!’他要回答你們:‘我不知道你們是從哪裡來的。’
26በዚያን ጊዜም። በፊትህ በላን ጠጣንም በአደባባያችንም አስተማርህ ልትሉ ትጀምራላችሁ፤
26那時,你們要說:‘我們在你面前吃過喝過,你也在我們街上教導過人。’
27እርሱም። እላችኋለሁ፥ ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም፤ ሁላችሁ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ይላችኋል።
27他要說:‘我告訴你們,我不曉得你們是從哪裡來的;你們所有作惡的人,離開我去吧!’
28አብርሃምንና ይስሐቅን ያዕቆብንም ነቢያትንም ሁሉ በእግዚአብሔር መንግሥት ባያችሁ ጊዜ፥ እናንተ ግን ወደ ውጭ ተጥላችሁ ስትቀሩ፥ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።
28當你們看見亞伯拉罕、以撒、雅各和眾先知都在 神的國裡的時候,你們卻被趕到外面去,在那裡必要哀哭切齒。
29ከምሥራቅና ከምዕራብም ከሰሜንና ከደቡብም ይመጣሉ፥ በእግዚአብሔርም መንግሥት በማዕድ ይቀመጣሉ።
29從東從南,從西從北,將有人來,在 神的國裡吃飯。
30እነሆም፥ ከኋለኞች ፊተኞች የሚሆኑ አሉ፥ ከፊተኞችም ኋለኞች የሚሆኑ አሉ።
30在後的將要在前,在前的將要在後。”
31በዚያን ሰዓት ከፈሪሳውያን አንዳንዱ ቀርበው። ሄሮድስ ሊገድልህ ይወዳልና ከዚህ ውጣና ሂድ አሉት።
31為耶路撒冷歎息(太23:37~39。參路19:41)就在那時候,有幾個法利賽人來對耶穌說:“你離開這裡走吧!因為希律想要殺你。”
32እንዲህም አላቸው። ሄዳችሁ ለዚያች ቀበሮ። እነሆ፥ ዛሬና ነገ አጋንንትን አወጣለሁ በሽተኞችንም እፈውሳለሁ፥ በሦስተኛውም ቀን እፈጸማለሁ በሉአት።
32他說:“你們去告訴那個狐狸,今天明天我趕鬼醫病,第三天我的事就完成了。
33ዳሩ ግን ነቢይ ከኢየሩሳሌም ውጭ ይጠፋ ዘንድ አይገባውምና ዛሬና ነገ ከነገ በስቲያም ልሄድ ያስፈልገኛል።
33然而,今天明天後天,我必須前行,因為先知不能在耶路撒冷以外喪命。
34ኢየሩሳሌም፥ ኢየሩሳሌም፥ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርስዋ የተላኩትንም የምትወግር፥ ዶሮ ጫጩቶችዋን በክንፎችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ፥ እናንተም አልወደዳችሁም።
34耶路撒冷啊,耶路撒冷,你殺害先知,又用石頭把奉派到你那裡的人打死。我多次想招聚你的兒女,好像母雞招聚小雞到翅膀底下,只是你們不願意。
35እነሆ፥ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል። እላችኋለሁም፥ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ ከእንግዲህ ወዲህ አታዩኝም።
35你看,你們的家必成為荒場留給你們。我告訴你們,從今以後,你們一定見不到我,直等到你們說:‘奉主名來的,是應當稱頌的。’”