Amharic: New Testament

聖經新譯本

Revelation

14

1አየሁም፥ እነሆም፥ በጉ በጽዮን ተራራ ቆሞ ነበር፥ ከእርሱም ጋር ስሙና የአባቱ ስም በግምባራቸው የተጻፈላቸው መቶ አርባ አራት ሺህ ነበሩ።
1救贖的新歌我又觀看,見羊羔站在錫安山上,跟他在一起的還有十四萬四千人。他們的額上都寫著他的名和他父的名。
2እንደ ብዙ ውኃም ድምፅና እንደ ታላቅ ነጐድጓድ ድምፅ ያለ ከሰማይ ድምፅን ሰማሁ፥ ደርዳሪዎችም በገና እንደሚደረድሩ ያለ ድምፅ ሰማሁ።
2我聽見有聲音從天上來,好像眾水的聲音,好像大雷的聲音;我所聽見的聲音,又像琴師彈奏的琴聲。
3በዙፋኑም ፊት በአራቱም እንስሶችና በሽማግሌዎቹ ፊት አዲስ ቅኔ ዘመሩ፤ ከምድርም ከተዋጁት ከመቶ አርባ አራት ሺህ በቀር ያን ቅኔ ሊማር ለማንም አልተቻለውም።
3他們在寶座前,在四個活物和眾長老面前唱新歌;除了從地上買來的那十四萬四千人以外,沒有人能學這歌。
4ከሴቶች ጋር ያልረከሱ እነዚህ ናቸው፥ ድንግሎች ናቸውና። በጉ ወደሚሄድበት የሚከተሉት እነዚህ ናቸው። ለእግዚአብሔርና ለበጉ በኵራት እንዲሆኑ ከሰዎች የተዋጁ እነዚህ ናቸው።
4這些人沒有跟婦女在一起而使自己玷污,他們原是童身的。羊羔無論到哪裡去,他們都跟隨他。這些人是從世人中買來的,作初熟的果子歸給 神和羊羔。
5በአፋቸውም ውሸት አልተገኘም፤ ነውር የለባቸውም።
5在他們口中找不著謊言;他們是沒有瑕疵的。
6በምድርም ለሚኖሩ ለሕዝብም ለነገድም ለቋንቋም ለወገንም ሁሉ ይሰብክ ዘንድ የዘላለም ወንጌል ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ መካከል ሲበር አየሁ፤
6三個天使的信息我又看見另一位天使在高空飛翔,有永遠的福音要傳給住在地上的人,就是各邦國、各支派、各方言、各民族的人。
7በታላቅ ድምፅም። የፍርዱ ሰዓት ደርሶአልና እግዚአብሔርን ፍሩ ክብርንም ስጡት፤ ሰማይንና ምድርንም ባሕርንም የውኃንም ምንጮች ለሠራው ስገዱለት አለ።
7他大聲說:“應當敬畏 神,把榮耀歸給他!因為他審判的時候到了,應當敬拜創造天、地、海和眾水泉源的那一位!”
8ሌላም ሁለተኛ መልአክ። አሕዛብን ሁሉ የዝሙትዋን ቍጣ ወይን ጠጅ ያጠጣች ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች እያለ ተከተለው።
8又有第二位天使接著說:“傾倒了!大巴比倫傾倒了!它曾經叫列國喝它淫亂烈怒的酒。”
9ሦስተኛም መልአክ ተከተላቸው፥ በታላቅ ድምፅ እንዲህ እያለ። ለአውሬውና ለምስሉ የሚሰግድ በግምባሩም ወይም በእጁ ምልክቱን የሚቀበል ማንም ቢኖር፥
9又有第三位天使接著他們大聲說:“如果有人拜獸和獸像,又在自己的額上或手上受了記號,
10እርሱ ደግሞ በቍጣው ጽዋ ሳይቀላቅል ከተዘጋጀው ከእግዚአብሔር ቍጣ ወይን ጠጅ ይጠጣል፥ በቅዱሳንም መላእክትና በበጉ ፊት በእሳትና በዲን ይሳቀያል።
10他就必定喝 神烈怒的酒:這酒是斟在 神震怒的杯中,純一不雜的。他必定在眾天使和羊羔面前,在火與硫磺之中受痛苦。
11የሥቃያቸውም ጢስ ለዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ይወጣል፥ ለአውሬውና ለምስሉም የሚሰግዱ የስሙንም ምልክት የሚቀበል ሁሉ ቀንና ሌሊት ዕረፍት የላቸውም።
11他們受痛苦的煙往上冒,直到永永遠遠。那些拜獸和獸像的,以及接受牠名字的記號的人,日夜得不到安息。”
12የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁት ኢየሱስንም በማመን የሚጸኑት ቅዱሳን ትዕግሥታቸው በዚህ ነው።
12在這裡,那些遵守 神的命令和耶穌的信仰的聖徒,要有忍耐。
13ከሰማይም። ከእንግዲህ ወዲህ በጌታ የሚሞቱ ሙታን ብፁዓን ናቸው። መንፈስ። አዎን፥ ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ፥ ሥራቸውም ይከተላቸዋል ይላል ብለህ ጻፍ የሚል ድምፅ ሰማሁ።
13我聽見從天上有聲音說:“你要寫下來!從今以後,那在主裡死去的人有福了!”聖靈說:“是的,他們脫離自己的勞苦,得享安息了,他們的作為也隨著他們。”
14አየሁም፥ እነሆም ነጭ ደመና፥ በደመናውም ላይ የሰውን ልጅ የሚመስል ተቀምጦአል፥ በራሱም ላይ የወርቅ አክሊል በእጁም ስለታም ማጭድ ነበረው።
14收割地上的莊稼我又觀看,見有一片白雲,雲上坐著一位好像人子的,頭上戴著金冠,手裡拿著鋒利的鐮刀。
15ሌላ መልአክም ከመቅደሱ ወጥቶ በደመናው ላይ ለተቀመጠው። የማጨድ ሰዓት ስለ ደረሰ ማጭድህን ስደድና እጨድ፥ የምድሪቱ መከር ጠውልጓልና ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ።
15有另一位天使從聖所出來,對那坐在雲上的大聲呼喊:“伸出你的鐮刀來收割吧!因為收割的時候已經到了,地上的莊稼已經熟透了。”
16በደመናውም ላይ የተቀመጠው ማጭዱን ወደ ምድር ጣለው ምድርም ታጨደች።
16於是那坐在雲上的向地上揮動鐮刀,地上的莊稼就被收割了。
17ሌላ መልአክም በሰማይ ካለው መቅደስ ወጣ፥ እርሱም ደግሞ ስለታም ማጭድ ነበረው።
17又有另一位天使從天上的聖所出來,他也拿著一把鋒利的鐮刀。
18በእሳትም ላይ ሥልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከመሠዊያው ወጥቶ ስለታም ማጭድ ያለውን። ዘለላዎቹ ፈጽመው በስለዋልና ስለታሙን ማጭድህን ስደድና በምድር ያለውን የወይን ዛፍ ዘለላዎች ቍረጥ ብሎ በታላቅ ድምፅ ጠራ።
18接著,又有一位天使從祭壇那裡出來,是有權柄掌管火的;他向那拿著鋒利鐮刀的天使大聲說:“伸出你鋒利的鐮刀來,收取地上葡萄樹纍纍的果子吧!因為葡萄已經熟透了。”
19መልአኩም ማጭዱን ወደ ምድር ጣለው፥ በምድርም ካለው ከወይን ዛፍ ቈርጦ ወደ ታላቁ ወደ እግዚአብሔር ቍጣ መጥመቂያ ጣለ።
19於是,那天使向地上揮動鐮刀,收取了地上的葡萄,把葡萄扔在 神烈怒的大壓酒池裡。
20የወይኑም መጥመቂያ ከከተማ ውጭ ተረገጠ፥ እስከ ፈረሶች ልጓምም የሚደርስ ደም ርቀቱ ሺህ ስድስት መቶ ምዕራፍ ሆኖ ከመጥመቂያው ወጣ።
20那壓酒池在城外被踹踏,就有血從壓酒池流出來,漲到馬的嚼環那麼高,流到三百公里(“三百公里”原文作“一千六百司他町”)那麼遠。