Amharic: New Testament

聖經新譯本

Luke

7

1ቃሉን ሁሉ በሕዝብ ጆሮዎች በጨረሰ ጊዜ ወደ ቅፍርናሆም ገባ።
1治好百夫長的僕人(太8:5~13)耶穌向群眾講完這一切話,就進了迦百農。
2አንድ የመቶ አለቃም ነበረ፤ የሚወደውም ባሪያው ታሞ ሊሞት ቀርቦ ነበር።
2有百夫長所重用的一個奴僕,病得快要死了。
3ስለ ኢየሱስም በሰማ ጊዜ የአይሁድን ሽማግሎች ወደ እርሱ ላከና መጥቶ ባሪያውን እንዲያድን ለመነው።
3百夫長聽見耶穌的事,就打發猶太人中幾個長老到他那裡,求他去醫治他的奴僕。
4እነርሱም ወደ ኢየሱስ መጥተው። ይህን ልታደርግለት ይገባዋል፤
4長老們就來見耶穌,懇切地求他說:“你給他行這事,是他配得的,
5ሕዝባችንን ይወዳልና ምኵራብም ራሱ ሠርቶልናል ብለው አጽንተው ለመኑት።
5因為他愛我們的人民,給我們建造會堂。”
6ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ሄደ። አሁንም ወደ ቤቱ በቀረበ ጊዜ የመቶው አለቃ ወዳጆቹን ወደ እርሱ ላከ፤ አለውም። ጌታ ሆይ በቤቴ ጣራ በታች ልትገባ አይገባኝምና አትድከም፤
6耶穌就和他們同去。離那家不遠的時候,百夫長派幾個朋友來說:“主啊,不必勞駕,因為你到舍下來,我實在不敢當,
7ስለዚህም ወደ አንተ ልመጣ እንዲገባኝ ሰውነቴን አልቈጠርሁትም፤ ነገር ግን ቃል ተናገር፥ ብላቴናዬም ይፈወሳል።
7我也覺得沒有資格去見你;只要你說一句話,我的僕人就必好了。
8እኔ ደግሞ ከሌሎች በታች የምገዛ ሰው ነኝ፥ ከእኔም በታች ወታደሮች አሉኝ፥ አንዱንም። ሂድ ብለው ይሄዳል፥ ሌላውንም። ና ብለው ይመጣል፥ ባሪያዬንም። ይህን አድርግ ብለው ያደርጋል።
8因為我自己是在別人的權下,也有兵在我以下;我對這個說:‘去!’他就去;對另一個說:‘來!’他就來;對我的僕人說:‘作這個!’他就作。”
9ኢየሱስም ይህን ሰምቶ በእርሱ ተደነቀ፥ ዘወርም ብሎ ለተከተሉት ሕዝብ። እላችኋለሁ፥ በእስራኤልስ እንኳ እንዲህ ያለ ትልቅ እምነት አላገኘሁም አላቸው።
9耶穌聽見這些話,就很驚奇,轉身對跟隨的眾人說:“我告訴你們,這樣的信心,我在以色列中從來沒有見過。”
10የተላኩትም ወደ ቤት ተመልሰው ባሪያውን ባለ ጤና ሆኖ አገኙት።
10奉派的人回到家裡,見那奴僕已經好了。
11በነገውም ናይን ወደምትባል ወደ አንዲት ከተማ ሄደ፥ ደቀ መዛሙርቱም ብዙ ሕዝብም ከእርሱ ጋር አብረው ሄዱ።
11使拿因城寡婦的兒子復活後來耶穌往拿因城去,與他同去的有門徒和一大群人。
12ወደ ከተማይቱም በር በቀረበ ጊዜ፥ እነሆ፥ የሞተ ሰው ተሸክመው አወጡ፤ እርሱም ለእናቱ አንድ ልጅ ነበረ፥ እርስዋም መበለት ነበረች፥ ብዙም የከተማ ሕዝብ ከእርስዋ ጋር አብረው ነበሩ።
12他走近城門的時候,有人把一個死人抬出來,是個獨生子,他母親又是個寡婦。城裡有一大群人陪著她。
13ጌታም ባያት ጊዜ አዘነላትና። አታልቅሽ አላት።
13主看見了,就憐憫她,對她說:“不要哭!”
14ቀርቦም ቃሬዛውን ነካ፥ የተሸከሙትም ቆሙ፤ አለውም። አንተ ጐበዝ፥ እልሃለሁ፥ ተነሣ።
14於是上前按著槓子,抬的人就站住。他說:“青年人,我吩咐你起來!”
15የሞተውም ቀና ብሎ ተቀመጠ ሊናገርም ጀመረ፥ ለእናቱም ሰጣት።
15那死人就坐起來,開口說話,耶穌就把他交給他母親。
16ሁሉንም ፍርሃት ያዛቸውና። ታላቅ ነቢይ በእኛ መካከል ተነሥቶአል፥ ደግሞ። እግዚአብሔር ሕዝቡን ጐበኘ እያሉ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
16眾人都驚懼,頌讚 神說:“有偉大的先知在我們中間興起來了!”又說:“ 神眷顧他的子民了!”
17ይህም ዝና ስለ እርሱ በይሁዳ ሁሉ በዙሪያውም ባለች አገር ሁሉ ወጣ።
17於是這話傳遍了猶太和周圍各地。
18ደቀ መዛሙርቱም ለዮሐንስ እነዚህን ሁሉ አወሩ።
18約翰派門徒去見耶穌(太11:2~6)約翰的門徒把這一切事告訴約翰。他就叫了兩個門徒,
19ዮሐንስም ከደቀ መዛሙርቱ ሁለት ወደ እርሱ ጠርቶ። የሚመጣው አንተ ነህን ወይስ ሌላውን እንጠብቅ? ብሎ ወደ ኢየሱስ ላከ።
19差他們往主那裡去,說:“你就是那位要來的,還是我們要等別人呢?”
20ሰዎቹም ወደ እርሱ መጥተው። መጥምቁ ዮሐንስ። የሚመጣው አንተ ነህን ወይስ ሌላውን እንጠብቅ? ብሎ ወደ አንተ ላከን አሉት።
20兩人來到耶穌跟前,說:“施洗的約翰差我們來問你:‘你就是那位要來的,還是我們要等別人呢?’”
21በዚያች ሰዓት ከደዌና ከሥቃይ ከክፉዎች መናፍስትም ብዙዎችን ፈወሰ፥ ለብዙ ዕውሮችም ማየትን ሰጠ።
21就在那時候,耶穌治好許多患疾病的、遭災難的、身上有污鬼附著的,並且施恩給瞎眼的,使他們看見。
22ኢየሱስም መልሶ። ሄዳችሁ ያያችሁትን የሰማችሁትንም ለዮሐንስ አውሩለት፤ ዕውሮች ያያሉ፥ አንካሶችም ይሄዳሉ፥ ለምጻሞችም ይነጻሉ፥ ደንቆሮዎችም ይሰማሉ፥ ሙታንም ይነሣሉ፥ ለድሆችም ወንጌል ይሰበካል፤
22耶穌回答他們:“你們回去,把看見和聽見的都告訴約翰,就是瞎的可以看見,跛的可以走路,患痲風的得到潔淨,聾的可以聽見,死人復活,窮人有福音聽。
23በእኔም የማይሰናከለው ሁሉ ብፁዕ ነው አላቸው።
23那不被我絆倒的,就有福了。”
24የዮሐንስ መልክተኞችም ከሄዱ በኋላ፥ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ይናገር ጀመር እንዲህም አለ። ምን ልታዩ ወደ ምድረ በዳ ወጣችሁ? ነፋስ የሚወዘውዘውን ሸምበቆን? ወይስ ምን ልታዩ ወጣችሁ?
24耶穌論約翰(太11:7~19)約翰差來的人走了以後,耶穌對群眾講起約翰來,說:“你們到曠野去,是要看甚麼?被風吹動的蘆葦嗎?
25ቀጭን ልብስ የለበሰውን ሰውን? እነሆ፥ ጌጠኛ ልብስ የሚለብሱና በቅምጥልነት የሚኖሩ በነገሥታት ቤት አሉ።
25你們出去到底要看甚麼?身穿華麗衣服的人嗎?這些衣服華麗,生活奢侈的人,是在王宮裡的。
26ወይስ ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችኋለሁ፥ ከነቢይም የሚበልጠውን።
26那麼,你們出去要看甚麼?先知嗎?我告訴你們,是的。他比先知重要得多了。
27እነሆ፥ መንገድህን በፊትህ የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ ተብሎ የተጻፈለት ይህ ነው።
27聖經所記:‘看哪,我差遣我的使者在你面前,他必在你前頭預備你的道路’,這句話是指著他說的。
28እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም፤ በእግዚአብሔር መንግሥት ግን ከሁሉ የሚያንሰው ይበልጠዋል።
28我告訴你們,婦人所生的,沒有一個比約翰更大,然而在 神的國裡最小的比他還大。”
29የሰሙትም ሕዝብ ሁሉ ቀራጮች እንኳ ሳይቀሩ በዮሐንስ ጥምቀት ተጠምቀው እግዚአብሔርን አጸደቁ፤
29眾人和稅吏受過約翰的洗禮,聽見這話,就稱 神為義。
30ፈሪሳውያንና ሕግ አዋቂዎች ግን በእርሱ ስለ አልተጠመቁ የእግዚአብሔርን ምክር ከራሳቸው ጣሉ።
30但法利賽人和律法師,未受過約翰的洗禮,就拒絕 神對他們的美意。
31እንግዲህ የዚችን ትውልድ ሰዎች በምን አስመስላቸዋለሁ? ማንንስ ይመስላሉ?
31耶穌又說:“我要把這世代的人比作甚麼呢?他們好像甚麼呢?
32በገበያ የሚቀመጡትን ልጆች ይመስላሉ፥ እርስ በርሳቸውም እየተጠራሩ። እንቢልታ ነፋንላችሁ አልዘፈናችሁምም፤ ሙሾ አወጣንላችሁ አላለቀሳችሁምም ይላል።
32他們好像小孩子坐在巿中心,彼此呼叫,說:‘我們給你們吹笛子,你們卻不跳舞;我們唱哀歌,你們也不啼哭。’
33መጥምቁ ዮሐንስ እንጀራ ሳይበላ የወይን ጠጅም ሳይጠጣ መጥቶ ነበርና። ጋኔን አለበት አላችሁት።
33因為施洗的約翰來了,不吃飯,不喝酒,你們說他是鬼附的。
34የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጥቶአልና። እነሆ፥ በላተኛና የወይን ጠጅ ጠጭ፥ የቀራጮችና የኃጢአተኞች ወዳጅ አላችሁት።
34人子來了,又吃又喝,你們說:‘你看,這人貪食好酒,與稅吏和罪人為友。’
35ጥበብም ለልጆችዋ ሁሉ ጸደቀች።
35但 神的智慧,藉著他的兒女就證實是公義的了。”
36ከፈሪሳውያንም አንድ ከእርሱ ጋር ይበላ ዘንድ ለመነው፤ በፈሪሳዊው ቤትም ገብቶ በማዕድ ተቀመጠ።
36赦免犯了罪的女人(太26:6~13;可14:3~9;約12:1~8)有一個法利賽人,請耶穌同他吃飯,他就到法利賽人家去赴席。
37እነሆም በዚያች ከተማ ኃጢአተኛ የነበረች አንዲት ሴት፤ በፈሪሳዊው ቤት በማዕድ እንደ ተቀመጠ ባወቀች ጊዜ፥ ሽቱ የሞላበት የአልባስጥሮስ ቢልቃጥ አመጣች።
37那城裡有一個女人,是個罪人,知道他在法利賽人家裡吃飯,就拿著一瓶香膏,
38በስተ ኋላውም በእግሩ አጠገብ ቆማ እያለቀሰች በእንባዋ እግሩን ታርስ ጀመረች፥ በራስ ጠጕርዋም ታብሰው እግሩንም ትስመው ሽቱም ትቀባው ነበረች።
38站在耶穌背後,挨近他的腳哭,眼淚滴濕他的腳,又用自己的頭髮擦乾,不住地吻他的腳,並且抹上香膏。
39የጠራው ፈሪሳዊም አይቶ። ይህስ ነቢይ ቢሆን፥ ይህች የምትዳስሰው ሴት ማን እንደ ሆነች እንዴትስ እንደ ነበረች ባወቀ ነበር፥ ኃጢአተኛ ናትና ብሎ በልቡ አሰበ።
39請他的法利賽人看見了,心裡說:“這人若是先知,必定知道摸他的是誰,是怎樣的女人,因為她是個罪人!”
40ኢየሱስም መልሶ። ስምዖን ሆይ፥ የምነግርህ ነገር አለኝ አለው። እርሱም። መምህር ሆይ፥ ተናገር አለ።
40耶穌對他說:“西門,我有句話要對你說。”他說:“老師,請說。”
41ለአንድ አበዳሪ ሁለት ተበዳሪዎች ነበሩት በአንዱ አምስት መቶ ዲናር ነበረበት በሁለተኛውም አምሳ።
41耶穌說:“一個債主有兩個債戶,一個欠五百銀幣,一個欠五十。
42የሚከፍሉትም ቢያጡ ለሁለቱም ተወላቸው። እንግዲህ ከእነርሱ አብልጦ የሚወደው ማንኛው ነው?
42他們都無力償還,債主就把兩人豁免了。他們之中哪一個更愛他呢?”
43ስምዖንም መልሶ። ብዙ የተወለቱ ይመስለኛል አለ። እርሱም። በእውነት ፈረድህ አለው።
43西門回答:“我想是那個多得恩免的。”耶穌說:“你判斷對了。”
44ወደ ሴቲቱም ዘወር ብሎ ስምዖንን እንዲህ አለው። ይህችን ሴት ታያለህን? እኔ ወደ ቤትህ ገባሁ፥ ውኃ ስንኳ ለእግሬ አላቀረብህልኝም፤ እርስዋ ግን በእንባዋ እግሬን አራሰች በጠጕርዋም አበሰች።
44於是轉身向著那女人,對西門說:“你看見這女人嗎?我進了你的家,你沒有給我水洗腳,但這女人用眼淚濕了我的腳,用頭髮擦乾。
45አንተ አልሳምኸኝም፤ እርስዋ ግን ከገባሁ ጀምራ እግሬን ከመሳም አላቋረጠችም።
45你沒有和我親嘴;但這女人,自從我進來,就不住地親我的腳。
46አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም፤ እርስዋ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች።
46你沒有用油抹我的頭;但這女人用香膏抹我的腳。
47ስለዚህ እልሃለሁ፥ እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአትዋ ተሰርዮላታል፤ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል።
47所以我告訴你,她許多罪都蒙赦免了,因為她的愛多;那赦免少的,愛就少。”
48እርስዋንም። ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል አላት።
48耶穌就對她說:“你的罪赦免了。”
49ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው። ኃጢአትን እንኳ የሚያስተሰርይ ይህ ማን ነው? ይሉ ጀመር።
49跟他一起吃飯的人心裡說:“這是誰,竟然赦罪呢?”
50ሴቲቱንም። እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ አላት።
50耶穌對那女人說:“你的信救了你,平安地去吧!”