Amharic: New Testament

Darby's Translation

John

10

1እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤
1Verily, verily, I say to you, He that enters not in by the door to the fold of the sheep, but mounts up elsewhere, *he* is a thief and a robber;
2በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው።
2but he that enters in by the door is [the] shepherd of the sheep.
3ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል።
3To him the porter opens; and the sheep hear his voice; and he calls his own sheep by name, and leads them out.
4የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤
4When he has put forth all his own, he goes before them, and the sheep follow him, because they know his voice.
5ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና።
5But they will not follow a stranger, but will flee from him, because they know not the voice of strangers.
6ኢየሱስ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ እነርሱ ግን የነገራቸው ምን እንደ ሆነ አላስተዋሉም።
6This allegory spoke Jesus to them, but they did not know what it was [of] which he spoke to them.
7ኢየሱስም ደግሞ አላቸው። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እኔ የበጎች በር ነኝ።
7Jesus therefore said again to them, Verily, verily, I say to you, I am the door of the sheep.
8ከእኔ በፊት የመጡ ሁሉ ሌቦችና ወንበዴዎች ናቸው፤ ዳሩ ግን በጎቹ አልሰሙአቸውም።
8All whoever came before me are thieves and robbers; but the sheep did not hear them.
9በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማሪያም ያገኛል።
9I am the door: if any one enter in by me, he shall be saved, and shall go in and shall go out and shall find pasture.
10ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።
10The thief comes not but that he may steal, and kill, and destroy: I am come that they might have life, and might have [it] abundantly.
11መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።
11I am the good shepherd. The good shepherd lays down his life for the sheep:
12እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል በጎቹንም ይበትናቸዋል።
12but he who serves for wages, and who is not the shepherd, whose own the sheep are not, sees the wolf coming, and leaves the sheep and flees; and the wolf seizes them and scatters the sheep.
13ሞያተኛ ስለ ሆነ ለበጎቹም ስለማይገደው ሞያተኛው ይሸሻል።
13Now he who serves for wages flees because he serves for wages, and is not himself concerned about the sheep.
14መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች ያውቁኛል፤ ነፍሴንም ስለ በጎች አኖራለሁ።
14I am the good shepherd; and I know those that are mine, and am known of those that are mine,
16ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።
15as the Father knows me and I know the Father; and I lay down my life for the sheep.
17ነፍሴን ደግሞ አነሣት ዘንድ አኖራለሁና ስለዚህ አብ ይወደኛል።
16And I have other sheep which are not of this fold: those also I must bring, and they shall hear my voice; and there shall be one flock, one shepherd.
18እኔ በፈቃዴ አኖራታለሁ እንጂ ከእኔ ማንም አይወስዳትም። ላኖራት ሥልጣን አለኝ ደግሞም ላነሣት ሥልጣን አለኝ ይህችን ትእዛዝ ከአባቴ ተቀበልሁ።
17On this account the Father loves me, because I lay down my life that I may take it again.
19እንግዲህ ከዚህ ቃል የተነሣ በአይሁድ መካከል እንደ ገና መለያየት ሆነ።
18No one takes it from me, but I lay it down of myself. I have authority to lay it down and I have authority to take it again. I have received this commandment of my Father.
20ከእነርሱም ብዙዎች። ጋኔን አለበት አብዶአልም፤ ስለ ምንስ ትሰሙታላችሁ? አሉ።
19There was a division again among the Jews on account of these words;
21ሌሎችም። ይህ ጋኔን ያለበት ሰው ቃል አይደለም፤ ጋኔን የዕውሮችን ዓይኖች ሊከፍት ይችላልን? አሉ።
20but many of them said, He has a demon and raves; why do ye hear him?
22በኢየሩሳሌምም የመቅደስ መታደስ በዓል ሆነ፤
21Others said, These sayings are not [those] of one that is possessed by a demon. Can a demon open blind people's eyes?
23ክረምትም ነበረ። ኢየሱስም በመቅደስ በሰሎሞን ደጅ መመላለሻ ይመላለስ ነበር።
22Now the feast of the dedication was celebrating at Jerusalem, and it was winter.
24አይሁድም እርሱን ከበው። እስከ መቼ ድረስ በጥርጣሪ ታቆየናለህ? አንተ ክርስቶስ እንደ ሆንህ ገልጠህ ንገረን አሉት።
23And Jesus walked in the temple in the porch of Solomon.
25ኢየሱስም መለሰላቸው፥ እንዲህ ሲል። ነገርኋችሁ አታምኑምም እኔ በአባቴ ስም የማደርገው ሥራ ይህ ስለ እኔ ይመሰክራል፤
24The Jews therefore surrounded him, and said to him, Until when dost thou hold our soul in suspense? If thou art the Christ, say [so] to us openly.
26እናንተ ግን እንደ ነገርኋችሁ ከበጎቼ ስላልሆናችሁ አታምኑም።
25Jesus answered them, I told you, and ye do not believe. The works which I do in my Father's name, these bear witness concerning me:
27በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ ይከተሉኝማል፤
26but ye do not believe, for ye are not of my sheep, as I told you.
28እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።
27My sheep hear my voice, and I know them, and they follow me;
29የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ ከአባቴም እጅ ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም።
28and I give them life eternal; and they shall never perish, and no one shall seize them out of my hand.
30እኔና አብ አንድ ነን።
29My Father who has given [them] to me is greater than all, and no one can seize out of the hand of my Father.
31አይሁድ ሊወግሩት ደግመው ድንጋይ አነሡ።
30I and the Father are one.
32ኢየሱስ። ከአባቴ ብዙ መልካም ሥራ አሳየኋችሁ፤ ከእነርሱ ስለ ማናቸው ሥራ ትወግሩኛላችሁ? ብሎ መለሰላቸው።
31The Jews therefore again took stones that they might stone him.
33አይሁድም። ስለ መልካም ሥራ አንወግርህም፤ ስለ ስድብ፤ አንተም ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለ ማድረግህ ነው እንጂ ብለው መለሱለት።
32Jesus answered them, Many good works have I shewn you of my Father; for which work of them do ye stone me?
34ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው። እኔ። አማልክት ናችሁ አልሁ ተብሎ በሕጋችሁ የተጻፈ አይደለምን?
33The Jews answered him, For a good work we stone thee not, but for blasphemy, and because thou, being a man, makest thyself God.
35መጽሐፉ ሊሻር አይቻልምና እነዚያን የእግዚአብሔር ቃል የመጣላቸውን አማልክት ካላቸው፥
34Jesus answered them, Is it not written in your law, I said, Ye are gods?
36የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ስላልሁ እናንተ አብ የቀደሰውን ወደ ዓለምም የላከውን። ትሳደባለህ ትሉታላችሁን?
35If he called *them* gods to whom the word of God came (and the scripture cannot be broken),
37እኔ የአባቴን ሥራ ባላደርግ አትመኑኝ፤
36do ye say of him whom the Father has sanctified and sent into the world, Thou blasphemest, because I said, I am Son of God?
38ባደርገው ግን፥ እኔን ስንኳ ባታምኑ አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ።
37If I do not the works of my Father, believe me not;
39እንግዲህ ደግመው ሊይዙት ፈለጉ፤ ከእጃቸውም ወጣ።
38but if I do, even if ye believe not me, believe the works, that ye may know [and believe] that the Father is in me and I in him.
40ዮሐንስም በመጀመሪያ ያጠምቅበት ወደ ነበረው ስፍራ ወደ ዮርዳኖስ ማዶ እንደ ገና ሄደ በዚያም ኖረ።
39They sought therefore again to take him; and he went away from out of their hand
41ብዙ ሰዎችም ወደ እርሱ መጥተው። ዮሐንስ አንድ ምልክት ስንኳ አላደረገም፥ ነገር ግን ዮሐንስ ስለዚህ ሰው የተናገረው ሁሉ እውነት ነበረ አሉ።
40and departed again beyond the Jordan to the place where John was baptising at the first: and he abode there.
42በዚያም ብዙዎች በእርሱ አመኑ።
41And many came to him, and said, John did no sign; but all things which John said of this [man] were true.
42And many believed on him there.