Amharic: New Testament

聖經新譯本

Luke

9

1አሥራ ሁለቱንም ሐዋርያት በአንድነት ወደ እርሱ ጠርቶ በአጋንንት ሁሉ ላይ ደዌንም ይፈውሱ ዘንድ ኃይልና ሥልጣን ሰጣቸው፤
1差遣十二使徒(太10:5~15;可6:7~13)耶穌召齊十二門徒,給他們能力、權柄,制伏一切鬼魔,醫治各樣的疾病,
2የእግዚአብሔርንም መንግሥት እንዲሰብኩና ድውዮችን እንዲፈውሱ ላካቸው፥
2差遣他們去宣講 神的國和醫治病人,
3እንዲህም አላቸው። በትርም ቢሆን፥ ከረጢትም ቢሆን፥ እንጀራም ቢሆን፥ ብርም ቢሆን ለመንገድ ምንም አትያዙ፥ ሁለት እጀ ጠባብም አይሁንላችሁ።
3對他們說:“不要帶著甚麼上路,不要帶手杖,不要帶口袋,不要帶食物,不要帶銀錢,也不要帶兩件衣服。
4በማናቸውም በምትገቡበት ቤት በዚያ ተቀመጡ ከዚያም ውጡ።
4無論進哪一家,就住在那裡,直到離開。
5ማናቸውም የማይቀበሉአችሁ ቢሆኑ፥ ከዚያ ከተማ ወጥታችሁ ምስክር እንዲሆንባቸው ከእግራችሁ ትቢያ አራግፉ።
5凡不接待你們的,你們離開那城的時候,當把腳上的灰塵跺下去,作為反對他們的表示。”
6ወጥተውም ወንጌልን እየሰበኩና በስፍራው ሁሉ እየፈወሱ በየመንደሩ ያልፉ ነበር።
6於是他們就出去,走遍各鄉,傳講福音,到處醫治病人。
7የአራተኛው ክፍል ገዥ ሄሮድስም የተደረገውን ነገር ሁሉ ሰምቶ፥ አንዳንድ ሰዎች።
7希律的困惑(太14:1~2;可6:14~16)分封王希律聽見所發生的一切事,猶豫不定,因為有人說:“約翰從死人中復活了。”
8ዮሐንስ ከሙታን ተነሣ፥ ሌሎችም። ኤልያስ ተገለጠ፥ ሌሎችም። ከቀደሙት ነቢያት አንዱ ተነሥቶአል ይሉ ስለ ነበሩ አመነታ።
8又有人說:“以利亞顯現了。”還有人說:“古時的一位先知復活了。”
9ሄሮድስም። ዮሐንስንስ እኔ ራሱን አስቈረጥሁት፤ ይህ እንዲህ ያለ ነገር የምሰማበት ማን ነው? አለ። ሊያየውም ይሻ ነበር።
9希律說:“約翰已經斬頭了,但這是誰,我怎麼會聽到他這些事呢?”就設法要見他。
10ሐዋርያትም ተመልሰው ያደረጉትን ሁሉ ነገሩት። ከእርሱ ጋርም ወስዶአቸው ቤተ ሳይዳ ከምትባል ከተማ አጠገብ ወደ ምድረ በዳ ለብቻው ፈቀቅ አለ።
10給五千人吃飽的神蹟(太14:13~21;可6:30~44;約6:1~13)使徒們回來,把所作的事報告耶穌。他帶著他們,悄悄地退往伯賽大城去。
11ሕዝቡም አውቀው ተከተሉት፤ ተቀብሎአቸውም ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ይነግራቸው ነበር፥ መፈወስ ያስፈለጋቸውንም ፈወሳቸው።
11群眾知道了,也跟了去。他接待他們,向他們講論 神的國,醫好需要醫治的人。
12ቀኑም ይመሽ ጀመር፤ አሥራ ሁለቱም ቀርበው። በዚህ በምድረ በዳ ነንና በዙሪያችን ወዳሉ መንደሮችና ገጠሮች ሄደው እንዲያድሩና ምግብ እንዲያገኙ ሕዝቡን አሰናብት አሉት።
12天將晚的時候,十二門徒來到他跟前,說:“請解散眾人,好讓他們往周圍的田舍村莊,去找地方住,找東西吃,因為我們這裡是曠野。”
13እርሱ ግን። እናንተ የሚበሉትን ስጡአቸው አላቸው። እነርሱም። ሄደን ለዚህ ሁሉ ሕዝብ ምግብ ካልገዛን፥ ከአምስት እንጀራና ከሁለት ዓሣ የሚበልጥ የለንም አሉት፤
13他說:“你們給他們吃吧!”他們說:“我們所有的,不過是五個餅兩條魚,除非去為這些人另買食物。”
14አምስት ሺህ ሰዎች ያህሉ ነበርና። ለደቀ መዛሙርቱ። በየክፍሉ አምሳ አምሳውን አስቀምጡአቸው አላቸው።
14原來男人就約有五千。他對門徒說:“叫他們一組一組地坐下,每組約五十人。”
15እንዲህም አደረጉ ሁሉንም አስቀመጡአቸው።
15門徒就照他的話,叫眾人坐下。
16አምስቱንም እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ፥ ወደ ሰማይ አሻቅቦ አየና ባረካቸው ቆርሶም ለሕዝቡ እንዲያቀርቡ ለደቀ መዛርሙርቱ ሰጠ።
16耶穌拿起這五個餅,兩條魚,望著天,祝謝了,擘開遞給門徒,擺在眾人面前。
17ሁሉም በልተው ጠገቡ፥ ከእነርሱም የተረፈውን ቍርስራሽ አሥራ ሁለት መሶብ ወሰዱ።
17他們都吃飽了,把剩下的零碎拾起來,裝滿了十二個籃子。
18ለብቻውም ሲጸልይ ደቀ መዛሙርቱ ከእርሱ ጋር ነበሩና። ሕዝቡ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ይላሉ? ብሎ ጠየቃቸው።
18彼得承認耶穌是基督(太16:13~19;可8:27~29)有一次耶穌獨自祈禱的時候,只有門徒和他在一起。他問他們:“人說我是誰?”
19እነርሱም መልሰው። መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም። ኤልያስ፥ ሌሎችም። ከቀደሙት ነቢያት አንዱ ተነሥቶአል ይላሉ አሉት።
19他們回答:“有人說是施洗的約翰,有人說是以利亞,還有人說是古時的一位先知復活了。”
20እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ጴጥሮስም መልሶ። ከእግዚአብሔር የተቀባህ ነህ አለ።
20他又問他們:“你們說我是誰?”彼得回答:“是 神的基督!”
21እርሱ ግን። የሰው ልጅ ብዙ መከራ ሊቀበል በሽማግሌዎችም በካህናት አለቆችም በጻፎችም ሊጣል ሊገደልም በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ይገባዋል ብሎ ለማንም ይህን እንዳይናገሩ አስጠንቅቆ አዘዘ።
21耶穌預言受難及復活(太16:20~28;可8:30~9:1)耶穌鄭重地囑咐他們,不要把這事告訴人。
23ለሁሉም እንዲህ አላቸው። በኋላዬ ሊመጣ የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ዕለት ዕለት ተሸክሞ ይከተለኝ።
22又說:“人子必須受許多苦,被長老、祭司長,和經學家棄絕、殺害,第三日復活。”
24ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታልና፤ ስለ እኔ ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ግን እርሱ ያድናታል።
23耶穌又對眾人說:“如果有人願意跟從我,就當捨己,天天背起他的十字架來跟從我。
25ሰው ዓለሙን ሁሉ አትርፎ ራሱን ቢያጠፋ ወይም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?
24凡是想救自己生命的,必喪掉生命;但為我犧牲自己生命的,必救了生命。
26በእኔና በቃሌ የሚያፍር ሁሉ፥ የሰው ልጅ በክብሩ በአባቱና በቅዱሳን መላእክቱ ክብርም ሲመጣ በእርሱ ያፍርበታል።
25人若賺得全世界,卻喪失自己,或賠上自己,有甚麼好處呢?
27እውነት እላችኋለሁ፥ በዚህ ከሚቆሙት ሰዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት እስኪያዩ ድረስ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ።
26凡是把我和我的道當作可恥的,人子在他與父並聖天使的榮耀裡降臨的時候,也必把他當作可恥的。
28ከዚህም ቃል በኋላ ስምንት ቀን ያህል ቈይቶ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ያዕቆብንም ይዞ ሊጸልይ ወደ ተራራ ወጣ።
27我實在告訴你們,站在這裡的,有人在沒有嘗過死味以前必定要看見 神的國。”
29ሲጸልይም የፊቱ መልክ ተለወጠ፤ ልብሱም ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ።
28在山上改變形象(太17:1~13;可9:2~8)說了這些話以後約有八天,耶穌帶著彼得、約翰和雅各,上山去禱告。
30እነሆም፥ ሁለት ሰዎች እነርሱም ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ይነጋገሩ ነበር፤
29正禱告的時候,他的面貌就改變了,衣服潔白發光。
31በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር።
30忽然有兩個人和他談話,就是摩西和以利亞。
32ነገር ግን ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ከበደባቸው፤ ነቅተው ግን ክብሩንና ከእርሱ ጋር ቆመው የነበሩትን ሁለት ሰዎች አዩ።
31他們在榮光裡顯現,談論他去世的事,就是他在耶路撒冷將要完成的。
33ከእርሱም ሲለዩ ጴጥሮስ ኢየሱስን። አቤቱ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነውና አንድ ለአንተ አንድም ለሙሴ አንድም ለኤልያስ ሦስት ዳሶች እንሥራ አለው፤ የሚለውንም አያውቅም ነበር።
32彼得和同伴都在打盹。醒過來之後,就看見他的榮光,並與他站在一起的那兩個人。
34ይህንም ሲናገር ደመና መጣና ጋረዳቸው፤ ወደ ደመናውም ሲገቡ ሳሉ ፈሩ።
33二人正要離開他的時候,彼得對耶穌說:“主啊,我們在這裡真好!我們可以搭三個帳棚,一個為你,一個為摩西,一個為以利亞。”他根本不知道自己在說甚麼。
35ከደመናውም። የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፥ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።
34他說這話的時候,有一片雲彩籠罩他們,他們入了雲彩,門徒就害怕起來。
36ድምፁም ከመጣ በኋላ ኢየሱስ ብቻውን ሆኖ ተገኘ። እነርሱም ዝም አሉ ካዩትም ነገር በዚያ ወራት ምንም ለማንም አላወሩም።
35有聲音從雲彩裡出來,說:“這是我的兒子,我所揀選的(“這是我的兒子,我所揀選的”有些抄本作“這是我的愛子”),你們要聽從他!”
37በነገውም ከተራራ ሲወርዱ ብዙ ሕዝብ ተገናኙት።
36聲音過了,只見耶穌獨自在那裡。在那些日子,門徒保持緘默,不把所看見的告訴任何人。
38እነሆም፥ ከሕዝቡ አንድ ሰው እንዲህ እያለ ጮኸ። መምህር ሆይ፥ ለእኔ አንድ ልጅ ነውና ልጄን እንድታይልኝ እለምንሃለሁ።
37治好癲癇病的小孩(太17:14~18;可9:14~27)第二天,他們下了山,有一大群人迎面而來。
39እነሆም፥ ጋኔን ይይዘዋል፥ ድንገትም ይጮኻል አረፋም እያስደፈቀው ያንፈራግጠዋል፥ እየቀጠቀጠም በጭንቅ ይለቀዋል፤
38在人群中有一個人喊叫說:“老師,求你憐憫我的兒子,因為他是我的獨生子。
40ደቀ መዛሙርትህንም እንዲያወጡት ለመንሁ፥ አልቻሉምም።
39你看,污靈一抓住他,他就忽然喊叫,並且抽瘋,口吐白沫;污靈又折磨糟踐他,不肯放過他。
41ኢየሱስም መልሶ። እናንተ የማታምን ጠማማ ትውልድ፥ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ልጅህን ወደዚህ አምጣው አለ።
40我求過你的門徒,把他趕出去,他們卻辦不到。”
42ሲቀርብም ጋኔኑ ጣለውና አንፈራገጠው፤ ኢየሱስ ግን ርኵሱን መንፈስ ገሥጾ ብላቴናውን ፈወሰው ለአባቱም መለሰው።
41耶穌說:“唉!這不信又乖謬的世代啊!我跟你們在一起,忍受你們,要到幾時呢?把你兒子帶到這裡來吧!”
43ሁሉም ከእግዚአብሔር ታላቅነት የተነሣ ተገረሙ። ሁሉም ኢየሱስ ባደረገው ሁሉ ሲደነቁ፥
42那孩子正走過來的時候,污鬼把他摔倒,使他重重地抽瘋。耶穌斥責那污靈,把孩子醫好,交給他父親。
44ለደቀ መዛሙርቱ። የሰው ልጅ በሰው እጅ ይሰጥ ዘንድ አለውና እናንተ ይህን ቃል በጆሮአችሁ አኑሩ አለ።
43眾人都驚奇 神的大能。眾人還在希奇耶穌所作的這一切時,他對門徒說:
45እነርሱ ግን ይህን ነገር አላስተዋሉም፥ እንዳይገባቸውም ተሰውሮባቸው ነበር፤ ስለዚህ ነገርም እንዳይጠይቁት ፈሩ።
44第二次預言受難及復活(太17:22~23;可9:30~32)“你們要把這些話存在心裡:人子將要被交在人的手裡。”
46ከእነርሱም ማን እንዲበልጥ ክርክር ተነሣባቸው።
45門徒不明白這話,因為這話的意思是隱藏的,不讓他們明白,他們也不敢問。
47ኢየሱስም የልባቸውን አሳብ አውቆ ሕፃንን ያዘ፤ በአጠገቡም አቁሞ።
46門徒爭論誰最大(太18:1~5;可9:33~40)後來,門徒起了意見,爭論誰是最大的。
48ማንም ይህን ሕፃን በስሜ የሚቀበል እኔን ይቀበላል፤ የሚቀበለኝም ሁሉ የላከኝን ይቀበላል፤ ከሁላችሁ የሚያንስ እርሱ ታላቅ ነውና አላቸው።
47耶穌看出他們的心意,就領了一個小孩子來,叫他站在自己旁邊,
49ዮሐንስም መልሶ። አቤቱ፥ አንድ ሰው በስምህ አጋንንትን ሲያወጣ አየነው፥ ከእኛ ጋርም ስለማይከተል ከለከልነው አለው።
48對他們說:“凡因我的名接待這小孩子的,就是接待我;凡接待我的,就是接待那差我來的。誰是你們中間最小的,那人就是最大的。”
50ኢየሱስ ግን። የማይቃወማችሁ ከእናንተ ጋር ነውና አትከልክሉት አለው።
49約翰說:“主,我們看見有一個人奉你的名趕鬼,就禁止他,因為他不和我們一起跟從你。”
51የሚወጣበትም ወራት በቀረበ ጊዜ ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ፊቱን አቀና፥
50耶穌說:“不要禁止他,因為不反對你們的,就是贊成你們的。”
52በፊቱም መልክተኞችን ሰደደ። ሄደውም ሊያሰናዱለት ወደ አንድ ወደ ሳምራውያን መንደር ገቡ፤
51撒瑪利亞人不接待主耶穌被接上升的日子快到了,他就決意向耶路撒冷去,
53ፊቱም ወደ ኢየሩሳሌም እንደሚሄድ ስለ ነበረ አልተቀበሉትም።
52並且差遣使者走在前頭;他們去了,進入撒瑪利亞的一個村莊,要為他預備。
54ደቀ መዛሙርቱም ያዕቆብና ዮሐንስ አይተው። ጌታ ሆይ፥ ኤልያስ ደግሞ እንዳደረገ እሳት ከሰማይ ወርዶ ያጥፋቸው እንል ዘንድ ትወዳለህን? አሉት።
53那裡的人不接待他,因為他面向著耶路撒冷走。
55እርሱ ግን ዘወር ብሎ ገሠጻቸውና። ምን ዓይነት መንፈስ እንደ ሆነላችሁ አታውቁም፤
54他的門徒雅各、約翰看見了,就說:“主啊,你要我們吩咐火從天降下來,燒滅他們嗎?”
56የሰው ልጅ የሰውን ነፍስ ሊያድን እንጂ ሊያጠፋ አልመጣም አለ። ወደ ሌላ መንደርም ሄዱ።
55耶穌就轉過身來,責備他們,
57እነርሱም በመንገድ ሲሄዱ አንድ ሰው። ጌታ ሆይ፥ ወደ ምትሄድበት ሁሉ እከተልሃለሁ አለው።
56然後他們就往別的村莊去了。
58ኢየሱስም። ለቀበሮዎች ጕድጓድ ለሰማይም ወፎች መሳፈሪያ አላቸው፥ ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም አለው።
57要求跟從耶穌(太8:19~22)他們走路的時候,有一個人對他說:“你無論往哪裡去,我都要跟從你!”
59ሌላውንም። ተከተለኝ አለው። እርሱ ግን። ጌታ ሆይ፥ አስቀድሜ ልሂድና አባቴን እቀብር ዘንድ ፍቀድልኝ አለ።
58耶穌說:“狐狸有洞,天空的飛鳥有窩,人子卻沒有棲身的地方。”
60ኢየሱስም። ሙታናቸውን እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው፤ አንተስ ሄደህ የእግዚአብሔርን መንግሥት ስበክ አለው።
59他對另一個人說:“你跟從我吧!”那人說:“主啊,請准我先回去安葬我的父親吧。”
61ደግሞ ሌላው። ጌታ ሆይ፥ እከተልሃለሁ፤ ነገር ግን አስቀድሜ ከቤቴ ሰዎች እንድሰናበት ፍቀድልኝ አለ።
60耶穌說:“讓死人去埋葬他們的死人,你應該去傳揚 神的國。”
62ኢየሱስ ግን። ማንም ዕርፍ በእጁ ይዞ ወደ ኋላ የሚመለከት ለእግዚአብሔር መንግሥት የተገባ አይደለም አለው።
61又有一個人說:“主,我要跟從你,但容我先回去,向家人道別。”
62耶穌說:“手扶著犁向後看的,不適合進 神的國。”