Amharic: New Testament

聖經新譯本

Revelation

17

1ሰባቱንም ጽዋዎች ከያዙ ከሰባቱ መላእክት አንዱ መጥቶ። ና በብዙም ውኃዎች ላይ የተቀመጠችውን የታላቂቱን ጋለሞታ ፍርድ አሳይሃለሁ፤
1騎著獸的大淫婦拿著七碗的七位天使中,有一位來跟我講話,說:“你來,我要把那坐在眾水之上的大淫婦所要受的審判指示你。
2የምድርም ነገሥታት ከእርስዋ ጋር ሴሰኑ በምድርም የሚኖሩ ከዝሙትዋ ወይን ጠጅ ሰከሩ ብሎ ተናገረኝ።
2地上的眾王都跟她行過淫,住在地上的人也都喝她淫亂的酒醉了。”
3በመንፈስም ወደ በረሀ ወሰደኝ፤ የስድብም ስሞች በሞሉበት፥ ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶችም ባሉበት በቀይ አውሬ ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣ አየሁ።
3我在靈裡被天使帶到曠野去,看見一個婦人,騎著朱紅色的獸,這獸布滿了褻瀆的名號,有七頭十角。
4ሴቲቱም በቀይና በሐምራዊ ልብስ ተጐናጽፋ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች በዕንቈችም ተሸልማ ነበር፥ በእጅዋም የሚያስጸይፍ ነገር የዝሙትዋም ርኵሰት የሞላባትን የወርቅ ጽዋ ያዘች፤
4那婦人穿著紫色和朱紅色的衣服,佩戴著金子、寶石和珍珠的裝飾,手裡拿著金杯,盛滿了可憎的物,和她淫亂的污穢。
5በግምባርዋም ምስጢር የሆነ ስም። ታላቂቱ ባቢሎን፥ የጋለሞታዎችና የምድር ርኵሰት እናት ተብሎ ተጻፈ።
5她額上寫著一個名號:“奧祕,大巴比倫,地上的淫婦和可憎的物之母。”
6ሴቲቱም በቅዱሳን ደምና በኢየሱስ ምስክሮች ደም ሰክራ አየኋት። ባየኋትም ጊዜ እጅግ ታላቅ ድንቅ አደነቅሁ።
6我又看見那婦人喝聖徒的血,和那為耶穌作見證的人的血,喝醉了。我看見了她,就大大驚奇。
7መልአኩም አለኝ። የምትደነቅ ስለ ምንድር ነው? የሴቲቱን ምስጢርና የሚሸከማትን፥ ሰባት ራሶችና አስር ቀንዶች ያሉትን የአውሬውን ምስጢር እኔ እነግርሃለሁ።
7天使對我說:“你為甚麼驚奇呢?我要把這婦人的奧祕,和馱著她的那七頭十角的獸的奧祕告訴你。
8ያየኸው አውሬ አስቀድሞ ነበረ፥ አሁንም የለም፥ ከጥልቁም ይወጣ ዘንድ አለው፥ ወደ ጥፋትም ይሄዳል፤ ስሞቻቸውም ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ በሕይወት መጽሐፍ ያልተጻፉ በምድር የሚኖሩ አውሬው አስቀድሞ እንደነበረ አሁንም እንደሌለ፥ ነገር ግን እንዳለ ሲያዩ ያደንቃሉ።
8你看見的那獸,先前在、現今不在、將來要從無底坑上來,然後走向滅亡。住在世上的人,凡是名字在創世以來沒有記在生命冊上的,看見了那先前在、現今不在、將來還要出現的獸,就都要驚奇。
9ጥበብ ያለው አእምሮ በዚህ ነው። ሰባቱ ራሶች ሴቲቱ የተቀመጠችባቸው ሰባት ተራራዎች ናቸው፥
9在這裡需要有智慧的心。七頭就是那婦人所坐的七座山,
10ሰባት ነገሥታት ደግሞ ናቸው፤ አምስቱ ወድቀዋል አንዱም አለ፥ የቀረውም ገና አልመጣም፤ ሲመጣም፥ ጥቂት ጊዜ ሊቆይ ይገባዋል።
10也就是七位王:五位已經倒了,一位還在,另一位還沒有來到;他來的時候,必須存留一會兒。
11የነበረውና የሌለውም አውሬ ራሱ ደግሞ ስምንተኛው ነው ከሰባቱም አንዱ ነው፥ ወደ ጥፋትም ይሄዳል።
11那先前在、現今不在的獸,就是第八位。他也是出於那七位中的一位的,並且正在走向滅亡。
12ያየሃቸውም አስሩ ቀንዶች ገና መንግሥትን ያልተቀበሉ አስር ነገሥታት ናቸው፥ ዳሩ ግን ከአውሬው ጋር ለአንድ ሰዓት እንደ ነገሥታት ሥልጣንን ይቀበላሉ።
12你看見的那十角,就是十王,他們還沒有取得王權;但要跟獸一同得著權柄,作王一個時期。
13እነዚህ አንድ አሳብ አላቸው፥ ኃይላቸውንና ሥልጣናቸውንም ለአውሬው ይሰጣሉ።
13他們同心合意,把自己的權力權柄交給那獸。
14እነዚህ በጉን ይወጋሉ፤ በጉም የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉሥ ስለ ሆነ እነርሱን ድል ይነሣል፥ ከእርሱም ጋር ያሉ የተጠሩና የተመረጡ የታመኑም ደግሞ ድል ይነሣሉ።
14他們要跟羊羔作戰,羊羔必勝過他們,因為他是萬主之主,萬王之王。那些與羊羔同在、蒙召、被選、有忠心的,也必勝過他們。”
15አለኝም። ጋለሞታይቱ የተቀመጠችባቸው ያየሃቸው ውኃዎች፥ ወገኖችና ብዙ ሰዎች አሕዛብም ቋንቋዎችም ናቸው።
15天使又對我說:“你所看見那淫婦坐著的眾水,就是多種民族、群眾、邦國,方言的人。
16ያየኃቸውም አስር ቀንዶችና አውሬው ጋለሞታይቱን ይጣላሉ፤ ባዶዋንና ራቁትዋንም ያደርጓታል፥ ሥጋዋንም ይበላሉ፥ በእሳትም ያቃጥሉአታል።
16你看見的十角和那獸,都要恨那淫婦,使她荒涼赤身,又要吃她的肉,用火把她燒掉。
17እግዚአብሔር አሳቡን እንዲያደርጉ አንድንም አሳብ እንዲያደርጉ የእግዚአብሔርም ቃል እስኪፈጸም ድረስ መንግሥታቸውን ለአውሬው እንዲሰጡ በልባቸው አግብቶአልና።
17 神要眾王行他的旨意,就把意念放在他們心中,叫他們同心把自己的國獻給那獸,直到 神的話都實現為止。
18ያየሃትም ሴት በምድር ነገሥታት ላይ የምትነግሥ ታላቂቱ ከተማ ናት።
18你看見的那婦人,就是有權統治地上的眾王的那座大城。”