1ወደ ኢያሪኮም ገብቶ ያልፍ ነበር። እነሆም ዘኬዎስ የሚባል ሰው፥ እርሱም የቀራጮች አለቃ ነበረ፥ ባለ ጠጋም ነበረ።
1稅吏長撒該耶穌進了耶利哥,正經過的時候,
3ኢየሱስንም የትኛው እንደ ሆነ ሊያይ ይፈልግ ነበር፤ ቁመቱም አጭር ነበረና ስለ ሕዝቡ ብዛት አቃተው።
2有一個人名叫撒該,是稅吏長,又很富有。
4በዚያችም መንገድ ያልፍ ዘንድ አለውና ያየው ዘንድ ወደ ፊት ሮጦ በአንድ ሾላ ላይ ወጣ።
3他想看看耶穌是怎麼樣的,因為人多,他又身材矮小,就看不見。
5ኢየሱስም ወደዚያ ስፍራ በደረሰ ጊዜ፥ አሻቅቦ አየና። ዘኬዎስ ሆይ፥ ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛልና ፈጥነህ ውረድ አለው።
4於是他跑到前頭,爬上一棵桑樹,要看看耶穌,因為耶穌就要從那裡經過。
6ፈጥኖም ወረደ በደስታም ተቀበለው።
5耶穌到了那裡,往上一看,對他說:“撒該,快下來,今天我要住在你家裡。”
7ሁሉም አይተው። ከኃጢአተኛ ሰው ጋር ሊውል ገባ ብለው አንጐራጐሩ።
6他就趕快下來,歡歡喜喜地接待耶穌。
8ዘኬዎስ ግን ቆሞ ጌታን። ጌታ ሆይ፥ ካለኝ ሁሉ እኵሌታውን ለድሆች እሰጣለሁ፤ ማንንም በሐሰት ከስሼ እንደ ሆንሁ አራት እጥፍ እመልሳለሁ አለው።
7眾人看見就紛紛議論說:“他竟到罪人家裡去住宿!”
9ኢየሱስም። እርሱ ደግሞ የአብርሃም ልጅ ነውና ዛሬ ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል፤
8撒該站著對主說:“主啊,請看,我要把家財的一半分給窮人,我若敲詐了誰,就還他四倍。”
10የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአለና አለው።
9耶穌說:“今天救恩到了這家,他也是亞伯拉罕的子孫。
11እነርሱም ይህን ሲሰሙ፥ ወደ ኢየሩሳሌም መቅረቡ ስለ ሆነ የእግዚአብሔርም መንግሥት ፈጥኖ ሊገለጥ እንዳለው ስለ መሰላቸው ምሳሌ ጭምር ተናገረ።
10因為人子來,是要尋找拯救失喪的人。”
12ስለዚህም እንዲህ አላቸው። አንድ መኰንን ለራሱ መንግሥትን ይዞ ሊመለሰ ወደ ሩቅ አገር ሄደ።
11十個僕人的比喻(參太25:14~30)眾人聽這些話的時候,因為耶穌已經接近耶路撒冷,又因他們以為 神的國快要出現,他就講了一個比喻,
13አሥር ባሪያዎችንም ጠርቶ አሥር ምናን ሰጣቸውና። እስክመጣ ድረስ ነግዱ አላቸው።
12說:“有一個貴族往遠方去要接受王位,然後回來。
14የአገሩ ሰዎች ግን ይጠሉት ነበርና። ይህ በላያችን ሊነግሥ አንወድም ብለው በኋላው መልክተኞችን ላኩ።
13他叫了自己的十個僕人來,給他們一千銀幣,說:‘你們拿去作生意,等到我回來。’
15መንግሥትንም ይዞ በተመለሰ ጊዜ፥ ገንዘብ የሰጣቸውን እነዚህን ባሪያዎች ነግደው ምን ያህል እንዳተረፉ ያውቅ ዘንድ እንዲጠሩለት አዘዘ።
14他本國的人卻恨他,就派使者跟著去說:‘我們不願意這個人作王統治我們。’
16የፊተኛውም ደርሶ። ጌታ ሆይ፥ ምናንህ አሥር ምናን አተረፈ አለው።
15他得了王位回來,就吩咐把那些領了錢的僕人召來,要知道他們作生意賺了多少。
17እርሱም። መልካም፥ አንተ በጎ ባሪያ፥ በጥቂት የታመንህ ስለ ሆንህ በአሥር ከተማዎች ላይ ሥልጣን ይሁንልህ አለው።
16第一個走過來說:‘主啊,你的一百銀幣,已經賺了一千。’
18ሁለተኛውም መጥቶ። ጌታ ሆይ፥ ምናንህ አምስት ምናን አተረፈ አለው።
17主人說:‘好,良善的僕人,你既然在最小的事上忠心,可以有權管理十座城。’
19ይህንም ደግሞ። አንተም በአምስት ከተማዎች ላይ ሁን አለው።
18第二個來說:‘主啊,你的一百銀幣,已經賺了五百。’
20ሌላውም መጥቶ። ጌታ ሆይ፥ በጨርቅ ጠቅልዬ የጠበቅኋት ምናንህ እነሆ፤
19主人說:‘你可以管理五座城。’
21ፈርቼሃለሁና፥ ጨካኝ ሰው ስለ ሆንህ፤ ያላኖርኸውን ትወስዳለህ ያልዘራኸውንም ታጭዳለህ አለው።
20另一個來說:‘主啊,你看,你的一百銀幣,我一直保存在手巾裡,
22እርሱም። አንተ ክፉ ባሪያ፥ አፍህ በተናገረው እፈርድብሃለሁ። እኔ ያላኖርሁትን የምወስድና ያልዘራሁትን የማጭድ ጨካኝ ሰው እንደ ሆንሁ አወቅህ፤ ምን ነው ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ያልሰጠኸው?
21因為我怕你,你一向是嚴厲的人,沒有存的要提取,沒有種的要收割。’
23እኔም መጥቼ ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር አለው።
22主人說:‘可惡的僕人!我要憑你的口定你的罪。你知道我是嚴厲的人,沒有存的要提取,沒有種的要收割嗎?
24በዚያም ቆመው የነበሩትን። ምናኑን ውሰዱበት አሥሩ ምናን ላለውም ስጡት አላቸው።
23那你為甚麼不把我的錢存入銀行,等我回來的時候,把它連本帶利取回來呢?’
25እነርሱም። ጌታ ሆይ፥ አሥር ምናን አለው አሉት።
24他就對侍衛說:‘奪過他的一百銀幣,給那有一千的。’
26እላችኋለሁ፥ ላለው ሁሉ ይሰጠዋል፥ ከሌለው ግን ያው ያለው ስንኳ ይወሰድበታል።
25他們說:‘主啊,他已經有一千銀幣了。’
27ነገር ግን እነዚያን በላያቸው ልነግሥ ያልወደዱትን ጠላቶቼን ወደዚህ አምጡአቸው በፊቴም እረዱአቸው።
26主人說:‘我告訴你們,凡是有的,還要給他;沒有的,就算他有甚麼也要拿去。
28ይህንም ከተናገረ በኋላ፥ ወደ ኢየሩሳሌም ሲወጣ ይቀድማቸው ነበር።
27至於我那些仇敵,就是不願意我作王統治他們的,把他們拉到這裡來,在我面前殺掉!’”
29ደብረ ዘይትም በሚባል ተራራ አጠገብ ወዳሉት ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ በቀረበ ጊዜ፥ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ላከና።
28騎驢進耶路撒冷(太21:1~9;可11:1~10;約12:12~15)耶穌講完這些話,就往前走,上耶路撒冷去。
30በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ፥ ወደ እርስዋም ገብታችሁ ከሰው ማንም ገና ያልተቀመጠበት ውርንጫ ታስሮ ታገኛላችሁ፥ ፈትታችሁም አምጡት።
29將到伯法其和伯大尼,就在橄欖山那裡,他差派兩個門徒,
31ማንም። ስለ ምን ትፈቱታላችሁ? ብሎ ቢጠይቃችሁ፥ እንዲሁ። ለጌታ ያስፈልገዋል በሉ አላቸው።
30說:“你們往對面的村子裡去,就會看見一頭從來沒有人騎過的小驢,拴在那裡,把牠解開牽來。
32የተላኩትም ሄደው እንዳላቸው አገኙ።
31如果有人問為甚麼解開牠,你們要這樣說:‘主需要牠。’”
33እነርሱም ውርንጫውን ሲፈቱ ጌቶቹ። ውርንጫውን ስለ ምን ትፈቱታላችሁ? አሉአቸውም
32被差的人去了,發現和主所說的一樣。
34እነርሱም። ለጌታ ያስፈልገዋል አሉ።
33他們解開小驢的時候,主人問他們:“你們為甚麼解開牠?”
35ወደ ኢየሱስም አመጡት፥ በውርንጫውም ላይ ልብሳቸውን ጭነው ኢየሱስን አስቀመጡት።
34他們說:“主需要牠。”
36ሲሄድም ልብሳቸውን በመንገድ ያነጥፉ ነበር።
35他們把小驢牽到耶穌那裡,把自己的衣服搭在上面,扶著耶穌上去。
37ወደ ደብረ ዘይት ቍልቍለትም አሁን በቀረበ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ሁላቸው ደስ እያላቸው ተአምራትን ሁሉ ስላዩ በታላቅ ድምፅ እግዚአብሔርን ሊያመሰግኑ ጀምረው።
36耶穌前行的時候,眾人把自己的衣服鋪在路上。
38በጌታ ስም የሚመጣ ንጉሥ የተባረከ ነው፤ በሰማይ ሰላም በአርያምም ክብር አሉ።
37他走近耶路撒冷,快要下橄欖山的時候,全體門徒因為所看見的一切神蹟,就歡樂起來,大聲讚美 神,
39ከሕዝብም መካከል ከፈሪሳውያን አንዳንዱ። መምህር ሆይ፥ ደቀ መዛሙርትህን ገሥጻቸው አሉት።
38說:“奉主名來的王,是應當稱頌的!在天上有和平,在至高之處有榮耀!”
40መልሶም። እላችኋለሁ፥ እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ይጮኻሉ አላቸው።
39群眾中有幾個法利賽人對他說:“先生,責備你的門徒吧!”
41ሲቀርብም ከተማይቱን አይቶ አለቀሰላት፥
40耶穌說:“我告訴你們,他們若不出聲,石頭都要呼叫了。”
42እንዲህ እያለ። ለሰላምሽ የሚሆነውን በዚህ ቀን አንቺስ ስንኳ ብታውቂ፤ አሁን ግን ከዓይንሽ ተሰውሮአል።
41為耶路撒冷哀哭耶穌走近耶路撒冷的時候,看見了城,就為城哀哭,
43ወራት ይመጣብሻልና፥ ጠላቶችሽም ቅጥር ይቀጥሩብሻል ይከቡሻልም በየበኵሉም ያስጨንቁሻል፤
42說:“巴不得你在這日子,知道關於你平安的事,但現在這事在你眼前是隱藏的。
44አንቺንም በአንቺም ውስጥ የሚኖሩትን ልጆችሽን ወደ ታች ይጥላሉ፥ በአንቺ ውስጥም ድንጋይ በድንጋይ ላይ አይተዉም፥ የመጐብኘትሽን ዘመን አላወቅሽምና።
43日子將到,你的仇敵必築壘攻擊你,周圍環繞你,四面困住你,
45ወደ መቅደስም ገብቶ በእርሱ የሚሸጡትን የሚገዙትንም ያወጣ ጀመር፤
44要摧毀你和你裡面的兒女,沒有一塊石頭留在另一塊石頭上面,因為你不知道那眷顧你的時期。”
46እርሱም። ቤቴ የጸሎት ቤት ይሆናል ተብሎ ተጽፎአል፤ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት አላቸው።
45潔淨聖殿(太21:12~17;可11:15~19;約2:13~22)耶穌進了聖殿,就趕走作買賣的人,
47ዕለት ዕለትም በመቅደስ ያስተምር ነበር፤ ነገር ግን የካህናት አለቆችና ጻፎች የሕዝቡ ታላላቆችም ሊገድሉት ይፈልጉ ነበር፥
46對他們說:“經上記著:‘我的殿是禱告的殿’,你們竟把它弄成賊窩了。”
48የሚያደርጉበትንም አጡ፤ ሕዝቡ ሁሉ ሲሰሙት ተንጠልጥለውበት ነበርና።
47他天天在聖殿裡教導人,祭司長、經學家和民間的首領,都想殺害他;
48但他們不知道要怎樣下手,因為眾人都圍著他,聽他的教訓。