1ጢባርዮስ ቄሣርም በነገሠ በአሥራ አምስተኛይቱ ዓመት፥ ጴንጤናዊው ጲላጦስም በይሁዳ ሲገዛ፥ ሄሮድስም በገሊላ የአራተኛው ክፍል ገዥ፥ ወንድሙ ፊልጶስም በኢጡርያስ በጥራኮኒዶስም አገር የአራተኛው ክፍል ገዥ፥ ሊሳኒዮስም በሳቢላኒስ የአራተኛው ክፍል ገዥ ሆነው ሳሉ፥
1Now in the fifteenth year of the government of Tiberius Caesar, Pontius Pilate being governor of Judaea, and Herod tetrarch of Galilee, and Philip his brother tetrarch of Ituraea and the region of Trachonitis, and Lysanias tetrarch of Abilene,
2ሐናና ቀያፋም ሊቃነ ካህናት ሳሉ፥ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ዘካርያስ ልጅ ወደ ዮሐንስ በምድረ በዳ መጣ።
2in the high priesthood of Annas and Caiaphas, [the] word of God came upon John, the son of Zacharias, in the wilderness.
3በነቢዩ በኢሳይያስ ቃል መጽሐፍ። የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ፤ ዐዘቅቱ ሁሉ ይሙላ ተራራውና ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይበል፥ ጠማማውም የቀና መንገድ ይሁን፥ ሸካራውም መንገድ ትክክል ይሁን፤ ሥጋም የለበሰ ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ይይ ተብሎ እንደ ተጻፈ ለኃጢአት ስርየት የንስሐን ጥምቀት እየሰበከ በዮርዳኖስ ዙሪያ ወዳለችው አገር ሁሉ መጣ።
3And he came into all the district round the Jordan, preaching [the] baptism of repentance for [the] remission of sins,
7ስለዚህ ከእርሱ ሊጠመቁ ለወጡት ሕዝብ እንዲህ ይላቸው ነበር። እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ከሚመጣው ቍጣ እንድትሸሹ ማን አመለከታችሁ?
4as it is written in [the] book of [the] words of Esaias the prophet: Voice of one crying in the wilderness: Prepare ye the way of [the] Lord, make straight his paths.
8እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ፤ በልባችሁም። አብርሃም አባት አለን ማለትን አትጀምሩ፤ ከእነዚህ ድንጋዮች ለአብርሃም ልጆች ሊያስነሣለት እግዚአብሔር እንዲችል እላችኋለሁና።
5Every gorge shall be filled up, and every mountain and hill shall be brought low, and the crooked [places] shall become a straight [path], and the rough places smooth ways,
9አሁንስ ምሳር ደግሞ በዛፎች ሥር ተቀምጦአል፤ እንግዲህ መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል ወደ እሳትም ይጣላል።
6and all flesh shall see the salvation of God.
10ሕዝቡም። እንግዲህ ምን እናድርግ? ብለው ይጠይቁት ነበር።
7He said therefore to the crowds which went out to be baptised by him, Offspring of vipers, who has forewarned you to flee from the coming wrath?
11መልሶም። ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው ያካፍል፥ ምግብም ያለው እንዲሁ ያድርግ ይል ነበር።
8Produce therefore fruits worthy of repentance; and begin not to say in yourselves, We have Abraham for [our] father, for I say unto you that God is able of these stones to raise up children to Abraham.
12ቀራጮችም ደግሞ ሊጠመቁ መጥተው። መምህር ሆይ፥ ምን እናድርግ? አሉት።
9And already also the axe is applied to the root of the trees; every tree therefore not producing good fruit is cut down and cast into [the] fire.
13ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ አላቸው።
10And the crowds asked him saying, What should we do then?
14ጭፍሮችም ደግሞ። እኛ ደግሞ ምን እናድርግ? ብለው ይጠይቁት ነበር። እርሱም። በማንም ግፍ አትሥሩ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፥ ደመወዛችሁም ይብቃችሁ አላቸው።
11And he answering says to them, He that has two body-coats, let him give to him that has none; and he that has food, let him do likewise.
15ሕዝቡም ሲጠብቁ ሳሉ ሁሉም በልባቸው ስለ ዮሐንስ። ይህ ክርስቶስ ይሆንን? ብለው ሲያስቡ ነበር፥
12And tax-gatherers came also to be baptised, and they said to him, Teacher, what should we do?
16ዮሐንስ መልሶ። እኔስ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ነገር ግን የጫማውን ጠፍር መፍታት ከማይገባኝ ከእኔ የሚበረታ ይመጣል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል፤
13And he said to them, Take no more [money] than what is appointed to you.
17መንሹም በእጁ ነው፥ አውድማውንም ፈጽሞ ያጠራል፥ ስንዴውንም በጎተራው ይከታል፥ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል አላቸው።
14And persons engaged in military service also asked him saying, And we, what should we do? And he said to them, Oppress no one, nor accuse falsely, and be satisfied with your pay.
18ስለዚህ ሕዝቡን በብዙ ሌላ ምክር እየመከራቸው ወንጌልን ይሰብክላቸው ነበር፤
15But as the people were in expectation, and all were reasoning in their hearts concerning John whether *he* might be the Christ,
19የአራተኛው ክፍል ገዥ ሄሮድስ ግን፥ ስለ ሄሮድያዳ ስለ ወንድሙ ስለ ፊልጶስ ሚስትና ሄሮድስ ስላደረገው ሌላ ክፋት ሁሉ ዮሐንስ ስለ ገሠጸው፥
16John answered all, saying, *I* indeed baptise you with water, but the mightier than I is coming, the thong of whose sandals I am not fit to unloose; *he* shall baptise you with [the] Holy Spirit and fire;
20ይህን ደግሞ ከሁሉ በላይ ጨምሮ ዮሐንስን በወኅኒ አገባው።
17whose winnowing-fan is in his hand, and he will thoroughly purge his threshing-floor, and will gather the wheat into his garner, but the chaff he will burn with fire unquenchable.
21ሕዝቡም ሁሉ ከተጠመቁ በኋላ ኢየሱስ ደግሞ ተጠመቀ። ሲጸልይም ሰማይ ተከፈተ፥
18Exhorting then many other things also he announced [his] glad tidings to the people.
22መንፈስ ቅዱስም በአካል መልክ እንደ ርግብ በእርሱ ላይ ወረደ፤ የምወድህ ልጄ አንተ ነህ፥ በአንተ ደስ ይለኛል የሚል ድምፅም ከሰማይ መጣ።
19But Herod the tetrarch, being reproved by him as to Herodias, the wife of his brother, and as to all the wicked things which Herod had done,
23ኢየሱስም ሊያስተምር ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ያህል ሆኖት ነበር እንደመሰላቸው የዮሴፍ ልጅ ሆኖ፥ የኤሊ ልጅ፥
20added this also to all [the rest], that he shut up John in prison.
24የማቲ ልጅ፥ የሌዊ ልጅ፥ የሚልኪ ልጅ፥
21And it came to pass, all the people having been baptised, and Jesus having been baptised and praying, that the heaven was opened,
25የዮና ልጅ፥ የዮሴፍ ልጅ፥ የማታትዩ ልጅ፥ የአሞጽ ልጅ፥ የናሆም ልጅ፥ የኤሲሊም ልጅ
22and the Holy Spirit descended in a bodily form as a dove upon him; and a voice came out of heaven, *Thou* art my beloved Son, in thee I have found my delight.
26የናጌ ልጅ፥ የማአት ልጅ፥ የማታትዩ ልጅ የሴሜይ ልጅ፥ የዮሴፍ ልጅ፥
23And Jesus himself was beginning to be about thirty years old; being as was supposed son of Joseph; of Eli,
27የዮዳ ልጅ፥ የዮናን ልጅ፥ የሬስ ልጅ፥ የዘሩባቤል ልጅ፥ የሰላትያል ልጅ፥ የኔሪ ልጅ፥
24of Matthat, of Levi, of Melchi, of Janna, of Joseph,
28የሚልኪ ልጅ፥ የሐዲ ልጅ፥ የዮሳስ ልጅ፥ የቆሳም ልጅ፥ የኤልሞዳም ልጅ፥ የኤር ልጅ፥
25of Mattathias, of Amos, of Naoum, of Esli, of Naggai,
29የዮሴዕ ልጅ፥ የኤልዓዘር ልጅ የዮራም ልጅ፥ የማጣት ልጅ፥ የሌዊ ልጅ፥
26of Maath, of Mattathias, of Semei, of Joseph, of Juda,
30የስምዖን ልጅ፥ የይሁዳ ልጅ፥ የዮሴፍ ልጅ፥
27of Joannes, of Resa, of Zorobabel, of Salathiel, of Neri,
31የዮናን ልጅ፥ የኤልያቄም ልጅ፥ የሜልያ ልጅ፥ የማይናን ልጅ፥ የማጣት ልጅ፥ የናታን ልጅ
28of Melchi, of Addi, of Cosam, of Elmodam, of Er,
32የዳዊት ልጅ፥ የእሴይ ልጅ፥ የኢዮቤድ ልጅ፥ የቦዔዝ ልጅ፥ የሰልሞን ልጅ፥
29of Joses, of Eliezer, of Joreim, of Matthat, of Levi,
33የነአሶን ልጅ፥ የአሚናዳብ ልጅ፥ የአራም ልጅ፥ የአሮኒ ልጅ፥ የኤስሮም ልጅ፥
30of Simeon, of Juda, of Joseph, of Jonan, of Eliakim,
34የፋሬስ ልጅ፥ የይሁዳ ልጅ፥ የያዕቆብ ልጅ፥ የይስሐቅ ልጅ፥ የአብርሃም ልጅ፥ የታራ ልጅ፥
31of Meleas, of Menan, of Mattatha, of Nathan, of David,
35የናኮር ልጅ፥ የሴሮህ ልጅ፥ የራጋው ልጅ፥ የፋሌቅ ልጅ፥ የአቤር ልጅ፥ የሳላ ልጅ፥
32of Jesse, of Obed, of Booz, of Salmon, of Naasson,
36የቃይንም ልጅ፥ የአርፋክስድ ልጅ፥ የሴም ልጅ፥ የኖኅ ልጅ፥ የላሜህ ልጅ፥
33of Aminadab, of Aram, of Esrom, of Phares, of Juda,
37የማቱሳላ ልጅ፥ የሄኖክ ልጅ፥ የያሬድ ልጅ፥
34of Jacob, of Isaac, of Abraham, of Terah, of Nachor,
38የመላልኤል ልጅ፥ የቃይናን ልጅ፥ የሄኖስ ልጅ፥ የሴት ልጅ፥ የአዳም ልጅ፥ የእግዚአብሔር ልጅ።
35of Seruch, of Ragau, of Phalek, of Eber, of Sala,
36of Cainan, of Arphaxad, of Sem, of Noe, of Lamech,
37of Methusala, of Enoch, of Jared, of Maleleel, of Cainan,
38of Enos, of Seth, of Adam, of God.