Amharic: New Testament

聖經新譯本

Luke

17

1ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ። መሰናክል ግድ ሳይመጣ አይቀርም፥ ነገር ግን መሰናክሉን ለሚያመጣው ወዮለት፤
1饒恕、信心、服事等教訓(太18:6~7、21~22;可9:42)耶穌又對門徒說:“使人犯罪的事是免不了的,但那使人犯罪的人有禍了!
2ከእነዚህ ከታናናሾች አንዱን ከማሰናከል ይልቅ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ባሕር ቢጣል ይጠቅመው ነበር።
2就算拿一塊大磨石拴在他的頸項上,把他沉在深海裡,比他使這小子中的一個犯罪還好。
3ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ወንድምህ ቢበድልህ ገሥጸው፥ ቢጸጸትም ይቅር በለው።
3你們應當謹慎。如果你弟兄得罪你,就勸戒他;他若懊悔,就饒恕他。
4በቀንም ሰባት ጊዜ እንኳ ቢበድልህ በቀንም ሰባት ጊዜ። ተጸጸትሁ እያለ ወደ አንተ ቢመለስ፥ ይቅር በለው።
4如果他一天七次得罪你,又七次回轉,對你說:‘我懊悔了!’你總要饒恕他。”
5ሐዋርያትም ጌታን። እምነት ጨምርልን አሉት።
5使徒對主說:“請你加添我們的信心。”
6ጌታም አለ። የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ሾላ። ተነቅለህ ወደ ባሕር ተተከል ብትሉት፥ ይታዘዝላችሁ ነበር።
6主說:“如果你們有信心像一粒芥菜種,就是對這棵桑樹說:‘拔起根來,栽到海裡去!’它也必聽從你們。
7ከእናንተም የሚያርስ ወይም ከብትን የሚጠብቅ ባሪያ ያለው፥ ከእርሻ ሲመለስ። ወዲያው ቅረብና በማዕድ ተቀመጥ የሚለው ማን ነው?
7“你們中間誰有僕人去耕地或是放羊,從田裡回來,你就對他說:‘快過來坐下吃飯’;
8የምበላውን እራቴን አሰናዳልኝ፥ እስክበላና እስክጠጣ ድረስ ታጥቀህ አገልግለኝ፥ በኋላም አንተ ብላና ጠጣ የሚለው አይደለምን?
8而不對他說:‘給我預備晚餐,束起腰來服事我,等我吃喝完了,你才吃喝’呢?
9ያንን ባሪያ ያዘዘውን ስላደረገ ያመሰግነዋልን?
9僕人作了所吩咐的事,主人還謝謝他嗎?
10እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ። የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል በሉ።
10你們也是這樣,作完一切吩咐你們的事,應該說:‘我們是無用的僕人,我們只作了應分作的。’”
11ወደ ኢየሩሳሌምም ሲሄድ በገሊላና በሰማርያ መካከል አለፈ።
11治好十個痲風病人耶穌往耶路撒冷去,經過撒瑪利亞和加利利的邊境。
12ወደ አንዲት መንደርም ሲገባ በሩቅ የቆሙት አሥር ለምጻሞች ተገናኙት፤
12他走進一個村莊,有十個痲風病人迎面而來,遠遠地站著,
13እነርሱም እየጮኹ። ኢየሱስ ሆይ፥ አቤቱ፥ ማረን አሉ።
13大聲說:“主耶穌啊,可憐我們吧!”
14አይቶም። ሂዱ፥ ራሳችሁን ለካህናት አሳዩ አላቸው።
14他看見了,就對他們說:“你們去給祭司檢查吧。”他們去的時候就潔淨了。
15እነሆም፥ ሲሄዱ ነጹ። ከእነርሱም አንዱ እንደ ተፈወሰ ባየ ጊዜ በታላቅ ድምፅ እግዚአብሔርን እያከበረ ተመለሰ፥
15內中有一個人見自己已經好了,就回來大聲頌讚 神,
16እያመሰገነውም በእግሩ ፊት በግንባሩ ወደቀ፤ እርሱም ሳምራዊ ነበረ።
16在耶穌腳前把臉伏在地上感謝他。他是一個撒瑪利亞人。
17ኢየሱስም መልሶ። አሥሩ አልነጹምን? ዘጠኙስ ወዴት አሉ?
17耶穌說:“潔淨了的不是有十個人嗎?那九個在哪裡?
18ከዚህ ከልዩ ወገን በቀር እግዚአብሔርን ሊያከብሩ የተመለሱ አልተገኙም አለ።
18除了這外族人,再沒有一個回來頌讚 神嗎?”
19እርሱንም። ተነሣና ሂድ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው።
19耶穌就對他說:“起來,走吧,你的信使你痊愈了。”
20ፈሪሳውያንም። የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች ብለው ቢጠይቁት፥ መልሶ። የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም፤
20 神的國降臨的情形(太24:37~41)法利賽人問耶穌:“ 神的國甚麼時候來到呢?”他回答:“ 神的國來到,是眼睛看不見的。
21ደግሞም። እንኋት በዚህ ወይም። እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።
21人不能說:‘看哪!在這裡’,或說:‘在那裡’;因為 神的國就在你們裡面。”
22ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ። ከሰው ልጅ ቀኖች አንዱን ልታዩ የምትመኙበት ወራት ይመጣል አታዩትምም።
22他又對門徒說:“日子將到,你們渴望看見人子的一個日子,卻見不到。
23እነርሱም። እነሆ በዚህ፥ ወይም። እነሆ በዚያ ይሉአችኋል፤ አትሂዱ አትከተሉአቸውም።
23有人會對你們說:‘看哪,在那裡;看哪,在這裡!’你們不要出去,也不要追隨他們。
24መብረቅ በርቆ ከሰማይ በታች ካለ ከአንድ አገር ከሰማይ በታች ወዳለው ወደ ሌላ አገር እንደሚያበራ፥ የሰው ልጅ በቀኑ እንዲህ ይሆናል።
24電光怎樣從天這邊一閃,直照到天那邊,人子在他的日子也是這樣。
25አስቀድሞ ግን ብዙ መከራ እንዲቀበል ከዚህም ትውልድ እንዲጣል ይገባዋል።
25但他必須先受許多苦,被這個世代棄絕。
26በኖኅ ዘመንም እንደ ሆነ፥ በሰው ልጅ ዘመን ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።
26挪亞的時代怎樣,人子的時代也是怎樣。
27ኖኅ ወደ መርከብ እስከ ገባበት ቀን ድረስ፥ ይበሉና ይጠጡ ያገቡና ይጋቡም ነበር፥ የጥፋት ውኃም መጣ ሁሉንም አጠፋ።
27當時人們吃喝嫁娶,直到挪亞進入方舟的那一天,洪水來了,把他們全都滅掉。
28እንዲሁ በሎጥ ዘመን እንደ ሆነ፤ ይበሉ ይጠጡም ይገዙም ይሸጡም ይተክሉም ቤትም ይሠሩ ነበር፤
28在羅得的時代也是這樣,人們吃喝買賣,耕種建造,
29ሎጥ ከሰዶም በወጣበት ቀን ግን ከሰማይ እሳትና ዲን ዘነበ ሁሉንም አጠፋ።
29直到羅得離開所多瑪的那一天,火與硫磺從天上降下來,把他們全都滅掉。
30የሰው ልጅ በሚገለጥበት ቀን እንዲሁ ይሆናል።
30人子顯現的日子也是這樣。
31በዚያም ቀን በሰገነት ያለ በቤቱ ያለውን ዕቃ ሊወስድ አይውረድ፥ እንዲሁም በእርሻ ያለ ወደ ኋላው አይመለስ።
31當那日,人在房頂上,器具在屋裡,不要下來拿;在田裡的,照樣不要回家。
32የሎጥን ሚስት አስቡአት።
32應當記著羅得的妻子的教訓。
33ነፍሱን ሊያድን የሚፈልግ ሁሉ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም የሚያጠፋ ሁሉ በሕይወት ይጠብቃታል።
33凡是想保全生命的,必喪掉生命;凡是犧牲生命的,卻必保全生命。
34እላችኋለሁ፥ በዚያች ሌሊት ሁለት ሰዎች በአንድ አልጋ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
34我告訴你們,當那夜,兩個人在一張床上,一個被接去,一個被撇下。
35ሁለት ሴቶች በአንድ ወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዲቱ ትወሰዳለች ሁለተኛይቱም ትቀራለች።
35兩個女人一起推磨,一個被接去,一個被撇下。”
36ሁለት ሰዎች በእርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
36(有些抄本有第36節:“兩個人在田裡,一個被接去,一個撇下來。”)
37መልሰውም። ጌታ ሆይ፥ ወዴት ነው? አሉት። እርሱም። ሥጋ ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ አላቸው።
37門徒問耶穌:“主啊,這些事會在哪裡發生呢?”主說:“屍首在哪裡,鷹也會聚集在哪裡。”