1ከማርያምና ከእኅትዋ ከማርታ መንደር ከቢታንያ የሆነ አልዓዛር የሚባል አንድ ሰው ታሞ ነበር።
1Now there was a certain [man] sick, Lazarus of Bethany, of the village of Mary and Martha her sister.
2ማርያምም ጌታን ሽቱ የቀባችው እግሩንም በጠጕርዋ ያበሰችው ነበረች፤ ወንድምዋም አልዓዛር ታሞ ነበር።
2It was [the] Mary who anointed the Lord with ointment and wiped his feet with her hair, whose brother Lazarus was sick.
3ስለዚህ እኅቶቹ ጌታ ሆይ፥ እነሆ የምትወደው ታሞአል ብለው ወደ እርሱ ላኩ።
3The sisters therefore sent to him, saying, Lord, behold, he whom thou lovest is sick.
4ኢየሱስም ሰምቶ። ይህ ህመም የእግዚአብሔር ልጅ በእርሱ ይከብር ዘንድ ስለ እግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት አይደለም አለ።
4But when Jesus heard [it], he said, This sickness is not unto death, but for the glory of God, that the Son of God may be glorified by it.
5ኢየሱስም ማርታንና እኅትዋን አልዓዛርንም ይወድ ነበር።
5Now Jesus loved Martha, and her sister, and Lazarus.
6እንደ ታመመም በሰማ ጊዜ ያን ጊዜ በነበረበት ስፍራ ሁለት ቀን ዋለ፤
6When therefore he heard, He is sick, he remained two days then in the place where he was.
7ከዚህም በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ። ወደ ይሁዳ ደግሞ እንሂድ አላቸው።
7Then after this he says to his disciples, Let us go into Judaea again.
8ደቀ መዛሙርቱ። መምህር ሆይ፥ አይሁድ ከጥቂት ጊዜ በፊት ሊወግሩህ ይፈልጉ ነበር፥ ደግሞም ወደዚያ ትሄዳለህን? አሉት።
8The disciples say to him, Rabbi, [even but] now the Jews sought to stone thee, and goest thou thither again?
9ኢየሱስም መልሶ። ቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት አይደለምን? በቀን የሚመላለስ ቢኖር የዚህን ዓለም ብርሃን ያያልና አይሰናከልም፤
9Jesus answered, Are there not twelve hours in the day? If any one walk in the day, he does not stumble, because he sees the light of this world;
10በሌሊት የሚመላለስ ቢኖር ግን ብርሃን በእርሱ ስለ ሌለ ይሰናከላል አላቸው።
10but if any one walk in the night, he stumbles, because the light is not in him.
11ይህን ተናገረ፤ ከዚህም በኋላ። ወዳጃችን አልዓዛር ተኝቶአል፤ ነገር ግን ከእንቅልፉ ላስነሣው እሄዳለሁ አላቸው።
11These things said he; and after this he says to them, Lazarus, our friend, is fallen asleep, but I go that I may awake him out of sleep.
12እንግዲህ ደቀ መዛሙርቱ። ጌታ ሆይ፥ ተኝቶስ እንደ ሆነ ይድናል አሉት።
12The disciples therefore said to him, Lord, if he be fallen asleep, he will get well.
13ኢየሱስስ ስለ ሞቱ ተናግሮ ነበር፤ እነርሱ ግን ስለ እንቅልፍ መተኛት እንደ ተናገረ መሰላቸው።
13But Jesus spoke of his death, but *they* thought that he spoke of the rest of sleep.
14እንግዲህ ያን ጊዜ ኢየሱስ በግልጥ። አልዓዛር ሞተ፤
14Jesus therefore then said to them plainly, Lazarus has died.
15እንድታምኑም በዚያ ባለመኖሬ ስለ እናንተ ደስ ይለኛል፤ ነገር ግን ወደ እርሱ እንሂድ አላቸው።
15And I rejoice on your account that I was not there, in order that ye may believe. But let us go to him.
16ስለዚህ ዲዲሞስ የሚሉት ቶማስ ለባልንጀሮቹ ለደቀ መዛሙርት። ከእርሱ ጋር እንሞት ዘንድ እኛ ደግሞ እንሂድ አለ።
16Thomas therefore, called Didymus, said to his fellow disciples, Let *us* also go, that we may die with him.
17ኢየሱስም በመጣ ጊዜ በመቃብር እስከ አሁን አራት ቀን ሆኖት አገኘው።
17Jesus therefore [on] arriving found him to have been four days already in the tomb.
18ቢታንያም አሥራ አምስት ምዕራፍ ያህል ለኢየሩሳሌም ቅርብ ነበረች።
18Now Bethany was near Jerusalem, about fifteen stadia off,
19ከአይሁድም ብዙዎች ስለ ወንድማቸው ሊያጽናኑአቸው ወደ ማርታና ወደ ማርያም መጥተው ነበር።
19and many of the Jews came to Martha and Mary, that they might console them concerning their brother.
20ማርታም ኢየሱስ እንደ መጣ በሰማች ጊዜ ልትቀበለው ወጣች፤ ማርያም ግን በቤት ተቀምጣ ነበር።
20Martha then, when she heard Jesus is coming, went to meet him; but Mary sat in the house.
21ማርታም ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ወንድሜ ባልሞተም ነበር፤
21Martha therefore said to Jesus, Lord, if thou hadst been here, my brother had not died;
22አሁንም ከእግዚአብሔር የምትለምነውን ሁሉ እግዚአብሔር እንዲሰጥህ አውቃለሁ አለችው።
22but even now I know, that whatsoever thou shalt ask of God, God will give thee.
23ኢየሱስም። ወንድምሽ ይነሣል አላት።
23Jesus says to her, Thy brother shall rise again.
24ማርታም። በመጨረሻው ቀን በትንሣኤ እንዲነሣ አውቃለሁ አለችው።
24Martha says to him, I know that he will rise again in the resurrection in the last day.
25ኢየሱስም። ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤
25Jesus said to her, I am the resurrection and the life: he that believes on me, though he have died, shall live;
26ሕያው የሆነም የሚያምንብኝም ሁሉ ለዘላለም አይሞትም፤ ይህን ታምኚያለሽን? አላት።
26and every one who lives and believes on me shall never die. Believest thou this?
27እርስዋም። አዎን ጌታ ሆይ፤ አንተ ወደ ዓለም የሚመጣው ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ እኔ አምናለሁ አለችው።
27She says to him, Yea, Lord; I believe that thou art the Christ, the Son of God, who should come into the world.
28ይህንም ብላ ሄደች እኅትዋንም ማርያምን በስውር ጠርታ። መምህሩ መጥቶአል ይጠራሽማል አለቻት።
28And having said this, she went away and called her sister Mary secretly, saying, The teacher is come and calls thee.
29እርስዋም በሰማች ጊዜ ፈጥና ተነሣች ወደ እርሱም መጣች፤
29She, when she heard [that], rises up quickly and comes to him.
30ኢየሱስም ማርታ በተቀበለችበት ስፍራ ነበረ እንጂ ገና ወደ መንደሩ አልገባም ነበር።
30Now Jesus had not yet come into the village, but was in the place where Martha came to meet him.
31ሲያጽናኑአት ከእርስዋ ጋር በቤት የነበሩ አይሁድም ማርያም ፈጥና እንደ ተነሣችና እንደ ወጣች ባዩ ጊዜ፥ ወደ መቃብር ሄዳ በዚያ ልታለቅስ መስሎአቸው ተከተሉአት።
31The Jews therefore who were with her in the house and consoling her, seeing Mary that she rose up quickly and went out, followed her, saying, She goes to the tomb, that she may weep there.
32ማርያምም ኢየሱስ ወዳለበት መጥታ ባየችው ጊዜ በእግሩ ላይ ወድቃ። ጌታ ሆይ፥ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ወንድሜ ባልሞተም ነበር አለችው።
32Mary therefore, when she came where Jesus was, seeing him, fell at his feet, saying to him, Lord, if thou hadst been here, my brother had not died.
33ኢየሱስም እርስዋ ስታለቅስ ከእርስዋም ጋር የመጡት አይሁድ ሲያለቅሱ አይቶ በመንፈሱ አዘነ በራሱም ታወከ፤
33Jesus therefore, when he saw her weeping, and the Jews who came with her weeping, was deeply moved in spirit, and was troubled,
34ወዴት አኖራችሁት? አለም። እነርሱም። ጌታ ሆይ፥ መጥተህ እይ አሉት።
34and said, Where have ye put him? They say to him, Lord, come and see.
35ኢየሱስም እንባውን አፈሰሰ።
35Jesus wept.
36ስለዚህ አይሁድ። እንዴት ይወደው እንደ ነበረ እዩ አሉ።
36The Jews therefore said, Behold how he loved him!
37ከእነርሱ ግን አንዳንዶቹ። ይህ የዕውሩን ዓይኖች የከፈተ ይህን ደግሞ እንዳይሞት ያደርግ ዘንድ ባልቻለም ነበርን? አሉ።
37And some of them said, Could not this [man], who has opened the eyes of the blind [man], have caused that this [man] also should not have died?
38ኢየሱስም በራሱ አዝኖ ወደ መቃብሩ መጣ፤ እርሱም ዋሻ ነበረ፤ ድንጋይም ተገጥሞበት ነበር።
38Jesus therefore, again deeply moved in himself, comes to the tomb. Now it was a cave, and a stone lay upon it.
39ኢየሱስ። ድንጋዩን አንሡ አለ። የሞተውም እኅት ማርታ። ጌታ ሆይ፥ ከሞተ አራት ቀን ሆኖታልና አሁን ይሸታል አለችው።
39Jesus says, Take away the stone. Martha, the sister of the dead, says to him, Lord, he stinks already, for he is four days [there].
40ኢየሱስ። ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርሁሽምን? አላት።
40Jesus says to her, Did I not say to thee, that if thou shouldest believe, thou shouldest see the glory of God?
41ድንጋዩንም አነሡት። ኢየሱስም ዓይኖቹን ወደ ላይ አንሥቶ። አባት ሆይ፥ ስለ ሰማኸኝ አመሰግንሃለሁ።
41They took therefore the stone away. And Jesus lifted up his eyes on high and said, Father, I thank thee that thou hast heard me;
42ሁልጊዜም እንድትሰማኝ አወቅሁ፤ ነገር ግን አንተ እንደ ላክኸኝ ያምኑ ዘንድ በዚህ ዙሪያ ስለ ቆሙት ሕዝብ ተናገርሁ አለ።
42but I knew that thou always hearest me; but on account of the crowd who stand around I have said [it], that they may believe that thou hast sent me.
43ይህንም ብሎ በታላቅ ድምፅ። አልዓዛር ሆይ፥ ወደ ውጭ ና ብሎ ጮኸ።
43And having said this, he cried with a loud voice, Lazarus, come forth.
44የሞተውም እጆቹና እግሮቹ በመግነዝ እንደ ተገነዙ ወጣ፤ ፈቱም በጨርቅ እንደ ተጠመጠመ ነበር። ኢየሱስም። ፍቱትና ይሂድ ተዉት አላቸው።
44And the dead came forth, bound feet and hands with graveclothes, and his face was bound round with a handkerchief. Jesus says to them, Loose him and let him go.
45ስለዚህ ወደ ማርያም ከመጡት፥ ኢየሱስም ያደረገውን ካዩት ከአይሁድ ብዙዎች በእርሱ አመኑ፤
45Many therefore of the Jews who came to Mary and saw what he had done, believed on him;
46ከእነርሱ አንዳንዶቹ ግን ወደ ፈሪሳውያን ሄደው ኢየሱስ ያደረገውን ነገሩአቸው።
46but some of them went to the Pharisees and told them what Jesus had done.
47እንግዲህ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ሸንጎ ሰብስበው። ምን እናድርግ? ይህ ሰው ብዙ ምልክቶች ያደርጋልና።
47The chief priests, therefore, and the Pharisees gathered a council, and said, What do we? for this man does many signs.
48እንዲሁ ብንተወው ሁሉ በእርሱ ያምናሉ፤ የሮሜም ሰዎች መጥተው አገራችንን ወገናችንንም ይወስዳሉ አሉ።
48If we let him thus alone, all will believe on him, and the Romans will come and take away both our place and our nation.
49በዚያችም ዓመት ሊቀ ካህናት የነበረ ቀያፋ የሚሉት ከእነርሱ አንዱ። እናንተ ምንም አታውቁም፤
49But a certain one of them, Caiaphas, being high priest that year, said to them, Ye know nothing
50ሕዝቡም ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡም አላቸው።
50nor consider that it is profitable for you that one man die for the people, and not that the whole nation perish.
51ይህንም የተናገረ ከራሱ አይደለም፥ ነገር ግን በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ነበረና ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው ትንቢት ተናገረ፤
51But this he did not say of himself; but, being high priest that year, prophesied that Jesus was going to die for the nation;
52ስለ ሕዝቡም ሁሉ አይደለም፥ ነገር ግን የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች ደግሞ በአንድነት እንዲሰበስባቸው ነው እንጂ።
52and not for the nation only, but that he should also gather together into one the children of God who were scattered abroad.
53እንግዲህ ከዚያ ቀን ጀምረው ሊገድሉት ተማከሩ።
53From that day therefore they took counsel that they might kill him.
54ከዚያ ወዲያም ኢየሱስ በአይሁድ መካከል ተገልጦ አልተመላለሰም፤ ነገር ግን ከዚያ በምድረ በዳ አጠገብ ወዳለች ምድር፥ ኤፍሬም ወደምትባል ከተማ ሄደ፤ በዚያም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጠ።
54Jesus therefore walked no longer openly among the Jews, but went away thence into the country near the desert, to a city called Ephraim, and there he sojourned with the disciples.
55የአይሁድም ፋሲካ ቀርቦ ነበር። ብዙ ሰዎችም ራሳቸውን ያነጹ ዘንድ ከፋሲካ በፊት ከአገሩ ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ።
55But the passover of the Jews was near, and many went up to Jerusalem out of the country before the passover, that they might purify themselves.
56ኢየሱስንም ይፈልጉት ነበር፤ በመቅደስም ቆመው እርስ በርሳቸው። ምን ይመስላችኋል? ወደ በዓሉ አይመጣም ይሆንን? ተባባሉ።
56They sought therefore Jesus, and said among themselves, standing in the temple, What do ye think? that he will not come to the feast?
57የካህናት አለቆችም ፈሪሳውያንም ይይዙት ዘንድ እርሱ ያለበትን ስፍራ የሚያውቀው ሰው ቢኖር እንዲያመለክታቸው አዘው ነበር።
57Now the chief priests and the Pharisees had given commandment that if any one knew where he was, he should make it known, that they might take him.