1በዚያን ጊዜ ጻፎችና ፈሪሳውያን ከኢየሩሳሌም ወደ ኢየሱስ ቀረቡና።
1不可因傳統廢棄 神的誡命(可7:1~23)有法利賽人和經學家從耶路撒冷前來,問耶穌:
2ደቀ መዛሙርትህ ስለ ምን የሽማግሎችን ወግ ይተላለፋሉ? እንጀራ ሲበሉ እጃቸውን አይታጠቡምና አሉት።
2“你的門徒為甚麼違背古人的傳統,在飯前不洗手呢?”
3እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው። እናንተስ ስለ ወጋችሁ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ስለ ምን ትተላለፋላችሁ?
3耶穌回答:“你們又為甚麼因你們的傳統,違背 神的誡命呢?
4እግዚአብሔር። አባትህንና እናትህን አክብር፤ ደግሞ። አባቱን ወይም እናቱን የሰደበ ፈጽሞ ይሙት ብሎአልና፤
4 神說:‘當孝敬父母’,又說:‘咒罵父母的必被處死’。
5እናንተ ግን። አባቱን ወይም እናቱን። ከእኔ የምትጠቀምበት መባ ነው የሚል ሁሉ፥
5你們卻說:‘人若對父母說:“我應該給你們的,已經作了獻給 神的禮物”,
6አባቱን ወይም እናቱን አያከብርም ትላላችሁ፤ ስለ ወጋችሁም የእግዚአብሔርን ቃል ሻራችሁ።
6他就可以不孝敬父母了。’你們因為你們的傳統,就廢棄了 神的話。
7እናንተ ግብዞች፥ ኢሳይያስ ስለ እናንተ።
7偽君子啊,以賽亞指著你們說的預言說得好:
8ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤
8‘這人民用嘴唇尊敬我,心卻遠離我;
9የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ብሎ በእውነት ትንቢት ተናገረ።
9他們把人的規條當作道理去教導人,所以拜我也是徒然。’”
10ሕዝቡንም ጠርቶ። ስሙ አስተውሉም፤
10耶穌叫群眾前來,對他們說:“你們要聽,也要明白。
11ሰውን የሚያረክሰው ወደ አፍ የሚገባ አይደለም፥ ከአፍ የሚወጣው ግን ሰውን የሚያረክሰው ይህ ነው አላቸው።
11進到口裡的不能使人污穢,只有從口裡出來的,才能使人污穢。”
12በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ቀርበው። ፈሪሳውያን ይህን ቃል ሰምተው እንደ ተሰናከሉ አወቅህን? አሉት።
12門徒前來告訴他:“法利賽人聽了這話很生氣,你知道嗎?”
13እርሱ ግን መልሶ። የሰማዩ አባቴ ያልተከለው ተክል ሁሉ ይነቀላል።
13耶穌說:“所有不是我天父栽種的植物,都要連根拔起來。
14ተዉአቸው፤ ዕውሮችን የሚመሩ ዕውሮች ናቸው፤ ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ አለ።
14由得他們吧!他們是瞎眼的,卻作了嚮導;如果瞎子領瞎子,二人都會跌進坑裡。”
15ጴጥሮስም መልሶ። ምሳሌውን ተርጕምልን አለው።
15彼得說:“請你給我們解釋這個比喻吧。”
16ኢየሱስም እንዲህ አለ። እናንተ ደግሞ እስካሁን የማታስተውሉ ናችሁን?
16耶穌說:“你們還是不明白嗎?
17ወደ አፍ የሚገባ ሁሉ ወደ ሆድ አልፎ ወደ እዳሪ እንዲጣል አትመለከቱምን?
17難道不知道一切進到口裡的,是進到肚腹,然後排泄到外面去嗎?
18ከአፍ የሚወጣ ግን ከልብ ይወጣል፥ ሰውንም የሚያረክሰው ያ ነው።
18但從口裡出來的,是發自內心,才會使人污穢。
19ከልብ ክፉ አሳብ፥ መግደል፥ ምንዝርነት፥ ዝሙት፥ መስረቅ፥ በውሸት መመስከር፥ ስድብ ይወጣልና።
19因為從心裡出來的,有惡念、兇殺、姦淫、淫亂、偷盜、假見證和毀謗。
20ሰውን የሚያረክሰው ይህ ነው እንጂ፥ ባልታጠበ እጅ መብላትስ ሰውን አያረክሰውም።
20這些才會使人污穢,不洗手吃飯卻不會這樣。”
21ኢየሱስም ከዚያ ወጥቶ ወደ ጢሮስና ወደ ሲዶና አገር ሄደ።
21迦南婦人的信心(可7:24~30)耶穌離開那裡,來到推羅、西頓境內。
22እነሆም፥ ከነናዊት ሴት ከዚያ አገር ወጥታ። ጌታ ሆይ፥ የዳዊት ልጅ፥ ማረኝ፤ ልጄን ጋኔን ክፉኛ ይዞአታል ብላ ጮኸች።
22有一個迦南的婦人從那地區出來,喊著說:“主啊,大衛的子孫,可憐我吧!我的女兒被鬼附得很苦。”
23እርሱ ግን አንዳች አልመለሰላትም። ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው። በኋላችን ትጮኻለችና አሰናብታት እያሉ ለመኑት።
23耶穌一句話也不回答她。門徒上前求他說:“請叫她走吧,她一直跟在我們後面喊叫。”
24እርሱም መልሶ። ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ።
24耶穌回答:“我被差遣,只是到以色列家的迷羊那裡去。”
25እርስዋ ግን መጥታ። ጌታ ሆይ፥ እርዳኝ እያለች ሰገደችለት።
25她來跪在耶穌面前說:“主啊,求你幫助我!”
26እርሱ ግን መልሶ። የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም አለ።
26耶穌回答:“拿兒女的餅丟給小狗吃是不好的。”
27እርስዋም። አዎን ጌታ ሆይ፤ ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ አለች።
27她說:“主啊,是的,不過小狗也吃主人桌子上掉下來的碎渣。”
28በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ። አንቺ ሴት፥ እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች።
28於是耶穌對她說:“婦人,你的信心真大,照你所想的給你成就吧!”從那時起,她的女兒就好了。
29ኢየሱስም ከዚያ አልፎ ወደ ገሊላ ባሕር አጠገብ መጣ፥ ወደ ተራራም ወጥቶ በዚያ ተቀመጠ።
29治好許多病人(可7:31~37)耶穌離開那裡,來到加利利海邊,就上山坐下。
30ብዙ ሕዝብም አንካሶችን፥ ዕውሮችንም፥ ዲዳዎችንም፥ ጉንድሾችንም፥ ሌሎችንም ብዙ ይዘው ወደ እርሱ ቀረቡ፥ በኢየሱስም እግር አጠገብ ጣሉአቸው፤ ፈወሳቸውም፤
30有許多人來到他那裡,把瘸腿的、瞎眼的、殘廢的、啞的和許多別的病人,都帶到耶穌跟前,他就醫好他們。
31ስለዚህም ሕዝቡ ዲዳዎች ሲናገሩ፥ ጉንድሾችም ሲድኑ፥ አንካሶችም ሲሄዱ፥ ዕውሮችም ሲያዩ አይተው ተደነቁ፤ የእስራኤልንም አምላክ አከበሩ።
31群眾看見啞巴說話,殘廢的復原,瘸腿的行走,瞎眼的看見,就十分驚奇,於是頌讚以色列的 神。
32ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ጠርቶ። ሕዝቡ ከእኔ ጋር እስካሁን ሦስት ቀን ውለዋልና የሚበሉት ስለ ሌላቸው አዝንላቸዋለሁ፤ በመንገድም እንዳይዝሉ ጦማቸውን ላሰናብታቸው አልወድም አላቸው።
32給四千人吃飽的神蹟(可8:1~10。參太14:13~21)耶穌叫門徒前來,說:“我憐憫這一群人,因為他們跟我在一起已經有三天,也沒有甚麼吃的;我不想叫他們餓著肚子回去,恐怕他們在路上暈倒。”
33ደቀ መዛሙርቱም። ይህን ያህል ሕዝብ የሚያጠግብ ይህን ያህል እንጀራ በምድረ በዳ ከወዴት እናገኛለን? አሉት።
33門徒對他說:“我們在這曠野地方,哪裡有足夠的食物給這許多的人吃飽呢?”
34ኢየሱስም። ስንት እንጀራ አላችሁ? አላቸው። እነርሱም። ሰባት፥ ጥቂትም ትንሽ ዓሣ አሉት።
34耶穌問他們:“你們有多少餅?”他們說:“七個餅和幾條小魚。”
35ሕዝቡም በምድር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፤
35他就吩咐群眾坐在地上,
36ሰባቱንም እንጀራ ዓሣውንም ይዞ አመሰገነ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ።
36拿起那七個餅和那些魚,祝謝了,擘開遞給門徒,門徒又分給眾人。
37ሁሉም በሉና ጠገቡ፥ የተረፈውንም ቁርስራሽ ሰባት ቅርጫት ሙሉ አነሡ።
37大家都吃了,並且吃飽了。他們把剩下的零碎拾起來,裝滿了七個大籃子。
38የበሉትም ከሴቶችና ከልጆች በቀር አራት ሺህ ወንዶች ነበሩ።
38吃的人,除了婦女和孩子,共有四千。
39ሕዝቡንም ካሰናበተ በኋላ ወደ ታንኳይቱ ገብቶ ወደ መጌዶል አገር መጣ።
39耶穌解散了群眾,就上了船,來到馬加丹地區。