1እርሱም ከመቅደስ ሲወጣ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ። መምህር ሆይ፥ እንዴት ያሉ ድንጋይዎችና እንዴት ያሉ ሕንጻዎች እንደ ሆኑ እይ አለው።
1預言聖殿被毀(太24:1~2;路21:5~6)耶穌從殿裡出來的時候,有一個門徒對他說:“老師,請看,這是多麼美好的石頭!多麼美好的建築!”
2ኢየሱስም መልሶ። እነዚህን ታላላቅ ሕንጻዎች ታያለህን? ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አለው።
2耶穌對他說:“你看見這些偉大的建築嗎?將來必沒有一塊石頭留在另一塊石頭上面,每一塊都要拆下來。”
3በመቅደስም ትይዩ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ጴጥሮስና ያዕቆብ ዮሐንስም እንድርያስም።
3這世代終結的預兆(太24:3~14;路21:7~19)耶穌在橄欖山上,面對聖殿坐著,彼得、雅各、約翰和安得烈私下問他:
4ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? ይህስ ሁሉ ይፈጸም ዘንድ እንዳለው ምልክቱ ምንድር ነው? ብለው ለብቻቸው ጠየቁት።
4“請告訴我們,甚麼時候會有這些事呢?這一切事將要成就的時候有甚麼預兆呢?”
5ኢየሱስም መልሶ እንዲህ ይላቸው ጀመር። ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ።
5耶穌就告訴他們說:“你們要小心,不要被人迷惑。
6ብዙዎች። እኔ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፥ ብዙዎችንም ያስታሉ።
6有許多人要來,假冒我的名說‘我就是基督’,並且要迷惑許多的人。
7ጦርንም የጦርንም ወሬ በሰማችሁ ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና፥ ነገር ግን መጨረሻው ገና ነው።
7你們聽見戰爭和戰爭的風聲,也不要驚慌,這是免不了的,不過,結局還沒有到。
8ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፤ በልዩ ልዩ ስፍራ የምድር መናወጥ ይሆናል፤ ራብ ይሆናል፤ እነዚህ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።
8一個民族要起來攻打另一個民族,一個國家要起來攻打另一個國家,到處要有地震,有饑荒,這些不過是痛苦的開始。
9እናንተ ግን ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤ ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል በምኵራብም ትገረፋላችሁ ምስክርም ይሆንባቸው ዘንድ ስለ እኔ በገዥዎችና በነገሥታት ፊት ትቆማላችሁ።
9但你們要小心!因為人要把你們交給公議會,你們要在會堂裡被鞭打,又要為我的緣故站在總督和君王面前,向他們作見證。
10አስቀድሞም ወንጌል ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበክ ዘንድ ይገባል።
10然而福音必須先傳給萬民。
11ሲጐትቱአችሁና አሳልፈው ሲሰጡአችሁም ምን እንድትናገሩ አስቀድማችሁ አትጨነቁ፥ ዳሩ ግን በዚያች ሰዓት የሚሰጣችሁን ተናገሩ፤ የሚነግረው መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እናንተ አይደላችሁምና።
11人把你們捉去送官的時候,用不著預先思慮要說甚麼,到那時候賜給你們甚麼話,你們就說甚麼,因為說話的不是你們,而是聖靈。
12ወንድምም ወንድሙን አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ። ይገድሉአቸውማል፤
12弟兄要出賣弟兄,父親要出賣兒子,甚至把他們置於死地;兒女要悖逆父母,害死他們。
13በሁሉም ዘንድ ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።
13你們為我的名,要被眾人恨惡,然而堅忍到底的必然得救。
14ነገር ግን በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋት ርኵሰት በማይገባው ስፍራ ቆሞ ብታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥ በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፥
14大災難的日子(太24:15~28;路21:20~24)“當你們看見‘那造成荒涼的可憎者’,站在不該站的地方(讀者必須領悟),那時,住在猶太的應當逃到山上;
15በሰገነትም ያለ ወደ ቤት አይውረድ ከቤቱም አንዳች ይወስድ ዘንድ አይግባ፥
15在房頂的不要下來,也不要進到屋子裡拿甚麼東西;
16በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ።
16在田裡的也不要回去取衣服。
17በዚያን ወራትም ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው።
17當那些日子,懷孕的和乳養孩子的有禍了!
18ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፤
18你們應當祈求,不要讓這些事在冬天發生。
19በዚያን ወራት እግዚአብሔር ከፈጠረው ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያልሆነ ደግሞም የማይሆን የመከራ ዓይነት ይሆናልና።
19因為那些日子必有災難,這是從 神創世的開始到現在未曾有過的,以後也必不會再有。
20ጌታስ ወራቶቹን ባያሳጥር፥ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም፤ ነገር ግን ስለ መረጣቸው ምርጦች ወራቶቹን አሳጠረ።
20如果不是主減少那些日子,沒有一個人可以存活;但是為了自己的選民,他必使那些日子減少。
21በዚያን ጊዜም ማንም። እነሆ፥ ክርስቶስ ከዚህ አለ፥ ወይም። እነሆ፥ ከዚያ አለ ቢላችሁ አትመኑ፤
21那時,如果有人對你們說:‘看哪,基督在這裡!看哪,他在那裡!’你們不要信。
22ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ ያስቱ ዘንድ ምልክትና ድንቅ ያደርጋሉ።
22因為必有假基督和假先知出現,行神蹟和奇事,如果可以的話,連選民也要迷惑了。
23እናንተ ግን ተጠንቀቁ፤ እነሆ፥ አስቀድሜ ሁሉን ነገርኋችሁ።
23所以你們應當小心!我已經事先把一切都告訴你們了。
24በዚያን ወራት ግን ከዚያ መከራ በኋላ ፀሐይ ይጨልማል ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፥
24人子必駕雲降臨(太24:29~35;路21:25~33)“當那些日子,在那災難以後,太陽就變黑了,月亮也不發光,
25ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፥ የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ።
25眾星從天墜落,天上的萬象震動。
26በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በብዙ ኃይልና ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል።
26那時,他們要看見人子,滿有能力和榮耀,駕著雲降臨;
27በዚያን ጊዜም መላእክትን ይልካል ከአራቱ ነፋሳትም ከምድር ዳርቻ እስከ ሰማይ ዳርቻ የተመረጡትን ይሰበስባቸዋል።
27他要差派天使,把他的選民從四方,從地極直到天邊,都招聚來。
28ምሳሌውንም ከበለስ ተማሩ፤ ጫፍዋ ሲለሰልስ ቅጠልዋም ሲያቈጠቍጥ፥ ያን ጊዜ በጋ እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ፤
28“你們應該從無花果樹學個功課:樹枝發出嫩芽長出葉子的時候,你們就知道夏天近了。
29እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህን ሁሉ መሆኑን ስታዩ ቀርቦ በደጅ እንደ ሆነ እወቁ።
29同樣,你們甚麼時候看見這些事發生,就知道他已經近在門口了。
30እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም።
30我實在告訴你們,這一切都必會發生,然後這世代才會過去。
31ሰማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን አያልፍም።
31天地都要過去,但我的話決不會廢去。
32ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን ከአባት በቀር የሚያውቅ የለም።
32警醒準備(太24:36~51;路21:34~36)“至於那日子和時間,沒有人知道,連天上的天使和子也不知道,只有父知道。
33ጊዜው መቼ እንዲሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፤ ጸልዩም።
33你們要小心,要警醒,因為你們不知道那日期甚麼時候來到。
34ቤቱን ትቶ ወደ ሌላ አገር እንደ ሄደ ሰው ነው፥ ለባሮቹም ሥልጣን ለእያንዳንዱም ሥራውን ሰጥቶ በረኛውን እንዲተጋ አዘዘ።
34這就像一個人出外遠行,把責任(“責任”原文作“權柄”)一一地交給他的僕人,又吩咐看門的要警醒。
35እንግዲህ በማታ ቢሆን ወይም በእኩለ ሌሊት ወይም ዶሮ ሲጮኽ ወይም በማለዳ ቢሆን ባለቤቱ መቼ እንዲመጣ አታውቁምና
35所以你們要警醒,因為你們不知道家主甚麼時候來到,也許在黃昏,也許在半夜,也許在雞叫時,也許在清晨。
36ድንገት መጥቶ ተኝታችሁ እንዳያገኛችሁ ስለዚህ ትጉ።
36恐怕他忽然來到,發現你們正在睡覺。
37ለእናንተም የምነግራችሁ ለሁሉ እላለሁ፤ ትጉ።
37我對你們所說的話,也是對眾人說的,‘你們要警醒’。”