1ከዚህም በኋላ እየሰበከና ስለ እግዚአብሔር መንግሥት የምሥራች እየተናገረ በየከተማይቱ በየመንደሩም ያልፍ ነበር፤
1跟從耶穌的婦女不久,耶穌周遊各城各村講道,宣揚 神的國的福音,和他在一起的有十二個門徒,
2አሥራ ሁለቱም ከእርሱ ጋር ነበሩ፥ ከክፉዎች መናፍስትና ከደዌም ተፈውሰው የነበሩ አንዳንድ ሴቶች፤ እነርሱም ሰባት አጋንንት የወጡላት መግደላዊት የምትባል ማርያም፥
2還有幾個蒙了醫治、脫離污鬼與疾病的婦女,其中有稱為抹大拉的馬利亞,曾有七個鬼從她身上趕出來;
3የሄሮድስ አዛዥ የኩዛ ሚስት ዮሐናም ሶስናም ብዙዎች ሌሎችም ሆነው በገንዘባቸው ያገለግሉት ነበር።
3有希律的管家古撒的妻子約亞拿,又有蘇珊娜,和許多別的婦女,她們都用自己的財物供給耶穌和門徒。
4ብዙ ሕዝብም በተሰበሰቡ ጊዜ ከከተማዎችም ሁሉ ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ በምሳሌ እንዲህ ሲል ተናገራቸው።
4撒種的比喻(太13:2~9;可4:1~9)當時有許多人聚在一起,還有人從各城來到耶穌那裡,他就用比喻說:
5ዘሪ ዘሩን ሊዘራ ወጣ። ሲዘራም አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀ ተረገጠም፥ የሰማይ ወፎችም በሉት።
5“有一個撒種的出去撒種,撒的時候,有的落在路旁,被人踐踏,或給空中的小鳥吃掉。
6ሌላውም በዓለት ላይ ወደቀ፥ በበቀለም ጊዜ እርጥበት ስላልነበረው ደረቀ።
6有的落在石頭地上,一長出來就枯萎了,因為得不著滋潤。
7ሌላውም በእሾህ መካከል ወደቀ፥ እሾሁም አብሮ በቀለና አነቀው።
7有的落在荊棘叢中,荊棘也一齊生長,把它擠住了。
8ሌላውም በመልካም መሬት ላይ ወደቀ፤ በበቀለም ጊዜ መቶ እጥፍ አፈራ። ይህን በተናገረ ጊዜ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ ብሎ ጮኸ።
8有的落在好土裡,就生長起來,結出百倍的果實。”他說了這些話,就大聲說:“有耳可聽的,就應當聽!”
9ደቀ መዛሙርቱም። ይህ ምሳሌ ምንድር ነው? ብለው ጠየቁት።
9用比喻的目的(太13:10~17;可4:10~12)門徒問他這比喻是甚麼意思。
10እርሱም እንዲህ አለ። ለእናንተ የእግዚአብሔርን መንግሥት ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፤ ለሌሎች ግን እያዩ እንዳያዩ እየሰሙም እንዳያስተውሉ በምሳሌ ነው።
10他說:“ 神的國的奧祕,只給你們知道,對別人就用比喻,叫他們看卻看不見,聽卻聽不明白。
11ምሳሌው ይህ ነው። ዘሩ የእግዚአብሔር ቃል ነው።
11解釋撒種的比喻(太13:18~23;可4:13~20)“這比喻是說,種子是 神的道,
12በመንገድ ዳርም ያሉት የሚሰሙ ናቸው፤ ከዚህ በኋላም ዲያብሎስ ይመጣል አምነውም እንዳይድኑ ቃሉን ከልባቸው ይወስዳል።
12那落在路旁的,就是人聽了,魔鬼隨即來到,從他們心裡把道奪去,恐怕他們相信就得救了。
13በዓለት ላይም ያሉት ሲሰሙ ቃሉን በደስታ የሚቀበሉ ናቸው፤ እነርሱም ለጊዜው ብቻ ያምናሉ እንጂ በፈተና ጊዜ የሚክዱ ሥር የሌላቸው ናቸው።
13那落在石頭地上的,就是人聽了,歡歡喜喜地接受,但是沒有根,不過是暫時相信,一旦遭遇試煉,就倒退了。
14በእሾህ መካከልም የወደቀ እነዚህ የሚሰሙት ናቸው፤ መንገዳቸውንም ሄደው በሕይወት ዘመን በአሳብና በባለ ጠግነት ምቾት ይታነቃሉ፥ ሙሉ ፍሬም አያፈሩም።
14那落在荊棘裡的,就是人聽了,走開以後,被今世的憂慮、財富和宴樂擠住了,結不出成熟的子粒來。
15በመልካም መሬት ላይም የወደቀ እነርሱ በመልካምና በበጎ ልብ ቃሉን ሰምተው የሚጠብቁት በመጽናትም ፍሬ የሚያፈሩ ናቸው።
15但那落在好土裡的,就是人用誠實良善的心來聽,把道持守住,忍耐著結出果實。
16መብራትንም አብርቶ በዕቃ የሚከድነው ወይም ከአልጋ በታች የሚያኖረው የለም፥ የሚገቡት ሰዎች ብርሃኑን እንዲያዩ በመቅረዝ ላይ ያኖረዋል እንጂ።
16隱藏的事終必顯露(可4:21~25)“沒有人點燈用器皿蓋上,或放在床底下,而是放在燈臺上,叫進來的人都看得見光。
17የማይገለጥ የተሰወረ የለምና፥ የማይታወቅም ወደ ግልጥም የማይመጣ የተሸሸገ የለም።
17因為沒有甚麼隱藏的事不被顯明,也沒有甚麼掩蓋的事不被人知道而暴露出來。
18እንግዲህ እንዴት እንድትሰሙ ተጠበቁ፤ ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና፥ ከሌለውም ሁሉ፥ ያው ያለው የሚመስለው እንኳ ይወሰድበታል።
18所以你們應當留心怎樣聽,因為凡是有的,還要給他;凡是沒有的,連他自以為有的,也要拿去。”
19እናቱና ወንድሞቹም ወደ እርሱ መጡ፥ ከሕዝቡም ብዛት የተነሣ ሊያገኙት አልተቻላቸውም።
19誰是耶穌的母親和弟兄(太12:46~50;可3:31~35)耶穌的母親和弟弟來到他那裡,因為人多,不能到他跟前。
20እናትህና ወንድሞችህ ሊያዩህ ወድደው በውጭ ቆመዋል ብለው ነገሩት።
20有人轉告耶穌:“你母親和弟弟站在外面要見你。”
21እርሱም መልሶ። እናቴና ወንድሞቼስ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚያደርጉት እነዚህ ናቸው አላቸው።
21他回答他們:“聽了 神的道而遵行的人,才是我的母親,我的弟兄。”
22ከዕለታቱም በአንዱ እርሱ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ታንኳ ገብቶ። ወደ ባሕር ማዶ እንሻገር አላቸው፤ ተነሡም።
22平靜風浪(太8:23~27;可4:35~41)有一天,耶穌和門徒上了船,他對他們說:“我們渡到海那邊去吧。”他們就開了船。
23ሲሄዱም አንቀላፋ። ዓውሎ ነፋስም በባሕር ላይ ወረደ፥ ውኃውም ታንኳይቱን ይሞላ ነበርና ይጨነቁ ነበር።
23船行的時候,他睡著了。海上忽然起了狂風,他們全身濕透,非常危險。
24ቀርበውም። አቤቱ፥ አቤቱ ጠፋን እያሉ አስነሡት። እርሱም ነቅቶ ነፋሱንና የውኃውን ማዕበል ገሠጻቸው፤ ተዉም፥ ጽጥታም ሆነ።
24門徒來叫醒耶穌,說:“主啊!主啊!我們沒命了!”他醒過來,斥責風浪,風浪就止息、平靜了。
25እርሱም። እምነታችሁ የት ነው? አላቸው። ፈርተውም ተደነቁ፥ እርስ በርሳቸውም። እንዲህ ነፋሳትንና ውኃን እንኳ የሚያዝ ለእርሱም የሚታዘዙለት ይህ ማን ነው? አሉ።
25耶穌對他們說:“你們的信心在哪裡?”他們又懼怕、又希奇,彼此說:“這到底是誰?他吩咐風浪,連風浪也聽從他。”
26በገሊላም አንጻር ወዳለችው ወደ ጌርጌሴኖን አገር በታንኳ ደረሱ።
26治好鬼附的格拉森人(太8:28~34;可5:1~20)船到了格拉森人的地區,正在加利利對面,
27ወደ ምድርም በወጣ ጊዜ አጋንንት ያደሩበት አንድ ሰው ከከተማ ወጥቶ ተገናኘው፥ ከብዙ ዘመንም ጀምሮ ልብስ ሳይለብስ በመቃብር እንጂ በቤት አይኖርም ነበር።
27耶穌一上岸,就有城裡一個被鬼附著的人,迎面而來。這人已經很久不穿衣服,不住在家裡,只住在墳墓裡。
28ኢየሱስንም ባየ ጊዜ ጮኾ በፊቱ ተደፋ በታላቅ ድምፅም። የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለኝ? እንዳትሣቀየኝ እለምንሃለሁ አለ።
28他一見耶穌,就俯伏喊叫,大聲說:“至高 神的兒子耶穌,我跟你有甚麼關係呢?求你不要使我受苦。”
29ርኵሱን መንፈስ ከሰውዬው እንዲወጣ ያዘው ነበርና። ብዙ ዘመንም ይዞት ነበርና፥ በሰንሰለትና በእግር ብረትም ታስሮ ይጠበቅ ነበር፤ እስራቱንም ሰብሮ በጋኔኑ ወደ ምድረ በዳ ይነዳ ነበር።
29因為耶穌已經吩咐這污靈從那人身上出來。原來這污靈屢次抓住那人;那人被鐵鍊和腳鍊捆鎖,而且有人看管,他竟掙斷鎖鍊,被鬼趕入曠野。
30ኢየሱስም። ስምህ ማን ነው? ብሎ ጠየቀው። እርሱም ብዙዎች አጋንንት ገብተውበት ነበርና። ሌጌዎን አለው።
30耶穌問他:“你叫甚麼名字?”他說:“群。”因為進到那人裡面的鬼很多。
31ወደ ጥልቁም ሊሄዱ እንዳያዛቸው ለመኑት።
31他們求耶穌,不要趕他們進入無底坑。
32በዚያም በተራራው የብዙ እሪያ መንጋ ይሰማሩ ነበር፤ ወደ እነርሱም ሊገቡ እንዲፈቅድላቸው ለመኑት፤ ፈቀደላቸውም።
32那裡有一大群豬正在山上吃東西。他們求耶穌准他們進入豬群。耶穌准許了,
33አጋንንትም ከሰውዬው ወጥተው ወደ እሪያዎች ገቡ፥ መንጋውም ከአፋፉ ወደ ባሕር ተጣደፉና ሰጠሙ።
33鬼就從那人身上出來,進入豬群,豬群闖下山崖,掉在海裡淹死了。
34እረኞችም የሆነውን ባዩ ጊዜ ሸሽተው በከተማውና በአገሩ አወሩት።
34放豬的看見所發生的事就逃跑,到城裡和各鄉村把這事傳開。
35የሆነውን ነገር ሊያዩ ወጥተውም ወደ ኢየሱስ መጡ፥ አጋንንትም የወጡለትን ሰው ለብሶ ልቡም ተመልሶ በኢየሱስ እግር አጠገብ ተቀምጦ አገኙትና ፈሩ።
35眾人就出來看發生了甚麼事。來到耶穌那裡,看見鬼已經離開的那人,穿著衣服,神志清醒,坐在耶穌腳前,他們就害怕。
36ያዩትም ደግሞ አጋንንት ያደሩበት ሰው እንዴት እንደ ዳነ አወሩላቸው።
36當時看見的人,把被鬼附過的人怎樣得到醫治,說給他們聽。
37በዙሪያውም በጌርጌሴኖን አገር ያሉት ሕዝብ ሁሉ ታላቅ ፍርሃት ይዞአቸዋልና ከእነርሱ እንዲሄድ ለመኑት በታንኳም ገብቶ ተመለሰ።
37格拉森一帶的人,都要求耶穌離開他們,因為他們大大懼怕。他就上船回去了。
38አጋንንት የወጡለት ሰውም ከእርሱ ጋር ይኖር ዘንድ ለመነው፤
38鬼已經離開的那人求耶穌,要跟他在一起;但耶穌打發他回去,說:
39ነገር ግን። ወደ ቤትህ ተመለስ፥ እግዚአብሔር እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረግልህ ንገር ብሎ አሰናበተው። ኢየሱስም እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገለት በከተማው ሁሉ እየሰበከ ሄደ።
39“你回家去,述說 神為你作了怎樣的事。”他就走遍全城,傳講耶穌為他作了怎樣的事。
40ኢየሱስም በተመለሰ ጊዜ ሁሉ ይጠብቁት ነበርና ሕዝቡ ተቀበሉት።
40治好血漏病的女人(太9:18~22;可5:21~34)耶穌回來的時候,眾人歡迎他,因為大家都在等著他。
41እነሆም፥ ኢያኢሮስ የሚባል ሰው መጣ፥ እርሱም የምኵራብ አለቃ ነበረ በኢየሱስም እግር ላይ ወድቆ ወደ ቤቱ እንዲገባ ለመነው፤
41那時,有一個人來了,名叫葉魯,他是一位會堂主管。他俯伏在耶穌腳前,求他往他家裡去,
42አሥራ ሁለት ዓመት የሆናት አንዲት ሴት ልጅ ነበረችውና፤ እርስዋም ለሞት ቀርባ ነበረች። ሲሄድም ሕዝቡ ያጨናንቁት ነበር።
42因為他的獨生女,約十二歲,快要死了。耶穌去的時候,群眾擁擠著他。
43ከአሥራ ሁለት ዓመትም ጀምሮ ደም የሚፈሳት ሴት ነበረች፥ ትዳርዋንም ሁሉ ለባለመድኃኒቶች ከስራ ማንም ሊፈውሳት አልተቻለውም።
43有一個女人,患了十二年的血漏病,在醫生手裡花盡了全部養生的(有些抄本無“在醫生手裡花盡了全部養生的”一句),沒有一個能醫好她。
44በኋላውም ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች፥ የደምዋም ፈሳሽ በዚያን ጊዜ ቆመ።
44她從後面擠來,一摸耶穌的衣裳繸子,血就立刻止住。
45ኢየሱስም። የዳሰሰኝ ማን ነው? አለ። ሁሉም በካዱ ጊዜ፥ ጴጥሮስና ከእርሱ ጋር የነበሩት። አቤቱ፥ ሕዝቡ ያጫንቁሃልና ያጋፉህማል፤ የዳሰሰኝ ማን ነው ትላለህን? አሉ።
45耶穌說:“摸我的是誰?”眾人都不承認。彼得說:“主啊,眾人都擁擠著你。”
46ኢየሱስ ግን። አንድ ሰው ዳስሶኛል፥ ኃይል ከእኔ እንደ ወጣ እኔ አውቃለሁና አለ።
46耶穌說:“必定有人摸我,因為我覺得有能力從我身上出去。”
47ሴቲቱም እንዳልተሰወረች ባየች ጊዜ እየተንቀጠቀጠች መጥታ በፊቱ ተደፋች፥ በምን ምክንያትም እንደ ዳሰሰችው ፈጥናም እንደ ተፈወሰች በሕዝቡ ሁሉ ፊት አወራች።
47那女人見不能隱瞞,就戰戰兢兢地過來,向他俯伏,把摸他的緣故,和怎樣立刻得到醫治,在眾人面前說出來。
48እርሱም። ልጄ ሆይ፥ እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ አላት።
48耶穌對她說:“女兒,你的信使你痊愈了,平安地去吧!”
49እርሱም ገና ሲናገር አንድ ሰው ከምኵራብ አለቃው ቤት መጥቶ። ልጅህ ሞታለች፤ እንግዲህ መምህሩን አታድክም አለ።
49使女孩復活(太9:23~26;可5:35~43)耶穌還在說話的時候,有人從會堂主管家裡來,說:“你的女兒死了,不必再勞動老師了。”
50ኢየሱስ ግን ሰምቶ። አትፍራ፤ እመን ብቻ ትድንማለች ብሎ መለሰለት።
50耶穌聽見就對他說:“不要怕,只要信,她必得痊愈。”
51ወደ ቤትም ሲገባ ከጴጥሮስና ከያዕቆብ ከዮሐንስም ከብላቴናይቱም አባትና እናት በቀር ማንም ከእርሱ ጋር ይገባ ዘንድ አልፈቀደም።
51到了那家,除了彼得、約翰、雅各和女孩的父母以外,他不准任何人同他進屋裡去。
52ሁሉም እያለቀሱላት ዋይ ዋይ ይሉ ነበር። እርሱ ግን። አታልቅሱ፤ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም አለ።
52眾人都在痛哭哀號,他說:“不要哭!她不是死了,而是睡著了。”
53እንደ ሞተችም አውቀው በጣም ሳቁበት።
53他們明知女孩已經死了,就嘲笑他。
54እርሱ ግን እጅዋን ይዞ። አንቺ ብላቴና፥ ተነሺ ብሎ ጮኸ።
54他進去拉著女孩的手,叫她說:“孩子,起來!”
55ነፍስዋም ተመለሰች፥ ፈጥናም ቆመች፥ የምትበላውንም እንዲሰጡአት አዘዘ።
55她的靈魂回來了,她就立刻起來。耶穌吩咐給她東西吃。
56ወላጆችዋም ተገረሙ፤ እርሱ ግን የሆነውን ለማንም እንዳይነግሩ አዘዛቸው።
56她父母非常驚奇。耶穌囑咐他們不要把他所作的事告訴人。