Amharic: New Testament

聖經新譯本

Luke

18

1ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥
1寡婦與法官的比喻耶穌對他們講一個比喻,論到人必須常常祈禱,不可灰心。
2እንዲህ ሲል። በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ።
2他說:“某城裡有一個法官,不懼怕 神,也不尊敬人。
3በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች። ከባላጋራዬ ፍረድልኝ ትለው ነበር።
3那城裡有一個寡婦,常常來到他那裡,說:‘求你給我伸冤,使我脫離我的對頭!’
4አያሌ ቀንም አልወደደም፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ። ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር፥
4他多次不肯,後來心裡說:‘我雖然不懼怕 神,也不尊敬人,
5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ እፈርድላታለሁ አለ።
5只是因為這寡婦常常來麻煩我,就給她伸冤吧,免得她不斷地來纏擾我。’”
6ጌታም አለ። ዓመፀኛው ዳኛ ያለውን ስሙ።
6主說:“你們聽聽這不義的法官所說的話吧。
7እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሣቸውም ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን?
7難道 神不會為晝夜呼籲他的選民伸冤嗎?難道 神會耽誤他們嗎?
8እላችኋለሁ፥ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል። ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?
8我告訴你們,他要快快地給他們伸冤。然而人子來的時候,在世上找得到這種信心嗎?”
9ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ሌሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፥
9稅吏和法利賽人的禱告耶穌向那些自恃為義、輕視別人的人,講了這個比喻:
10እንዲህ ሲል። ሁለት ሰዎች ሊጸልዩ ወደ መቅደስ ወጡ፥ አንዱ ፈሪሳዊ ሁለተኛውም ቀራጭ።
10“有兩個人上聖殿去祈禱,一個是法利賽人,一個是稅吏。
11ፈሪሳዊም ቆሞ በልቡ ይህን ሲጸልይ። እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ፤
11法利賽人站著,禱告給自己聽,這樣說:‘ 神啊,我感謝你,我不像別人,勒索、不義、姦淫,也不像這個稅吏。
12በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጦማለሁ፥ ከማገኘውም ሁሉ አሥራት አወጣለሁ አለ።
12我一個禮拜禁食兩次,我的一切收入都奉獻十分之一。’
13ቀራጩ ግን በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን። አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር።
13稅吏卻遠遠站著,連舉目望天也不敢,只捶著胸說:‘ 神啊,可憐我這個罪人!’
14እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል።
14我告訴你們,這個人回去,比那個倒算為義了。因為高抬自己的,必要降卑;自己謙卑的,必要升高。”
15እንዲዳስሳቸውም ሕፃናትን ደግሞ ወደ እርሱ አመጡ፤ ደቀ መዛሙርቱም አይተው ገሠጹአቸው።
15讓小孩子到我這裡來(太19:13~15;可10:13~16)有人抱著嬰孩到耶穌面前,要他撫摩他們。門徒看見了,就責備那些人。
16ኢየሱስ ግን ሕፃናትን ወደ እርሱ ጠርቶ። ሕፃናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተዉአቸው አትከልክሉአቸውም፤ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ እነዚህ ላሉት ናትና።
16耶穌卻叫他們過來,說:“讓小孩子到我這裡來,不要禁止他們,因為 神的國正屬於這樣的人。
17እውነት እላችኋለሁ፥ የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደ ሕፃን የማይቀበላት ሁሉ ከቶ አይገባባትም አለ።
17我實在告訴你們,凡不像小孩子一樣接受 神的國的,決不能進去。”
18ከአለቆችም አንዱ። ቸር መምህር፥ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ? ብሎ ጠየቀው።
18有錢的人難進 神的國(太19:16~29;可10:17~30)有一個官長問耶穌:“良善的老師,我當作甚麼,才可以承受永生?”
19ኢየሱስም። ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።
19耶穌對他說:“你為甚麼稱我是良善的呢?除了 神一位以外,沒有良善的。
20ትእዛዛቱን ታውቃለህ፥ አታመንዝር፥ አትግደል፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥ አባትህንና እናትህን አክብር አለው።
20誡命你是知道的:不可姦淫,不可殺人,不可偷盜,不可作假證供,當孝敬父母。”
21እርሱም። ይህን ሁሉ ከሕፃንናቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ አለ።
21他說:“這一切我從小都遵守了。”
22ኢየሱስም ይህን ሰምቶ። አንዲት ገና ቀርታሃለች፤ ያለህን ሁሉ ሽጠህ ለድሆች ስጥ፥ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ፥ መጥተህም ተከተለኝ አለው።
22耶穌聽了,就告訴他:“你還缺少一件,應當變賣你一切所有的,分給窮人,你就必定有財寶在天上,而且你還要來跟從我。”
23እርሱ ግን ይህን ሰምቶ እጅግ ባለ ጠጋ ነበርና ብዙ አዘነ።
23他聽見這話,非常憂愁,因為他十分富有。
24ኢየሱስም ብዙ እንዳዘነ አይቶ። ገንዘብ ላላቸው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት ጭንቅ ይሆናል።
24耶穌見他這樣,就說:“富有的人要進 神的國,是多麼難哪!
25ባለ ጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ሊገባ ይቀላል አለ።
25駱駝穿過針眼,比有錢的人進 神的國還容易呢。”
26የሰሙትም። እንግዲህ ማን ሊድን ይችላል? አሉ።
26聽見的人說:“這樣,誰可以得救呢?”
27እርሱ ግን። በሰው ዘንድ የማይቻል በእግዚአብሔር ዘንድ ይቻላል አለ።
27耶穌說:“人所不能的,在 神卻是可能的。”
28ጴጥሮስም። እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ አለ።
28彼得說:“你看,我們已捨棄自己所有的,跟從你了!”
29እርሱም። እውነት እላችኋለሁ፥ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ቤትን ወይም ወላጆችን ወይም ወንድሞችን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን የተወ፥
29耶穌說:“我實在告訴你們,人為 神的國撇下房屋、妻子、弟兄、父母或兒女,
30በዚህ ዘመን ብዙ እጥፍ በሚመጣውም ዓለም የዘላለምን ሕይወት የማይቀበል ማንም የለም አላቸው።
30沒有不在今世得許多倍,來世得永生的。”
31አሥራ ሁለቱንም ወደ እርሱ አቅርቦ እንዲህ አላቸው። እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፥ ስለ ሰው ልጅም በነቢያት የተጻፈው ሁሉ ይፈጸማል።
31第三次預言受難及復活(太20:17~19;可10:32~34)耶穌把十二門徒帶到一邊,對他們說:“我們現在上耶路撒冷去,先知所寫的一切,都要成就在人子身上。
32ለአሕዛብ አሳልፈው ይሰጡታልና፥ ይዘብቱበትማል ያንገላቱትማል ይተፉበትማል፤
32他要被交給外族人,受戲弄,被凌辱,他們要向他吐唾沫,
33ከገረፉትም በኋላ ይገድሉታል፥ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል።
33鞭打他,殺害他;第三日他要復活。”
34እነርሱም ከዚህ ነገር ምንም አላስተዋሉም፥ ይህም ቃል ተሰውሮባቸው ነበር፥ የተናገረውንም አላወቁም።
34這些話的含義對門徒是隱藏的。他們聽了,一點也不明白,不知道他說的是甚麼。
35ወደ ኢያሪኮም በቀረበ ጊዜ አንድ ዕውር እየለመነ በመንገድ ዳር ተቀምጦ ነበር።
35治好瞎眼的人(太20:29~34;可10:46~52)耶穌走近耶利哥的時候,有一個瞎眼的人坐在路旁討飯,
36ሕዝብም ሲያልፍ ሰምቶ። ይህ ምንድር ነው? ብሎ ጠየቀ።
36他聽見人群經過,就問是甚麼事。
37እነርሱም። የናዝሬቱ ኢየሱስ ያልፋል ብለው አወሩለት።
37別人告訴他,是拿撒勒人耶穌經過。
38እርሱም። የዳዊት ልጅ፥ ኢየሱስ ሆይ፥ ማረኝ እያለ ጮኸ።
38他就喊叫說:“大衛的子孫耶穌啊,可憐我吧!”
39በስተ ፊት ይሄዱ የነበሩትም ዝም እንዲል ገሠጹት፤ እርሱ ግን። የዳዊት ልጅ ሆይ፥ ማረኝ እያለ አብዝቶ ጮኸ።
39在前頭走的人責備他,叫他不要出聲;但他越發喊叫:“大衛的子孫,可憐我吧!”
40ኢየሱስም ቆሞ ወደ እርሱ እንዲያመጡት አዘዘ። በቀረበም ጊዜ። ምን ላደርግልህ ትወዳለህ? ብሎ ጠየቀው።
40耶穌站住,吩咐領他過來。等他走近,就問他:
41እርሱም። ጌታ ሆይ፥ አይ ዘንድ ነው አለው።
41“你要我為你作甚麼?”他說:“主啊,叫我能看見!”
42ኢየሱስም። እይ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው።
42耶穌說:“你就看見吧!你的信使你痊愈了。”
43በዚያን ጊዜም አየ፥ እግዚአብሔንም እያከበረ ተከተለው። ሕዝቡም ሁሉ አይተው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
43他立刻看見了,就跟隨耶穌,頌讚 神。眾人看見這事,也讚美 神。