Amharic: New Testament

Darby's Translation

Luke

2

1በዚያም ወራት ዓለሙ ሁሉ እንዲጻፍ ከአውግስጦስ ቄሣር ትእዛዝ ወጣች።
1But it came to pass in those days that a decree went out from Caesar Augustus, that a census should be made of all the habitable world.
2ቄሬኔዎስ በሶርያ አገር ገዥ በነበረ ጊዜ ይህ የመጀመሪያ ጽሕፈት ሆነ።
2The census itself first took place when Cyrenius had the government of Syria.
3ሁሉም እያንዳንዱ ይጻፍ ዘንድ ወደ ከተማው ሄደ።
3And all went to be inscribed in the census roll, each to his own city:
4ዮሴፍም ደግሞ ከዳዊት ቤትና ወገን ስለ ነበረ ከገሊላ ከናዝሬት ከተማ ተነሥቶ ቤተ ልሔም ወደምትባል ወደ ዳዊት ከተማ ወደ ይሁዳ፥ ፀንሳ ከነበረች ከእጮኛው ከማርያም ጋር ይጻፍ ዘንድ ወጣ።
4and Joseph also went up from Galilee out of the city Nazareth to Judaea, to David's city, the which is called Bethlehem, because he was of the house and family of David,
6በዚያም ሳሉ የመውለጃዋ ወራት ደረሰ፥
5to be inscribed in the census roll with Mary who was betrothed to him [as his] wife, she being great with child.
7የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥ በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው በግርግም አስተኛችው።
6And it came to pass, while they were there, the days of her giving birth [to her child] were fulfilled,
8በዚያም ምድር መንጋቸውን በሌሊት ሲጠብቁ በሜዳ ያደሩ እረኞች ነበሩ።
7and she brought forth her first-born son, and wrapped him up in swaddling-clothes and laid him in the manger, because there was no room for them in the inn.
9እነሆም፥ የጌታ መልአክ ወደ እነርሱ ቀረበ የጌታ ክብርም በዙሪያቸው አበራ፥ ታላቅ ፍርሃትም ፈሩ።
8And there were shepherds in that country abiding without, and keeping watch by night over their flock.
10መልአኩም እንዲህ አላቸው። እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤
9And lo, an angel of [the] Lord was there by them, and [the] glory of [the] Lord shone around them, and they feared [with] great fear.
11ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።
10And the angel said to them, Fear not, for behold, I announce to you glad tidings of great joy, which shall be to all the people;
12ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ።
11for to-day a Saviour has been born to you in David's city, who is Christ [the] Lord.
13ድንገትም ብዙ የሰማይ ሠራዊት ከመልአኩ ጋር ነበሩ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ።
12And this is the sign to you: ye shall find a babe wrapped in swaddling-clothes, and lying in a manger.
14ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።
13And suddenly there was with the angel a multitude of the heavenly host, praising God and saying,
15መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ፥ እረኞቹ እርስ በርሳቸው። እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ ተባባሉ።
14Glory to God in the highest, and on earth peace, good pleasure in men.
16ፈጥነውም መጡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ።
15And it came to pass, as the angels departed from them into heaven, that the shepherds said to one another, Let us make our way then now as far as Bethlehem, and let us see this thing that is come to pass, which the Lord has made known to us.
17አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ።
16And they came with haste, and found both Mary and Joseph, and the babe lying in the manger;
18የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሩአቸው ነገር አደነቁ፤
17and having seen [it] they made known about the country the thing which had been said to them concerning this child.
19ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር።
18And all who heard [it] wondered at the things said to them by the shepherds.
20እረኞችም እንደ ተባለላቸው ስለ ሰሙትና ስላዩት ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እያከበሩ ተመለሱ።
19But Mary kept all these things [in her mind], pondering [them] in her heart.
21ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥ በማኅፀን ሳይረገዝ በመልአኩ እንደ ተባለ፥ ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ።
20And the shepherds returned, glorifying and praising God for all things which they had heard and seen, as it had been said to them.
22እንደ ሙሴም ሕግ የመንጻታቸው ወራት በተፈጸመ ጊዜ፥ በጌታ ሕግ። የእናቱን ማኅፀን የሚከፍት ወንድ ሁሉ ለጌታ የተቀደሰ ይባላል ተብሎ እንደ ተጻፈ በጌታ ፊት ሊያቆሙት፥ በጌታም ሕግ። ሁለት ዋሊያ ወይም ሁለት የርግብ ጫጩቶች እንደ ተባለ፥ መሥዋዕት ሊያቀርቡ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት።
21And when eight days were fulfilled for circumcising him, his name was called Jesus, which was the name given by the angel before he had been conceived in the womb.
25እነሆም፥ በኢየሩሳሌም ስምዖን የሚባል ሰው ነበረ፥ ይህም ሰው የእስራኤልን መጽናናት ይጠባበቅ ነበር፤ ጻድቅና ትጉህም ነበረ፥ መንፈስ ቅዱስም በእርሱ ላይ ነበረ።
22And when the days were fulfilled for their purifying according to the law of Moses, they brought him to Jerusalem to present [him] to the Lord
26በጌታም የተቀባውን ሳያይ ሞትን እንዳያይ በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ ነበር።
23(as it is written in the law of [the] Lord: Every male that opens the womb shall be called holy to the Lord),
27በመንፈስም ወደ መቅደስ ወጣ፤ ወላጆቹም እንደ ሕጉ ልማድ ያደርጉለት ዘንድ ሕፃኑን ኢየሱስን በአስገቡት ጊዜ፥
24and to offer a sacrifice according to what is said in the law of [the] Lord: A pair of turtle doves, or two young pigeons.
28እርሱ ደግሞ ተቀብሎ አቀፈው እግዚአብሔርንም እየባረከ እንዲህ አለ።
25And behold, there was a man in Jerusalem whose name was Simeon; and this man was just and pious, awaiting the consolation of Israel, and [the] Holy Spirit was upon him.
29ጌታ ሆይ፥ አሁን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ፤
26And it was divinely communicated to him by the Holy Spirit, that he should not see death before he should see [the] Lord's Christ.
30ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና፤
27And he came in the Spirit into the temple; and as the parents brought in the child Jesus that they might do for him according to the custom of the law,
32ይህም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን ለሕዝብህም ለእስራኤል ክብር ነው።
28*he* received him into his arms, and blessed God, and said,
33ዮሴፍና እናቱም ስለ እርሱ በተባለው ነገር ይደነቁ ነበር።
29Lord, now thou lettest thy bondman go, according to thy word, in peace;
34ስምዖንም ባረካቸው እናቱን ማርያምንም። እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥ በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት።
30for mine eyes have seen thy salvation,
36ከአሴር ወገንም የምትሆን የፋኑኤል ልጅ ሐና የምትባል አንዲት ነቢይት ነበረች፤ እርስዋም ከድንግልናዋ ጀምራ ከባልዋ ጋር ሰባት ዓመት ኖረች፤
31which thou hast prepared before the face of all peoples;
37እርስዋም ሰማኒያ አራት ዓመት ያህል መበለት ሆና በጣም አርጅታ ነበር፤ በጾምና በጸሎትም ሌሊትና ቀን እያገለገለች ከመቅደስ አትለይም ነበር።
32a light for revelation of [the] Gentiles and [the] glory of thy people Israel.
38በዚያችም ሰዓት ቀርባ እግዚአብሔርን አመሰገነች፤ የኢየሩሳሌምንም ቤዛ ለሚጠባበቁ ሁሉ ስለ እርሱ ትናገር ነበር።
33And his father and mother wondered at the things which were said concerning him.
39ሁሉንም እንደ ጌታ ሕግ ከፈጸሙ በኋላ፥ ወደ ገሊላ ወደ ከተማቸው ወደ ናዝሬት ተመለሱ።
34And Simeon blessed them, and said to Mary his mother, Lo, this [child] is set for the fall and rising up of many in Israel, and for a sign spoken against;
40ሕፃኑም አደገ፥ ጥበብም ሞልቶበት በመንፈስ ጠነከረ፤ የእግዚአብሔርም ጸጋ በእርሱ ላይ ነበረ።
35(and even a sword shall go through thine own soul;) so that [the] thoughts may be revealed from many hearts.
41ወላጆቹም በያመቱ በፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ይወጡ ነበር።
36And there was a prophetess, Anna, daughter of Phanuel, of [the] tribe of Asher, who was far advanced in years, having lived with [her] husband seven years from her virginity,
42የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ፥ እንደ በዓሉ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ፤
37and herself a widow up to eighty-four years; who did not depart from the temple, serving night and day with fastings and prayers;
43ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ፥ ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፥ ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር።
38and she coming up the same hour gave praise to the Lord, and spoke of him to all those who waited for redemption in Jerusalem.
44ከመንገደኞች ጋር የነበረ ስለ መሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ፥ ከዘመዶቻቸውም ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት፤
39And when they had completed all things according to the law of [the] Lord, they returned to Galilee to their own city Nazareth.
45ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ።
40And the child grew and waxed strong [in spirit], filled with wisdom, and God's grace was upon him.
46ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ አገኙት፤
41And his parents went yearly to Jerusalem at the feast of the passover.
47የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ።
42And when he was twelve years old, and they went up [to Jerusalem] according to the custom of the feast
48ባዩትም ጊዜ ተገረሙ፥ እናቱም። ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው።
43and had completed the days, as they returned, the boy Jesus remained behind in Jerusalem, and his parents knew not [of it];
49እርሱም። ስለ ምን ፈለጋችሁኝ? በአባቴ ቤት እሆን ዘንድ እንዲገባኝ አላወቃችሁምን? አላቸው።
44but, supposing him to be in the company that journeyed together, they went a day's journey, and sought him among their relations and acquaintances:
50እነርሱም የተናገራቸውን ነገር አላስተዋሉም።
45and not having found him they returned to Jerusalem seeking him.
51ከእነርሱም ጋር ወርዶ ወደ ናዝሬት መጣ፥ ይታዘዝላቸውም ነበር። እናቱም ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ ትጠብቀው ነበር።
46And it came to pass, after three days they found him in the temple, sitting in the midst of the teachers and hearing them and asking them questions.
52ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።
47And all who heard him were astonished at his understanding and answers.
48And when they saw him they were amazed: and his mother said to him, Child, why hast thou dealt thus with us? behold, thy father and I have sought thee distressed.
49And he said to them, Why [is it] that ye have sought me? did ye not know that I ought to be [occupied] in my Father's business?
50And they understood not the thing that he said to them.
51And he went down with them and came to Nazareth, and he was in subjection to them. And his mother kept all these things in her heart.
52And Jesus advanced in wisdom and stature, and in favour with God and men.