1ሰንበትም ካለፈ በኋላ መግደላዊት ማርያም የያዕቆብም እናት ማርያም ሰሎሜም መጥተው ሊቀቡት ሽቱ ገዙ።
1耶穌復活(太28:1~8;路24:1~10;約20:1~10)過了安息日,抹大拉的馬利亞、雅各的母親馬利亞和撒羅米,買了香膏,要去膏耶穌。
2ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን እጅግ በማለዳ ፀሐይ ከወጣ በኋላ ወደ መቃብር መጡ።
2禮拜日的大清早,出太陽的時候,她們就來到墳墓那裡,
3እርስ በርሳቸውም። ድንጋዩን ከመቃብር ደጃፍ ማን ያንከባልልልናል? ይባባሉ ነበር፤
3彼此說:“誰可以給我們輥開墓門的石頭呢?”
4ድንጋዩ እጅግ ትልቅ ነበርና፤ አሻቅበውም አይተው ድንጋዩ ተንከባሎ እንደ ነበር ተመለከቱ።
4原來那塊石頭非常大,她們抬頭一看,卻見石頭已經輥開了。
5ወደ መቃብሩም ገብተው ነጭ ልብስ የተጎናጸፈ ጎልማሳ በቀኝ በኩል ተቀምጦ አዩና ደነገጡ።
5她們進了墳墓,看見一位身穿白袍的青年,坐在右邊,就非常驚恐。
6እርሱ ግን። አትደንግጡ፤ የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ትፈልጋላችሁ፤ ተነሥቶአል፥ በዚህ የለም፤ እነሆ እርሱን ያኖሩበት ስፍራ።
6那青年對她們說:“不要驚慌!你們尋找那釘十字架的拿撒勒人耶穌,他不在這裡,已經復活了;請看他們安放他的地方。
7ነገር ግን ሄዳችሁ ለደቀ መዛሙርቱ ለጴጥሮስም። ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል፤ እንደ ነገራችሁ በዚያ ታዩታላችሁ ብላችሁ ንገሩአቸው አላቸው።
7你們去告訴他的門徒和彼得:他要比你們先到加利利去,你們在那裡必定看見他,正如他從前告訴你們的。”
8መንቀጥቀጥና መደንገጥ ይዞአቸው ነበርና ወጥተው ከመቃብር ሸሹ፤ ይፈሩ ነበርና ለማንም አንዳች አልነገሩም። እነርሱም ያዘዛቸውን ሁሉ ለጴጥሮስና ከእርሱ ጋር ላሉት በአጭሩ ተናገሩ። ከዚህም በኋላ ኢየሱስ ራሱ ለዘላለም ድኅነት የሆነውን የማይለወጠውን ቅዱስ ወንጌል ከፀሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያው ድረስ በእጃቸው ላከው።
8因為驚恐戰慄,她們一從墳墓出來就逃跑;由於害怕,她們甚麼也沒有告訴人。(有些抄本無第9至20節)
9ከሳምንቱም በመጀመሪያው ቀን ማልዶ በተነሣ ጊዜ፥ አስቀድሞ ሰባት አጋንንት ላወጣላት ለመግደላዊት ማርያም ታየ።
9主向抹大拉的馬利亞顯現(約20:11~18)禮拜日的清早,耶穌復活了,先向抹大拉的馬利亞顯現,耶穌曾經從她身上趕出七個鬼。
10እርስዋ ሄዳ ከእርሱ ጋር ሆነው ለነበሩት ሲያዝኑና ሲያለቅሱ ሳሉ አወራችላቸው፤
10她就去告訴那些向來和耶穌在一起的人,那時他們正在悲哀哭泣。
11እነርሱም ሕያው እንደ ሆነ ለእርስዋም እንደ ታያት ሲሰሙ አላመኑም።
11他們聽見耶穌活了,又被馬利亞看見了,卻不相信。
12ከዚህም በኋላ ከእነርሱ ለሁለቱ ወደ ባላገር ሲሄዱ በመንገድ በሌላ መልክ ተገለጠ፤
12向兩個門徒顯現(路24:13~35)這事以後,門徒中有兩個人往鄉下去,正走路的時候,耶穌用另外的形象,向他們顯現,
13እነርሱም ሄደው ለሌሎቹ አወሩ፤ እነዚያንም ደግሞ አላመኑአቸውም።
13他們就去告訴其他的人,那些人也不相信。
14ኋላም በማዕድ ተቀምጠው ሳሉ ለአሥራ አንዱ ተገለጠ፥ ተነሥቶም ያዩትን ስላላመኑአቸው አለማመናቸውንና የልባቸውን ጥንካሬ ነቀፈ።
14吩咐門徒往普天下傳福音(太28:16~20;路24:36~49;約20:19~23;徒1:6~8)後來,十一個門徒吃飯的時候,耶穌向他們顯現,責備他們的不信和心硬,因為他們不信那些在他復活以後見過他的人。
15እንዲህም አላቸው። ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።
15他又對他們說:“你們到全世界去,向所有的人傳福音。
16ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።
16信而受洗的必定得救,不信的必被定罪。
17ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ፥
17信的人必有神蹟隨著他們,就是奉我的名趕鬼,用新方言說話,
18የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም፤ እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ።
18用手握蛇,喝了甚麼毒物也不受害,手按病人就必好了。”
19ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ።
19耶穌升天(路24:50~53;徒1:9~11)主耶穌向門徒講完了話,就被接到天上,坐在 神的右邊。
20እነርሱም ወጥተው በየስፍራው ሁሉ ሰበኩ፥ ጌታም ከእነርሱ ጋር ይሠራ ነበር፥ በሚከተሉትም ምልክቶች ቃሉን ያጸና ነበር።
20門徒出去,到處傳揚福音,主和他們同工,藉著相隨的神蹟,證實所傳的道。(有少數抄本有〔較短的結語〕:9“那些婦女把耶穌所吩咐的一切都告訴彼得和他的同伴。10這些事以後,耶穌藉著他們親自把那神聖不朽、永遠救恩的信息從東到西傳揚出去。阿們。”放在第8節之後;另有少數抄本把它放在第20節之後。)