1ለቅዱሳን ስለሚሆነው አገልግሎት ልጽፍላችሁ አያስፈልግምና፤
1For concerning the ministration which [is] for the saints, it is superfluous my writing to you.
2በጎ ፈቃዳችሁን አውቄአለሁና፤ ስለዚህም። አካይያ ከአምና ጀምሮ ተዘጋጅቶአል ብዬ ለመቄዶንያ ሰዎች በእናንተ እመካለሁ፥ ቅንዓታችሁም የሚበዙቱን አነሣሥቶአል።
2For I know your readiness, which I boast of as respects you to Macedonians, that Achaia is prepared since a year ago, and the zeal [reported] of you has stimulated the mass [of the brethren].
3ነገር ግን ለእነርሱ እንዳልሁ፥ የተዘጋጃችሁ ትሆኑ ዘንድ በዚህም ነገር ስለ እናንተ ያለው ትምክህታችን ከንቱ እንዳይሆን ወንድሞችን እልካለሁ፤
3But I have sent the brethren, in order that our boasting about you may not be made void in this respect, in order that, as I have said, ye may be prepared;
4ምናልባት የመቄዶንያ ሰዎች ከእኔ ጋር ቢመጡ፥ ያልተዘጋጃችሁም ሆናችሁ ቢያገኙአችሁ፥ እናንተ እንድታፍሩ አላልንም እኛ ግን በዚህ እምነታችን እንድናፍር አይሁን።
4lest haply, if Macedonians come with me and find you unprepared, *we*, that we say not *ye*, may be put to shame in this confidence.
5እንግዲህ እንደ በረከት ሆኖ ከስስት የማይሆን ይህ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ አስቀድመው ወደ እናንተ መጥተው፥ አስቀድማችሁ ተስፋ የሰጣችሁትን በረከት አስቀድመው እንዲፈጽሙ ወንድሞችን እለምን ዘንድ እንዲያስፈልገኝ አሰብሁ።
5I thought it necessary therefore to beg the brethren that they would come to you, and complete beforehand your fore-announced blessing, that this may be ready thus as blessing, and not as got out of you.
6ይህንም እላለሁ። በጥቂት የሚዘራ በጥቂት ደግሞ ያጭዳል፥ በበረከትም የሚዘራ በበረከት ደግሞ ያጭዳል።
6But this [is true], he that sows sparingly shall reap also sparingly; and he that sows in [the spirit of] blessing shall reap also in blessing:
7እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም።
7each according as he is purposed in his heart; not grievingly, or of necessity; for God loves a cheerful giver.
8በተነ፥ ለምስኪኖች ሰጠ፥ ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ እግዚአብሔር፥ ሁልጊዜ በነገር ሁሉ ብቃትን ሁሉ አግኝታችሁ ለበጎ ሥራ ሁሉ ትበዙ ዘንድ፥ ጸጋን ሁሉ ሊያበዛላችሁ ይችላል።
8But God is able to make every gracious gift abound towards you, that, having in every way always all-sufficiency, ye may abound to every good work:
10ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱም የምትዘሩትን ዘር ይሰጣችኋል ያበረክትላችሁማል፥ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያሳድጋል፤
9according as it is written, He has scattered abroad, he has given to the poor, his righteousness remains for ever.
11በእኛ በኩል ለእግዚአብሔር የምስጋና ምክንያት የሚሆነውን ልግስና ሁሉ እንድታሳዩ በሁሉ ነገር ባለ ጠጎች ትሆናላችሁ።
10Now he that supplies seed to the sower and bread for eating shall supply and make abundant your sowing, and increase the fruits of your righteousness:
12የዚህ ረድኤት አገልግሎት ለቅዱሳን የሚጎድላቸውን በሙሉ የሚሰጥ ብቻ አይደለምና፥ ነገር ግን ደግሞ በብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር ይበዛል፤
11enriched in every way unto all free-hearted liberality, which works through us thanksgiving to God.
13በዚህ አገልግሎት ስለ ተፈተናችሁ፥ በክርስቶስ ወንጌል በማመናችሁ ስለሚሆን መታዘዝ እነርሱንና ሁሉንም ስለምትረዱበት ልግስና እግዚአብሔርን ያከብራሉ፥
12Because the ministration of this service is not only filling up the measure of what is lacking to the saints, but also abounding by many thanksgivings to God;
14ራሳቸውም ስለ እናንተ ሲያማልዱ፥ በእናንተ ላይ ከሚሆነው ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሣ ይናፍቁአችኋል።
13they glorifying God through the proof of this ministration, by reason of your subjection, by profession, to the glad tidings of the Christ, and your free-hearted liberality in communicating towards them and towards all;
15ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን።
14and in their supplication for you, full of ardent desire for you, on account of the exceeding grace of God [which is] upon you.
15Thanks [be] to God for his unspeakable free gift.