Amharic: New Testament

Darby's Translation

2 Corinthians

10

1እኔም ራሴ ጳውሎስ፥ በእናንተ ዘንድ ፊት ለፊት ሳለሁ ትሑት የሆንሁ፥ ከእናንተ ግን ብርቅ የምደፍራችሁ፥ በክርስቶስ የዋህነትና ገርነት እመክራችኋለሁ፤
1But I myself, Paul, entreat you by the meekness and gentleness of the Christ, who, as to appearance, [when present] [am] mean among you, but absent am bold towards you;
2በዓለማዊ ልማድ እንደምንመላለስ በሚቆጥሩን በአንዳንዶች ላይ አምኜ ልደፍር አስባለሁ፥ በዚያ እምነት ግን ከእናንተ ጋር ሆኜ እንዳልደፍር እለምንችኋለሁ።
2but I beseech that present I may not be bold with the confidence with which I think to be daring towards some who think of us as walking according to flesh.
3በሰው ልማድ ምንም እንኳ የምንመላለስ ብንሆን፥ እንደ ሰው ልማድ አንዋጋም፤
3For walking in flesh, we do not war according to flesh.
4የጦር ዕቃችን ሥጋዊ አይደለምና፥ ምሽግን ለመስበር ግን በእግዚአብሔር ፊት ብርቱ ነው፤
4For the arms of our warfare [are] not fleshly, but powerful according to God to [the] overthrow of strongholds;
5የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፥
5overthrowing reasonings and every high thing that lifts itself up against the knowledge of God, and leading captive every thought into the obedience of the Christ;
6መታዘዛችሁም በተፈጸመች ጊዜ አለመታዘዝን ሁሉ ልንበቀል ተዘጋጅተናል።
6and having in readiness to avenge all disobedience when your obedience shall have been fulfilled.
7በፊታችሁ ያለውን ተመልከቱ። ማንም የክርስቶስ መሆኑን ተረድቶ ቢሆን፥ ይህን እንደ ገና በራሱ ይቁጠረው፤ እርሱ የክርስቶስ እንደ ሆነ እኛ ደግሞ እንዲሁ ነን።
7Do ye look at what concerns appearance? If any one has confidence in himself that he is of Christ, let him think this again in himself, that even as he [is] of Christ, so also [are] we.
8ጌታ እናንተን ለማነጽ እንጂ እናንተን ለማፍረስ ያይደለ በሰጠው በሥልጣናችን ከፊት ይልቅ ብመካ እንኳ አላፍርም።
8For and if I should boast even somewhat more abundantly of our authority, which the Lord has given [to us] for building up and not for your overthrowing, I shall not be put to shame;
9በመልእክቶቼ የማስደነግጣችሁ አይምሰላችሁ።
9that I may not seem as if I was frightening you by letters:
10መልእክቶቹስ ከባድና ኃይለኛ ናቸው፥ ሰውነቱ ግን ሲታይ ደካማ ነው፥ ንግግሩም የተናቀ ነው ይላሉና።
10because his letters, he says, [are] weighty and strong, but his presence in the body weak, and his speech naught.
11እንዲሁ የሚል ይህን ይቁጠረው፤ በሩቅ ሳለን በመልእክታችን በኩል በቃል እንዳለን፥ በፊቱ ደግሞ ሳለን በሥራ እንዲሁ ነን።
11Let such a one think this, that such as we are in word by letters [when] absent, such also present in deed.
12ራሳቸውን ከሚያመሰግኑ ከአንዳንዶች ጋር ራሳችንን ልንቆጥር ወይም ራሳችንን ልናስተያይ አንደፍርምና፤ ነገር ግን እነርሱ ራሳቸውን ከራሳቸው ጋር ሲያመዛዝኑ፥ ራሳቸውንም ከራሳቸው ጋር ሲያስተያዩ፥ አያስተውሉም።
12For we dare not class ourselves or compare ourselves with some who commend themselves; but these, measuring themselves by themselves, and comparing themselves with themselves, are not intelligent.
13እኛ ግን እግዚአብሔር እንደ ወሰነልን እስከ እናንተ እንኳ እንደሚደርስ እንደ ክፍላችን ልክ እንጂ ያለ ልክ አንመካም።
13Now *we* will not boast out of measure, but according to the measure of the rule which the God of measure has apportioned to us, to reach to you also.
14ወደ እናንተ እንደማንደርስ አድርገን ከመጠን አናልፍምና፥ የክርስቶስን ወንጌል በመስበክ እስከ እናንተ እንኳ ደርሰናልና፤
14For we do not, as not reaching to you, overstretch ourselves, (for we have come to you also in the glad tidings of the Christ;)
15በሌሎች ድካም ያለ ልክ አንመካም፥ ነገር ግን እምነታችሁ ሲያድግ ከእናንተ ወዲያ ባለው አገር እስክንሰብክ ሥራችንን እየጨመርን፥ በክፍላችን በእናንተ ዘንድ እንድንከብር ተስፋ እናደርጋለን፤ በሌላው ክፍል ስለ ተዘጋጀው ነገር አንመካም።
15not boasting out of measure in other people's labours, but having hope, your faith increasing, to be enlarged amongst you, according to our rule, yet more abundantly
17የሚመካ ግን በጌታ ይመካ፤ እግዚአብሔር የሚያመሰግነው እንጂ ራሱን የሚያመሰግን እርሱ ተፈትኖ የሚወጣ አይደለምና።
16to announce the glad tidings to that [which is] beyond you, not to be boasting in another's rule of things made ready to hand.
17But he that boasts, let him boast in the Lord.
18For not *he* that commends himself is approved, but whom the Lord commends.