Amharic: New Testament

Darby's Translation

3 John

1

1ሽማግሌው በእውነት እኔ ለምወደው ለተወደደው ለጋይዮስ።
1The elder to the beloved Gaius, whom I love in truth.
2ወዳጅ ሆይ፥ ነፍስህ እንደሚከናወን፥ በነገር ሁሉ እንዲከናወንልህና ጤና እንዲኖርህ እጸልያለሁ።
2Beloved, I desire that in all things thou shouldest prosper and be in health, even as thy soul prospers.
3ወንድሞች መጥተው አንተ በእውነት እንደምትሄድ ስለ እውነትህ ሲመሰክሩ እጅግ ደስ ብሎኛልና።
3For I rejoiced exceedingly when [the] brethren came and bore testimony to thy [holding fast the] truth, even as *thou* walkest in truth.
4ልጆቼ በእውነት እንዲሄዱ ከመስማት ይልቅ የሚበልጥ ደስታ የለኝም።
4I have no greater joy than these things that I hear of my children walking in the truth.
5ወዳጅ ሆይ፥ ምንም እንግዶች ቢሆኑ፥ ለወንድሞች በምታደርገው ሁሉ የታመነ ሥራ ትሠራለህ፥ እነርሱም በማኅበር ፊት ስለ ፍቅርህ መስክረዋል፤
5Beloved, thou doest faithfully [in] whatever thou mayest have wrought towards the brethren and that strangers,
6ለእግዚአብሔር እንደሚገባ አድርገህ በጉዞአቸው ብትረዳ መልካም ታደርጋለህ፤
6(who have witnessed of thy love before [the] assembly,) in setting forward whom on their journey worthily of God, thou wilt do well;
7ከአሕዛብ አንዳች ሳይቀበሉ ስለ ስሙ ወጥተዋልና።
7for for the name have they gone forth, taking nothing of those of the nations.
8እንግዲህ ከእውነት ጋር አብረን እንድንሠራ እኛ እንዲህ ያሉትን በእንግድነት ልንቀበል ይገባናል።
8*We* therefore ought to receive such, that we may be fellow-workers with the truth.
9ወደ ቤተ ክርስቲያን ጻፍሁ፤ ዳሩ ግን ዋናቸው ሊሆን የሚወድ ዲዮጥራጢስ አይቀበለንም።
9I wrote something to the assembly; but Diotrephes, who loves to have the first place among them, receives us not.
10ስለዚህ፥ እኔ ብመጣ፥ በእኛ ላይ በክፉ ቃል እየለፈለፈ የሚያደርገውን ሥራውን አሳስባለሁ፤ ይህም ሳይበቃው እርሱ ራሱ ወንድሞችን አይቀበልም፥ ሊቀበሉአቸውም የሚወዱትን ከልክሎ ከቤተ ክርስቲያን ያወጣቸዋል።
10For this reason, if I come, I will bring to remembrance his works which he does, babbling against us with wicked words; and not content with these, neither does he himself receive the brethren; and those who would he prevents, and casts [them] out of the assembly.
11ወዳጅ ሆይ፥ በጎ የሆነውን እንጂ ክፉን አትምሰል። በጎ የሚያደርግ ከእግዚአብሔር ነው፤ ክፉን የሚያደርግ ግን እግዚአብሔርን አላየውም።
11Beloved, do not imitate what is evil, but what is good. He that does good is of God. He that does evil has not seen God.
12ለድሜጥሮስ ሁሉ ይመሰክሩለታል፥ እውነት ራስዋም ትመሰክርለታለች፤ እኛም ደግሞ እንመሰክርለታለን፥ ምስክርነታችንም እውነት እንደ ሆነ ታውቃላችሁ።
12Demetrius has witness borne to him by all, and by the truth itself; and *we* also bear witness, and thou knowest that our witness is true.
13ልጽፍልህ የምፈልገው ብዙ ነገር ነበረኝ፥ ዳሩ ግን በቀለምና በብርዕ ልጽፍልህ አልወድም፤
13I had many things to write to thee, but I will not with ink and pen write to thee;
14ነገር ግን ወዲያው ላይህ ተስፋ አደርጋለሁ፥ አፍ ለአፍም እንነጋገራለን። ሰላም ለአንተ ይሁን። ወዳጆች ሰላምታ ያቀርቡልሃል። ወዳጆችን በየስማቸው እየጠራህ ሰላምታ አቅርብልኝ።
14but I hope soon to see thee, and we will speak mouth to mouth.
15Peace [be] to thee. The friends greet thee. Greet the friends by name.